Being a light in this world.
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈሳዊ ውጊያ ምን ያስተምራል?
በፈቀደው አልፎ ወደ ፈቃዱ መድረስ
በፈቀደው አልፎ ወደ ፈቃዱ መድረስ
ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ሲገጥሙን እንዴት ምላሽ እንጣለን
ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ሲገጥሙን እንዴት ምላሽ እንጣለን
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
በቤተሰብ ዙሪያ የቀረበ - የጥያቄና የመልስ ጊዜ
በህልም ዙሪያ የቅረበ - የጥያቄና የመልስ ጊዜ
የእግዚአብሔር መላዕክት ዙሪያ የቀረበ - የጥያቄና የመልስ ጊዜ
በሕይወት ሙላት ዙሪያ የቅረበ - የጥያቄና የመልስ ጊዜ 1
በሕይወት ሙላት ዙሪያ የቅረበ - የጥያቄና የመልስ ጊዜ 2
በሕይወት ሙላት ዙሪያ የቅረበ - የጥያቄና የመልስ ጊዜ 3
ጸሎታችንና የእግዚአብሔር ማንነት - ክፍል 1
ጸሎታችንና የእግዚአብሔር ማንነት - የጥያቄና የመልስ ጊዜ - ክፍል 1
ጸሎታችንና የእግዚአብሔር ማንነት - ክፍል 2
ጸሎታችንና የእግዚአብሔር ማንነት - የጥያቄና የመልስ ጊዜ - ክፍል 2
እግዚአብሔር ወደፊት የሚያሰኬደን ደግሞም የሚባርከን በጎውን ሀሳብ በቃሉ አማካኝነት ወደእኛ በማምጣት ነው:: ቃሉ ሲመጣ የአሰተሳሰባችን ቅኝት ይቀየራል ከወንድሞች ጋርም ያለን ህብረትም ይፈወሳል:: ጠላትም ሊጎትተን ደግሞም ሊጥለን ሲፈልግ ሥራ የሚጀምረው ሀሳባችን ላይ ነው:: ዛሬ የምናስበው ሀሳብ የነገውን ቁመናችንን ይወስናል ወደፊት ለመሔድ ወይንም ለመቆማችን ምክንያት ነው::
እግዚአብሔር አምላኩ የሆነ ገዢው የሆነ መሪው የሆነ ሰው በሚያልፍበት ማንኛውም ችግር መፍትሔ የሚያገኘው ከራሱ ከእግዚአብሔር ነው:: ሰው በራሱ የሚወሰደው አርምጃ ራሱ የሚጎዳበት ደግሞም አግዚአብሔርን የማያሰከብር ይሆናል:: *** ለችግሮቻችን መፍትሔ የሚመጣው የሚመነጨው የአካሉ ራስ ከሆነው በነገር ሀሉ ክብርን ልንሰጠው ከተገባው ከእግዚአብሔር ዘንዱ ነው:: አኛን ይጠቅማል ጌታንም ያከብራልና::
ክርስትና የግለኝነት ህይወት አይደለም:: የተጠራነው ደግሞም የምንኖረው ለአካሉ ነው:: የአንዱን መከራ ሌላው እየተሰማው በፀጋው አቅም የምንኖረው ኑሮ ነው:: በፀጋው ለመኖር መረጥን ማለት ደግሞ ለመስቀሉ በቃን ማለት ነው:: መሰቀልን ያራቀ ደግሞም ወደ ህግ ዘወር ያለ ህይወትና ኑሮ እውነተኛውን የወንጌል ኑሮ እየኖረ አይደለም::
እግዚአብሔር እርሱ ሉአላዊ አምላክ ነው:: ስህተት በእርሱ ዘንድ የለም የፈቀደውን ያደርጋል:: ይህን ሲያደርግ ደግሞ አርሱ ፍፀም ፃድቅ ነው:: ሰለዚህ አካሔድን ከእርሱ ጋር ለማድረግ ወደ ልቡ ፈቃድ መድረስ ሀሳቡንም መረዳት ያስፈልጋል:: ወደ ልቡ ፈቃድ ለመድረስ ቀዳሚው ደግሞ ከራሰ መውጣት ነው:: *** ከራሱ የወጣ ወደ ጌታም ወደ ልቡ ፈቃድ የደረሰ እርሱ የእግዚአብሔር ምስጢረኛ ነው ደግሞም መልካም ሰለሆነው ብቻ ሳይሆን መልካም በማይመስለውም ሰለሁሉ ያመሰግናል:
አግዚአብሔርን ማወቅ ብቃት ነው:: የሰው መንፈሳዊ ብቃቱ እግዚአብሔርን ባወቀበት ልክ ነው:: በመከራ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ እርሱ ይበረታል ይፀናልም:: *** በዚህ አሰጨናቂ አለም ክፉውን ፀንተን መቃወም የምንችለው ተስፋችንም እለተ እለት የሚታደሰው ጌታ ከእኛ ጋር መሆኑን ባወቅነው መጠን ነው::
አማኝ ሁልጊዜ የህይወት ሙላት እንዲኖረው የእግዚአብሔረ ቃል ያዛል:: የአገዚአብሐር ነገር በእኛ ውስጥ ሲያልፍ ስንፀለይ ቃሉን ስናነብ ከቅዱሳን ጋር ህብረት ስናደርግ ለመነፈሳዊ ህይወታችን ሙላት ይሰማናል:: በጌታ ተምህርት ምክርና ምሪት ውስጥ የሆነ አርሱ በሙላት ውስጥ እንዳለ ይታወቀዋል:: ነገር ግን የጌታን ምክር በራሱ ሀሳብ የተካ በምክሩም ያልተመራ በባዶነት ይኖራል:: *** በሙላት ውስጥ ያለ ሰው እርሱ የራሱን ነገር ወደ ጌታ አምጥቶ የጣለ የእግዚአብሔርም ፈቃድና ሀሳብ በእርሱ ውስጥ የሚያልፍነው::
የእግዚአብሔር ጥልቅ ምስጢር ጌታ ኢየሱስ ነው:: ይህም ምስጢር ስጋና ደም ሊረዳውና ሊያውቀው የማይችል ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ የሚገለጥ ነው:: ወደ እግዚአብሔረ ጥልቅ ነገር መግባት መድረስ የምንችለው ጌታ ወደ እኛ ጥልቅ የደረሰውን ያህል ነው:: ደግሞም ጌታ ወደ ህይወታችን ጥልቅ የሚደርሰው እኛ የፈቀድለትን ያህል ነው:: *** ጌታ ምን ያህል ወይም የት ድረስ ነው ወደ ህይወቴ ጠልቆ የገባው? እኔስ ምን ያህል ነው ወደ ጌታ ጥልቅ ነገር የገባሁት? የሚሉት ጥያቄዎች ሁልጊዜ አማኝ ራሱን የሚያይበት ጥያቄዎቸ ናቸው::
አግዚአብሔር ቃሉን ሲልክ ቃሉን ሲያፈስ ፈቃዱን ለመግለጥ ነው:: ደግሞም ቃሉን ተከትሎ የሚገለጥ የአግዚአብሔር ክብር አለ:: ቃሉ ፈቃዱን እንዲፈፅም ደግሞም ፍሬ እነዲያፈራ ቃሉ የሚወድቅበት ልብ ወሳኝ ነው:: በፈተና ውስጥም ያልፋል:: በዚህ ትምህርት አራት አይነት የቃሉን አቀባበልና ፍሬ ማፍራት እናያለ::
እግዙአብሔር አሰራሩ ውስን ስላልሆነ የቀደመውን አታስታውሱ ይላል:: ሰለዚህም ደግሞ አዲስን ነገር አሁን አደርጋለሁ ይላል:: አደራረጉ አይለመድምና የጌታ ስራ በልምድ አይሰራም:: *** በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ እንሁን አዲስን ነገር አደርርጋለሁ ያለ የእርሱ መገኘት ችግሮቻችን ሳይለወጡ ለእኛ የህይወት ለውጥ በረከትና ክብርን ያመጣል:;
የሰው ህይወቱ በመፈለግ የተሞላ ነው:: መንፈሳዊውንም ሆነ ስጋዊውን እንፈልጋለን:: በህይወታችን ሳንፈልገው ያገኘነው መዳንን ብቻ ነው:: ጌታ ራሱ ፈልጎ አገኘን እንጂ:: ከዳንን በኃላ ግን ብዙ የምንፈልጋቸው ነገሮች አሉ:: የእግዚአብሔርም ቃል ፈልጉ ታገኛላችሁ ሲል መፈለግ አንዱ የህይወታችን ክፍል እንደሆነ ይጠቁማል:: *** የምንፈልገውን ሁሉ እንደምናገኝ ወይም እንደምንቀበል ዋስትና አልተሰጠንም ነገር ግን እግዚአብሔር እነደ ወደደ ለእርሱ ክብር የሚያመጣውን ለእኛም ደግሞ የሚጠቅመንን ይሰጠናል እንጂ::
እግዚአብሔር በተናገረው ቃል አይኖቻችን ሲበሩ እኛ በዛ ቃል ውስጥ እንሆናለን:: ቃሉን ብዙ ልንናገር እንችላለን: ነገር ግን ቃሉ ተገልጦልን በርቶልን እግዚአብሔርን ካየነው በላይ ማየት አንችልም:: ፍሬያችንም በተናገርነው መጠን ሳይሆን በቃሉ ባየነው ልክ ነው:: *** እግዚአብሔር በቃሉ የተናገረው በተናገረውም ውስጥ ራሱን ያገኘ እርሱ በጉድለት በፈተናና በመከራም ውስጥ ቢሆንም እንኳ ነገሮች ሳይለወጡ የተረጋጋና የፀና ነው::
በክርስትና ህይወታችን እየተሰራን ጌታን የህይወታችን ሙላት ወደ ማድረግ የምናድግበት መንገድ አንዱ መጠበቅ ነው:: እግዚአብሔርን መጠበቅ ማለት በእርሱ መንገድ መሄድ ማለት ነው:: እግዚአብሔር በአጋጣሚ አይባርክም በዘላለም ሀሳቡ እንዳቀደ በራሱ መንገድ እንጂ:: ጌታን የሚጠብቅ እርሱ ሰውን አያይም በሰውም አይጎዳም ደግሞም በመጠበቅ ውሰጥ ጊዜ አይወስንም ጌታ የራሱ ጊዜ አለውና::
መንፈሳዊ ከፍታ የእግዚአብሔረ አላማ በህይወታችን የሚከናወንበት በእርሱም በረከት የምንባረክበት ደግሞም በእርሱ አሸናፊነት አሸናፊውን ህይወት መኖር የምንጀምርበት ነው:: *** በእግዚአብሔረ ፀጋ ውስጥ ራሳችንን ያገኘንበት: ጨርሰን ከራሳችን ወጥተን ፀጋው ብቻ በእኛ የሚሰራበት እርሱ ነው ከፍታችን::
ምሪት የሚያስፈልገን የምንኖረው ኑሮ የእግዚአብሔር ኑሮ ሲሆን ነው:: በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር ሰንሆን በእውቀት እያደግን ስንመጣ ወደ እገዚአብሔር ፈቃድ የምንደርስበትን ምሪት እንቀበላለን:: ሰው ከእግዚአብሔር ሰአት ጋር የሚራመደው ራዕይ ስላለው ሳይሆን ምሪት ስላለው ነው:: ያለ ምሪት የሆኑ ሰዎች እነርሱ በራሳቸው ጊዜ ይወጣሉ በራሳቸው ጊዜ ይገባሉ::
የመንፈስ ቅዱስ ምሪት በመጀመሪያ በእርሱ ላይ የተጣለ ማንነትን ይሻል:: በእርሱ ላይ የተጣለ ደግሞ የእኔ የሚለው አማራጭ ሰለማይኖረው በምሪቱ ደስተኛ ነው:: እግዚአብሔረም በራሱ መንገድ ነገሮችን መገጣጠም ይጀምራል:: *** እግዚአብሔር እርሱ በማይቀድምበት አይመራንም:: ጌታ ሲመራን ከፊት ያለውን የሚያይልን ጌታ እርሱ ይቀድማል እኛም እነከተላለን::
እኛ ሰዎች ነንና የመንፈስ ቅዱስን ፈቃድ የምናውቀው ከፍለን ነው:: ምሪቱ የሚገባን ደግሞም ፈቅደን የምንቀበለው በራሳችን ነገርና ሁኔታ ባልተያዝንበት መጠን ነው:: የመንፈስ ምሪት ትክክለኛውን መንገድ እንድንሔድ እንድንኖርም ያደርጋል:: ይህ በፀጋው ችሎት እነጂ በእኛ አይደለም:: *** የመንፈስ ቅዱስ ምሪት ለህይወታችን ደግሞም በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ለምንስራው ስራ ፍሬያማነት ዋነኛ ነው::
እግዚአብሔር ህዝቡን በመንገዱ ይመራል:: ሲመራም በድልና በሸናፊነት ነው:: በመንገዳችን እርሱ ከእኛ ይሁን እንጂ ተግዳሮቶቻችንን እናልፋቸዋለን:: በእኛ ማንነት ሳይሆን በፀጋ ሐይልና ጉልበት:: *** እግዚአብሔር የሚያስኬደን መንገድ ሁልጊዜ በእምነትና በመታዘዝ አንድንከተል የሚጠይቅ ደግሞም ሰላምንም የሚሞላ ነው::
እውነተኛ የሆነ የክርስቶስ ህይወት ኑሮ ባለበት በዛ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት አለ:: በመንፈስ ምሪት ውስጥ ያለውም የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው:: የእርሱም ፈቃድ በእኛ የሚሰራው ደግሞ የራሳችንን ፈቃድ በተውንበት በጣልንበት ነው:: *** ሁሉን የሚችል አምላክ ፈቃዱን በእኛ ድካም ውስጥ ሊፈፅም በወደደ ጊዜ የእኛ ድርሻ ምሪቱን መቀበል መታዘዝ ደግሞም ፈቃዱን የሚፈፅመውን ጌታ ማሰቀደም እኛም ደግሞ መከተል ነው::
እግዚአብሔር ሰላምና እረፍትን ወደ ህይወታችን ሲያመጣ አላማው ወደ እርሱ እንድንጠጋና በምስጋና እንድንሆን ነው:: በሰላም ጊዜ እግዚአብሔር እንዳለና እንደሚመራን እንዲሁ የጨለማ ጊዜ የመከራ ጊዜ በምንለውም ውስጥ እርሱ አለ ይመራናልም:: በዚህም ውስጥ ምስጋና ለእግዚአብሔር ነው:: *** በነገር ሁሉ እግዚአብሔርን ስናመሰግን የምናደርገው እግዚአብሔርን ከፊት እኛን ከኃላ::
ፀሎት ሸክም ነው :: ደገሞም ተዕዛዝ ነው:: ፀሎት በጉዳያችን ውስጥ ጌታን ማኖር ነው:: የሚፀልይ ሰው የሌለውን ነገር ወደፊት ያያል በፈረሰው ላይ ቆሞ የሚገነባውን የሚተደሰውን ያያል:: ዛሬ ላይ ሆኖ ነገን ያያል:: *** ሁላችን የምንፀልየው በሊቀካህኑ በኢየሱስ ስር ሆነን ነው:: ሰለዚህ ፀሎታችን ኢየሱስን በመምስል መሆን አለበት:/ የፍቅር ሰው: ይቅር ባይ: ትሁት ወዘተ.../::
እግዚአብሔር አዲስ ነገር አደረጋለሁ የቀደመውን አታስቡ ሲል: በዘመናት ድንቅን የሚያደርግ ክንዱን ሀይሉንና ብርታቱን ሳይሆን: አታስቡ የሚለው አደራረጉን ነው:: እግዚአብሔር እርሱ ሀሳቡን እንደወደደ በራሱ መንገድ ይሰራልና አሰራሩ ሁልጊዜ አንድ አይነት አይደለም:: *** የእግዚአብሔር ህልውና መገኘት ከእኛ ጋር ይሁን እንጂ ከፊታችን ባለው አስፈሪና አሰጨናቂ ሁኔታ ላይ የምንሻገርበትንና የምናልፍበትን ያልተጠባበቅነውን አዲስ ነገር ያደርጋል:: ምስጋናም ይበዛልናል::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 1:1-4
ሁለንተናችንን ወደሚቆጣጠር ጠሊቅ ወደሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ ስንገባ ወደ ጠለቀ ፀሎት ውስጥ እንገባለን:: ወደዚህ ፀሎት ስንገባ የመጀመሪያው በጌታ ፊት ራስን ማዋረድና ዝቅ ማድረግ ነው:: ከራሳችን ፈቃድ ወጥተን ለጌታ ፈቃድ እንገዛለን እንታዘዛለንም:: ጌታም ወደ ከፍታ ያወጣናል:: *** ነጋችን ሲያስፈራን: ከእኛ ያለፈ ለአካባቢ ለህብረተሰብ ለሀገር ሸክም ሲኖረን እነዲሁም በመንፈሳዊ ህይወታችን ፈተና ሲመጣ ወዘተ.. የጠለቀ ፀሎት ውሰጥ እንድንገባ ምክንያቶች ናቸው::
መንፈሳዊ ሰው ከውጭ የሚሰማው ተፅዕኖ አያደርግበትም:: ነገር ግን ያን የሰማውን ወደ ጌታ ያቀርባል::የእግዚአብሔርን ሀሳብ ይጠይቅበታል:: መንፈሳዊ ስንሆን እግዚአብሔር በቀላሉ አያልፈንም:: ይናገረናል:: *** ለመንፈሳዊ ምሪት ከሚያስፈልገን አንዱ የትብብር መንፈሰ ነው:: ምሪቱን ከተቀበለው ጋር መተባበር::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 1:1-6
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 1:1-7
ቀኑ እየመሸ ሲሄድ በተፈጥሮ የምናውቀው እንደሚጨልም ነው:: እግዚአብሔር ግን ሲመሽ ብርሀን ይሆናል ይላል:: እግዚአብሔር እኛ በጠበቅነው ሳይሆን እርሱ እንደወደደ የሚገለጥ ጊዜ ቦታና ሁኔታ የማይወስነው ከአዕምሮ በላይ በሆነ መንገድ ወደ እኛ ወደ ኑሮአችን ወደ ህይወታች የሚመጣ አምላክ ነው:: *** አለቀ: መጨረሻ ነው ሞቷል ተስፋ የለውም በምንለው ነገራችን ላይ በራሱ ጊዜና ሁኔታ የሚገለጥ እግዚአብሔር ሲመሽ ብርሀን ይሆናል ይላል::
የሰማነው የእግዚአብሔር ቃል እንዲሁም ያነበብነው እና የተረዳነው ሙሉ እውቀት የሚሆነው ከኢየሱስ ጋር ሲያገናኘንና ሲገለጥልን ነው:: የለበለዚየሰ እውቀት ብቻ ይሆናለ:: አነዳንድ መከራዎቻችን የምናልፍባቸው አስቸጋሪ ሁኔተዎች የእግዚአብሔር መታያ መንገዶች ናቸው:: በተለየ መንገድ እርሱን የምናይበት:: ለምስጋናና ለውዳስ የሚያደርጉን:: *** ጌታ ለእኛ በሚታይበት በዛ በምናልፍበት እርሱ ይጨከናል:: ስለዚህ የግድ በሆነበት በዚህ ሁኔታ እኛ ግን የሚያስችል እስክናየው የሚያፀና ፀጋውን ልንለምን ያስፈልጋል::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 1:1-11
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 1:8-17
እግዚአብሔር ታውቆ የማይጨረስ ዘለአለማዊ አምላክ ነው:: በመሆኑም እግዚአብሔርን አውቄ ጨርሻለሁ የሚል የለም:: በህይወት ዘመናችን እግዚአብሔርን ማወቅ የማይቆም የሚቀጥል ነው:: እግዚአብሔርን እያየን ወደ ደስታችን ከፍታ መድረሰ የምንችለው መንፈስ ቆዱስም በእኛ ውስጥ ክርስቶስን የሚገልጠው ነፍሳችንን በተውንበትና በጣልንበት መጠነ ነው Activity
በሆኑልን በተሳኩልንና በተከናወኑልን ድልም ባገኘንባቸው ነገሮች ሁሉ እውቅናና ምስጋና ሊቀበል የተገባው እርሱ እግዚአብሔር ነው:: እንደገናም ድል ባላገኘንባቸውና ባልተሳኩልንም በሁሉ ልናመሰግን ይገባል እግዚአብሔር ፃድቅ ታማኝ አምላክ ነውና:: *** ህይወታችን ከማንጎራጎር ነፃ ወጥቶ በሁሉ ማመስገንን የሚያስቀድም በሆነ ጊዜ በምሰጋና ውስጥ በዙፋኑ ላይ ዛሬም በክብር ያለውን ጌታ እናከብራለን:: ከዛም በሚመጣ በረከት ፈውስና መፅናናት እንሞላለን::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 2:1-7
እግዙአብሔር ሰዎች ሊረዱ በሚችሉበት ሁኔታ ረሱን በማዳን ይገልጣል:: ደግሞም የሰጠውን ተስፋ በእምነት ለሚጠብቁ ተሰፋን ለማፅናት በመባረክ ይገለጣል:: የመጀመሪያው በረከት አራሳችንን በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ሰናገኘው ነው:: ይሄን ጊዜ በእምነት አሸናፊዎች እንሆናለን:: *** ተስፋ ያደረግነው ደግሞም በእምነት የተከተልነው ጌታ በእኛ ሁኔታ ለብቻችን በተገለጠልን በታየልን ጊዜ አሰፈሪ ሁኔታው አያለ እኛ እንለወጣለን:: ድፍረት ሀይልና በረከት ይሆንልናል::
ከእግዚአብሔር ጋር ተስማምተን እንደ ፍቃዱ እንድንኖር ሁልጊዜም በሀጠአትና በከፉው ላይ አሸናፊዎች እንድንሆን የእርሱ ፈቃድ ነው:: የፀጋው ሀይልና ጉልበት ይህን ያደርጋል:: ዛሬን የመቆማችን የብርታታችን ምክንያት እርሱ ትናንት የረዳን ያገዘን ያቆመን በድል የመራን ጸጋውን ያበዛልን እርሱ ጌታ እግዚአብሔርነው:: *** ሁልጊዜ በጉዞ ላይ በውጊያ እንዳለን እያየን በንቃት ሆነን ለፈቃዱ እየታዘዝን በጽድቅና በእውነት ልንኖር ያስፈልጋል::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 2:4-7
በሆኑልን በተሳኩልንና በተከናወኑልን ድልም ባገኘንባቸው ነገሮች ሁሉ እውቅናና ምስጋና ሊቀበል የተገባው እርሱ እግዚአብሔር ነው:: እንደገናም ድል ባላገኘንባቸውና ባልተሳኩልንም በሁሉ ልናመሰግን ይገባል እግዚአብሔር ፃድቅ ታማኝ አምላክ ነውና:: *** ህይወታችን ከማንጎራጎር ነፃ ወጥቶ በሁሉ ማመስገንን የሚያስቀድም በሆነ ጊዜ በምሰጋና ውስጥ በዙፋኑ ላይ ዛሬም በክብር ያለውን ጌታ እናከብራለን:: ከዛም በሚመጣ በረከት ፈውስና መፅናናት እንሞላለን::
አማኝ ሊኖረው ከሚገባው መረዳት አንዱና ዋነኛው ነገር የተቀበለውን ፀጋ ነው:: ይህ ፀጋ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንድንሆን እንድንበቃን እንድናደርግ የተሰጠ ፀጋ ነው:: በመንፈሳዊ ህይወት ያለፀጋው ምንም የሆነ የለም ወደሚል በቃል በቻ ሳይሆን ነገር ግን ወደ ህይወት ምስክርነት መምጣት ከሀጢአት ከጠላት ክሰና ከፈተና ይጠበቃል:: *** ያለእውቀትና ያለመረዳት በምንሔድበትና በሚጓዝበት ጊዜም መንፈስ ቅዱስ የሚያደርገው ይህንኑ የተሰጠንን ፀጋ በእምነት አይን እንድናይናእንድንረዳ ማድረግ ነው::
እያለፍን ያለንበትን አስፈሪና አሰጨናቂ ሁኔታ እግዚአብሔር እንድንሻገረው ሲያደርግ ሲፈውሰንና ሲያፅናናን አላማው ከእኛ ባለፈ በእኛ ጉብኝት ሌሎችንም በምህረቱ በማዳኑና በማፅናናቱ ለመድረስ ነው:: *** በዚህ ምድር የመኖራችንን ምክንያት እንደሚገባ በተረዳን ጊዜ በመከራና በፈተና ሁሉ ውስጥ ፀንቶ ለመቆም ሀይልና ብርታት ተሰፋም ይሆንልናል:: የላቀው የመኖራችን ምክንያት ወንጌል ነው::
እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኘው ሰው እርሱ ኑሮው የተለወጠ መውጣት መግባቱም በልዩነት የሆነ ደግሞም ባገኘውና በያዘው ጌታ በመታመን የፀና ነው:: እግዚአብሔር ያገኛቸውን እነርሱን ፈቃዱንና ሀሳቡን ያገለግሉ ዘነድ በራሱ መንገድ ይመራቸዋል:: *** በእግዚአብሔር የተገኘ እርሱ ኑሮዬ ይበቃኛል ይላል:: ደግሞም ሌላው ይተርፋል::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 3:5-11
የተያዝንበትን የጌታን አጅና የፀጋውን ጉልበት ባልተረዳንበትና ባላስተዋልንበት ደግሞም አብልጠን ድካማችንንና የሚፈትነንን ድምፅ ብቻ በሰማንና አተልቀን ባየን ጊዜ ጠላት እኛን ለመጣል መንገድ ያገኛል:: ነገር ግን በእምነት ማየት ያለብን የያዘችንን ብርቱዋን የእግዚአብሔርን አጅ ደግሞም የፀጋውን ጉልበት ነው:: *** የአንድ አማኝ ዋስትናው ሰላምና ደህንነት መሆኑ አይደለም:: ነገር ግን የተያዘበት ፅኑ የእግዚአብሔር እጅ ይህንንም ደግሞ ማስተዋሉ ነው::
አማኝ እግዚአብሔር እንደሚያየው በመንፈሱ እርግጠኛ በሆነበትና መንፈስ ቅዱስም ይህንን መረዳት በሰጠው መጠን መጽናናት ሀይልና ብብታትም ይሆንለታል:: በሚያየውና በሚሰማው ደግሞም ከፉቱ ከሚየሰፈራራው አየደነግጥም :: የእግዚአብሔርን የፊቱን ብርሀን በማየት ሁኔታዎች እያሉ የተስፋ መታደስና የእምነት ሀይል ይሆናል *** ልባችንን ባቀናን እለት እለትም ፊቱን በፈለግን ቁጥር የፊቱ ብርሀን በእኛ ላይ ደግሞም በነገራችን ላይ ይበራል::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 4:1-16
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 5:1-9
የምንሰማውንና የምናየውን ነገር በእኛ ላይ እንደሚሆን እንደሚደርስብንም አድርገን ስንቆጥር እንፈራለን:: የእግዚአብሔር ቃል እመን እንጂ አትፍራ እንደሚል በፊታችን ያለው አሰፈሪ ነገር ደግሞም የማስፈራራቱ ድምፅ እያለ ነገር ግን አለመፍራት የምርጫ ወይም የችሎታ ጉዳይ አይደለም:: የፀጋ ጉዳይ ነው እንጂ:: እምነት በጨመርን ቁጥር የሚያስፈራውን ነገር ከላይ ወደ ታች መመልከት እንጀምራለን:: እምነት ፍርሀትን አይቀበልምና:: *** የእግዚአብሔር ድምፅ በየዘመናቱ ደግሞ ዛሬም ለሕዝቡ አትፍሩ የሚል ነው::
ተስፋ ቃል ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል አሁንስ ተስፋዬ ማነው? እግዚአብሔር አይደለምን እንደሚል : ተስፋ ራሱ እግዚአብሔር ነው:: አግዚአብሔር ከተሰጠን ተስፋ በላይ ነው:: ነገር ግን ወደ እኛ የሚመጣው እግዚአብሔር ለእኛ የሚሆንልን እንደሰጠን ተስፋ መጠን ልክ ነው:: *** መንፈሰ ቅዱስ በእኛ ውስጥ የመኖሩ አላማ ተሰፋችንን ለማስረገጥ ለማድመቅ ነው:: ተስፋ ደምቆ ባለበት በዛ መሄድ መሻገር አለ:: ሞትም ቢሆን በዛ መንገድ አለ:: ምክንያቱም ተስፋ የሰጠው የታመነ ነውና::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 5:9-16 ምዕራፍ 6:1-3
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ የጠራን ለድል ህይወት ነው:: ለአሸናፊነት ህይወት ነው:: ይህ የአሸናፊነት ህይወት ደግሞ እውን የሚሆነው በቃሉ እውነት በተመላለስንበት በፅድቅና ቅድሰና በኖርንበት ነው:: በአንደም ወይም በሌላ የተሸነፍንበት ነገር ቢኖር ያለንንም አሰማርከን ቢሆን ወደ እግዚአብሔር ወደ ፈቃዱ በመመለስ ቃል ኪዳናችንን በማደስ በዛ እንደገና ድል አለ የምርኮ መመለስም አለ::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 6:1-12
እግዚአብሔር የፈጠረውን ሁሉ ለራሱ ክብር ፈጥሮታል:: ሰውም የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ክብር ነው :: በእርሱ ክብር ውስጥ ሆኖ ለእግዚአብሔ የሚገባውንም ክብር እንዲያመጣ:: ከኃጢአት በሰተቀር ሰው የሚያደረገውን ሁሉ የሚያደርገው የእግዚአብሔርን ክብር ማዕከል በማድረግ ነው:: ኃጢአት ከሰው ህይወት የእግዚአብሔር ክብር እንዲጎግል ምክክያት ሆኗል:: ስለዚህ ሰው እንደቃሉ ሲኖን ደግሞም ስለ ኃጢአቱ ንስሀ ሲገባ ለእግዚአብሔር ክብርን ያመጣል:: *** እግዚአብሔር ለልጆቹ የሚያደርገው ሁሉ በክብር ነው:: የምናልፍበት ባይገባንም ያለ ጌታ ፈቃድ አንዳች በእኛ ላይ አይሆንምና ይህም ለእርሱ ክብር ነው::
ኢሱስ ክርስቶስን በማመን በዳግም ልደት የእግዚአብሔር ልጆች በሆንን ጊዜ የእርሱ መንፈስ በእኛ ውስጥ ይኖራልና መንፈሳውያን ሆነናል:: የእግዚአብሔር ልጆች በአለም ካሉት የሚለዩት በሚታየውና በሚሰማው ሁሉ በደስታም ሆነ በሀዘን ተፅዕኖ ውስጥ የማይወድቁ ነገር ግን ከነገሮች በስተጀርባ ያለውን የእግዚአብሔር ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ የሚረዱ በመሆናቸው ነው:: *** በነገሮች ላይ መንፈሳውያን በመሆናችን ከጠላት ማታለል ደግሞም ማስፈራራት እንጠበቃለን:: ከእኛም አልፎ ለሌሎች በረከትና መፅናናት ምክንያት እንሆናለን::
ፍፃሜያችንን ብዙ ጊዜ የሚወስነው ዛሬ የምንወስነውና የምንሰራው ነው:: እግዚአብሔር ማንንም በክፉ አይፈትንም ተበሎ እንደተፃፈ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብናልፍ እግዚአብሔር ፃድቅ አምላክ ነውና የመጀመሪያውን ጥያቄ መጠየቅ ያለብን ራሳችንን ነው:: በመከራ ጊዜም የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ደግሞም በተዕግስት መቆየት ለመፅናናት ብሎም ከችገር ለመጣት መንገዱ ነው:: *** እግዚአብሔር የመፅናናታችን እንጂ የመከራቸን ምክንያት አይደለም::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 7:1-13
በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የዘለዓለም ህይወት እንድናገኝ ከዘለዓለም በፊት በእግዚአብሔር የተወሰነ የመዳን መንገድ ነው:: የዳኑትም ደግሞ የልጁን መልክ እንዲመስሉ እነዲሁ በዘለዓለሙ ጌታ ከዘለዓለም በፊት የተወሰነ ነው:: የልጁን መልክ ወደ መምሰል የምንመጣው ሠራተኛ የሆነው ጌታ እግዚአብሔር በመንፈሱና በቃሉ እየቀረፀ ደግሞም በማንወዳቸው አንዳንድ ሁኔታዎች ውስጥ በማሳለፍ ነው:: *** የምናልፍበት ሁኔተ ሁሉ በእግዚአብሔር እውቀት ውስጥ ያለ ሲሆን ለእኛም ደግሞ የሚያበረታ የሚያቆምና የሚየፀናም የእርሱ ፀጋ አለ::
ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የእግዚአብሔር ልጆች የሆኑ ሁሉ በምድር ላይ ያለው ህይወታቸው አላማ ወንጌል ነው:: ያለተስፋ በጨለማ ላሉት ብንሃን በረከትና መፅናናት ለመሆን ነው:: የምናልፍባቸው ፈተናዎችና አንዳንድ አስጨናቂ ሁኔታዎች የሚያጠፉን ሳይሆኑ በእኛ ሁኔታ እግዚአብሔር ሊስራ ያለውን የዘላለም ፈቃዱን ሊገልጥበት ደግሞም እኛንም ወደ ላቀው የመኖራችን ምክንያት ወደ ሆነው ወደ ወንጌል እውነት ምሰክር ሊያመጣን ነው::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን -ምዕራፍ 7:11,12 ምዕራፍ 8:1-3
የፅድቅና የህይወት ጉዳይ ጌታ በመስቀል ላይ ራሱን የሰጠበት ጉዳይ ስለሆነ በዚህ መደራደር ወይንም ይህን ተክቶ በህይወታችን ስፍራን የሚይዝ ሊኖር ፈፅሞ አይገባም:: እግዚአብሔር በፀጋው የሚገልፀው ወይም የሚሰራው የእኛን ህይወት ሳይሆን የሚያሳየው የፀጋውን ነገር የእግዚአብሔርን ሉዐላዊነትና ምህረት ነው የሚያሳየው:: *** በዘመናችን ደግሞም በዙሪያችን ያለውን ክፋት አሰራሩንም እያሰተዋልን በፅድቅ ልንነቃ ከኃጢአትና በደልም ልንርቅ ጊዜው ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው::
አማኝ እግዚአብሔርን አንደ አምላክነቱ መጠን እያወቀው በሄደ ቁጥር እረፍት እየተሞላ ይሄዳል:: ታላቅነቱንና ሁሉን ቻይነቱን ታማኝነቱንና የማይለወጥ እንደ ቃሉ መሆኑን መረዳት: ከምናልፍበት አንዳንድ ሁኔታዎች ተፅእኖ ሥር እንዳንወድቅ ደግሞም በክፉው የማስፈራሪያ ወጥመድ ውስጥ እንዳንወድቅ ያደርጋል:: የእግዚአብሔር አይኖች በምድር ዙሪያ ሀሉ ያያሉ:: ስለዚህ የኛ ነገር ሁሉ በእርሱ ፊት ነው:: ይህን ማወቅ እግዚአብሔርን በአምላክነቱ ችሎት ማወቅና ማክበር ደግሞም በእርሱ መደገፍ ነው::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 8:4-7
እግዚአብሔር ለጥያቄዎቻችን መልስ የሚሰጠው በእኛ ጊዜ ደግሞም እኛ በምንጠብቀው መንገድ አይሆንም:: ሰለዚህ ብዙ ጊዜ ጌታ የዘገየ ደግሞም የተወን ይመስለናል:: ነገር ግን እግዚአብሐር ሁሉን ለክብሩ በሚሆን መንገድ ይመልሳል:: ባልተጠባበቅነውም ሁኔታ ራሱን ይገልጥበታል :: ሁሉን ቻይነቱን ማዳኑን ቸርነቱንና በጎነቱን::
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን - ምዕራፍ 8:7-14
እግዚአብሔር በባህርዩ ፃድቅ አምላክ ነው:: ይህም የትክክለኛነቱና የቅንነቱ መግለጫ ነው:: ይህ የተሰወረበት አማኝ ለራሱ የመሰለውን ይናገራል :: በእግዚአብሔርም ላይ የድፍረት ቃል አስከ ማውጣት ይደርሳል:: የእግዚአብሔር ፅድቅ የተገለጠለት እርሱ በመጀመሪያ ከራሱ ነገር ይወጣል ራሱንም በፊቱ ያዋርዳል:: መንፈሳዊ ጤንነታችን ያለው እግዚአብሔር ፃድቅ ነው ባልንበት ላይ ነው::
የአንድ አማኝ የመነፈሰዊ ህይወቱ ጥንካሬ እዚአብሔር ሁለን ቻይ ደግሞም ሁሉን የሚቆጣጠርና ከእርሱ የሚሰወር የሌለ መሆኑን በተረዳበትና በተገለጠለት መጠን ልክ ነው:: የምናልፍበት ሁኔታ አሰጨነቆን በጌታ ያልታየን ቢመሰለን እነኳ እግዚአብሔር ግን ማንንም አያሰጨንቅም ነገር ግን ከቁጥጥራችን ውጭ በወጣው በዛ እርሱ እኛን በግላጭ የሚያገኝበት ይሆንል:: *** ሁላችን ሁሉን በሚቆጣጠር በእግዚአብሔር አይኖች ፊት ነን:: በምንም ሁኔታ ውስጥ እንለፍ እርሱ እግዚአብሔር ለኛ በሆነልን ውሰጥ ያሳልፈናል::
መቆም ማለት በጌታ ተስፋ ቃል ላይ እንዲሁም በእኛ ሁኔታ በተገለጠልንና በተናገረን ላይ ተመስርተን በእምነት የተዋሀደን ያ የቆምንበት ነው:: ቆምን ማለት ቃሉ በእምነት ተዋህዶን የሆንበተ ማንነት ነው:: ደስ የምንሰኝበት የሚሰማንና የምንነካባቸው ሁሉ የቆምንባቸው አይደሉም:: መንፈሳዊ ነገር ሰሜት ላይ ብቻ የሚቀር ሳይሆን ከዚህ ያለፈ ወደ መሇን የሚደርስ ነው:: *** እግዚአብሔር የሚፈልገው ውጫቸውን በውስጣቸው በቆመ ማንነታቸው ያሸነፉ የገዙ ሰዎች ማውጣት ነው:: እነዚህ ናቸው ሁሉን ፈፅመው በሰው ልጅ ፊት ለመገለጥ የሚበቁት::
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሚያምኑ ሁሉ የዘላለምን ህይወት ብቻ ሳይሆን በምድርም ሳለን በኃጢአት በሰጋና በአለም ላይ በድል አድራጊነት እንዲመላለሱ ሰጥቷል:: የእግዚአብሔር ቃል የሰው ህይወት በምድር ላይ ብርቱ ሰልፍ ነው ይላል:: ነገር ግን በክርሰቶስ ኢየሱስ ላሉት ሰጋን ከክፉ ምኞቱና መሻቱ ጋር የሰቀሉ እነርሱ በአሸናፊነት ይመላለሳሉ:: *** አማኝ ህይወቱ በድል አድራጊነት እየበረታ እነዲሄድ ህይወቱን እንደ እግዚአብሔር ቃል ሊመራ ደግሞም በፍቅር ሆኖ ሊመላለስ ይገባዋል::
ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ሲገጥሙን እንዴት ምላሽ እንጣለን
የተባረከው ተስፋችን በደጅ ነው...ተዘጋጅተናል?
የተባረከው ተስፋችን በደጅ ነው...ተዘጋጅተናል?
የተባረከው ተስፋችን በደጅ ነው...ተዘጋጅተናል?
የተባረከው ተስፋችን በደጅ ነው...ተዘጋጅተናል?
የአማኝ ትልቁ ዋስትና የሚያመልከው እርሱ እግዚአብሔር የሚሰማ አምላክ ነው:: የሚለው ነው:: በእኛ ሁኔታ ደግሞም በነገሮች የማይወሰነው ጌታ የሚሰማው ሁልጊዜ ነው:: መልሱ ግን በራሱ ጊዜና በወደደው መንገድ ነው:: ትልቅነቱን ታማኝነቱን ደግሞም እንደ ቃሉ መሆኑን በማስረገጥ ይመልሳል:: *** የምናልፍበት ነገርና ሁኔታ እንዳልተሰማን አስመስሎ ጨለማውን ቢያሳየንም ጌታ ግን በክብር ይመጣል ብርሃንም ይሆናል::
አግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ከራሱ ጋር አሰታርቆናል:: ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋው መቆረስ የጥሉን ግድግዳ ስላፈረሰ እዳችንም ሰለተከፈለ ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም አድርገናል:: ይህም የህይወት ሰላም በእኛ ዘንድ የሚጠበቀው በክርስቶስ ውስጥ በመሆን ነው:: *** ሰላም ህይወት ነው ሰላም ኑሮም ነው:: በክርስቶስ ውስጥ እስከሆን ደግሞም የምናከናውነውን ሁሉ በጌታ ፍቅር ወስጥ ሆነን እስካደረግን ድረስ:: በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ ጌታ ሰላማችን ነው::
አማኝ በመንፈሳዊ ህይወቱ በጎ ከመኘት ከማሰብና ከመፈለግ አልፎ ወደ መሆንና ወደ ማድረግ መንፈሳዊ ደረጃ የሚመጣው ለዛ ያልበቃውን ማንነቱን በብርሀን ውስጥ እያገኘ በእግዚአብሔር ፀጋ ዋጋ መክፈል ያለበትን አየከፈለና መውጣት ካለበትም እየወጣ ሲሸጋገር ነው:: *** በብርሀን ውስጥ ያልበቃውን ማንነታችንን ባገኘን ጊዜ የሚረዳንን ፀጋ ተቀብለን ካለንበት ለመውጣት ፈቅደን ራሳችንን ልናዋርድ የተገባ ነው::
እግዚአብሔር የሚለውን ተረጋግቶ መስማት ለመፅናናታችንና ለፈውሳችን ደግሞም ከክፉ አደጋና ፈተና ለመዳናችን ምክንያት ይሆንልናል:: ዛረ የምንሰማው ነጋችንን ብሩህ ያደርጋል:: ደግሞም በመከራ ውስጥ አፅንቶ ያቆመናል:: *** በህይወት ዘመናችን አለኝ ብለን የምንኮራበት የምንመካበትና የምንተማመንበት ነገር ቢኖር እርሱ እግዚአብሔር የተናገረን እኛም የሰማነው ነው::
አማኝ በዚህ ምድር ሲኖር የልጁን የኢየሱስ ክርስቶስን መልክ እንዲመስል የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው:: ይኸውም በፅድቅና በእውነት ሊመላለስ በጨለማው አለም ብርሃን ጣዕም ለሆነው ለሌለው አለም ጨው ሆኖ መገለጡ ነው:: የልጁን መልክ መምሰላችን መገለጫው በጊዜውም አለጊዜውም በእኛ ህይወት የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ባህርያት መንፀባረቁ ነው::
በደረሰብንና በምናልፍበት ችግርና ፈተና ውስጥ ሳናማርር ወይንም መራራ ሳንሆን በፀሎት ራሳችንን በማዋረድ የጌታን ፊት ልንፈልግ ደግሞም የጠፋብንን ያጣነውን ብቻ ሳይሆን ከጌታ የተቀበልነውን ብዙዉን ልናይ ምስጋናና እምነት ሊሆንልን የተገባ ነው:: *** ጠላት ችግራችንን አግዝፎ እንድንማረር ያደርጋል:: እግዚአብሔር ግን በችግራችን ላይ ምህረቱንና ቸርነቱን ይገልጣል:: ሁኔታዎቻችንንም ይለውጣል::
የአንድ መንፈሳዊ ሰው ጥንካሬ ወደፊት ሄዶ የእግዚአብሔርን ፀጋ መቀበሉ ብቻ ሳይሆን ነገር ግን የተቀበለውን መጠበቁ በተቀበለውም መገኘቱና መቆሙ ነው:: የተቀበለውን ፀጋ ለማሰጠበቅ ደግሞ ዋጋ ማስከፈሉ ግድ ነው:: በህይወታችን ምንም ያህል እናድርግ ምንም ያህል ፀጋ በህይወታችን ይገለጥ ህይወታችንን የመጠበቅ አቅማችን ያለው ራሳችንን ለእግዚአብሔር የሰጠነውን ያህል ነው:: ሰለዚህ ዕለት ዕለት ህይወታችንን እየመረመርን ለእግዚአብሔር ያልተሰጠውን ማንነታችንን ልናስገዛ ልንቀድስ ያስፈልጋል::
አማኝ ሊደርስ ወደሚፈልገው መድረስ ሊያገኝ የሚፈልገውን የሚያገኘው መሆን የሚፈልገውንም መሆን የሚችለው ከፊት ለፊቱ ያለውን ቅጥር በማለፍ ነው:: ያለበለዚያ ምኞት ብቻ የሆናል:: ፍርሀት ይሉኝታ የቅር አለማለት ዝናና ከብር ሌሎችም እነዚህን የሚመስሉ ሁሉ ከፊታችን የሚቆሙ ቅጥሮ ናቸው:: *** በመንፈሳዊ ህይወታችን ባለጠጎች ልንሆን ደግሞም በድል አድራጊነት መጓዝ የምንችለው ከፊታችን ያለውን ቅጥር አልፈን ስንሄድ ነው::
አማኝ በዚህ ምድር የሚኖረው ራሱን ላሰገዛለት ለጌታ ነው:: ለእግዚአብሔር መንግስት የመኖራችንም ፍሬ ከራሳችን ወጥተን ለሌላ ስንሆን ነው:: ለሌላው ለመሆንና የመንፈስን ፍሬ ለማፍራት ደግሞ ዋናውና ቀዳሚው የራስ ሸክም የሆነውን በጌታ ላይ መጣልና ከጭንቀት ከፍርሀት ነፃ መሆን ነው:: *** ለሌሎች መሆን አንዱ በእግዚአብሔር ፀጋ ታግዘን ዋጋ የምንከፍልበተና ጌታን የምናሳይበት ከራሳችንም ወጥተን ለተፈጠርንበት የእግዚአብሔር አላማ የምንኖርበትነው::
አማኝ በጌታ የሚኖረው የሚመላለሰውም የእምነቱን መጠን ያህል ነው:: መቆማችን በፈተናም ሁሉ ፀንተን መቆማችን ያመነውን ያህል ነው::ሰለዚህ አንዳንድ ጊዜ ከእምነታችን መጠን ያለፈ ችግር ሲደርስብን እግዚአብሐር የተወን እሰኪመስለን ድረስ እንጨነቃለን:: ጌታ ግን በፀጋው ይረዳንና በእምነታችን እንድናድግ ያደርጋል:: የህይወታችን አሸናፊነትና ድል እግዚአብሔርን በእምነት በመኖር የሚሆኑ ናቸው::
ጠላት ብዙዉን ጊዜ ሊያጠምደን የሚሞክረው እውነት ባልሆነ ነገር ግን እውነት በሚመስል ነገር ነው:: ስለዚህ ነው በነገሮች ላይ ወስነን አንድ እርምጃ ከመራመዳችን በፊት ልንመረመር ደግሞም የእግዚአብሔርን ፈቃድ መጠየቅ ያለብን:: *** ጠላት ይሸነግላል አማኝ ግን የሚመራው በእግዚአብሔር መንፈስ ሰለሆነ አስቀድሞ የመነፈስ ቅዱስን ድምፅ በመስማት ነገሮችን ይመረምራል::
እምነት ጉዞ ነው:: ከእግዚአብሔር ጋር ተስማምተን የምንጓዘው የህይወት ጉዞ:: ከማየት ከመዳሰስ ወጥተን እንደሰማን እንደበራልን ጌታ እንዳለን ብቻ ማድረግ እርሱ አንዳለ መሆን መብቃተ ነው:: *** እምነት የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው:: ነገር ግን ደግሞ በእውቀት የምንወስደው እርምጃ መኖር አለበት::
የአማኝ የሰላሙ መጀመሪያ የእግዚአብሔር ን ታላቅነት ባየው ነው;: ያደከመን እረፍት ያሳጣን ነገር ሁሉ ከእርሱ ታላቀነት በታች ነው:: ነጋችንን የሚያውቅ ጌታ እንድንታመንበት ይፈልጋል:: ችግሩ እያለ ማስፈራራቱም እያለ ሰላማችን ግን የበዘ ይሆናል:: ማረፍ ማለት ነገርን ሁሉ ለጌታ መተው ነው::ደግሞም ጌታ አለኝ እርሱ አለኝ ብሎ በእርሱ መደገፍ ነው: በቃሉ መታመን ነው::በዚህች በምትናወጥ አለም ፈውሰ መፅናናት ሰላምና እረፍት በእርሱ ነው::
በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከእግዚአብሔር ጋር ላልታረቀ የዘለአለሙን ብቻ ሳይሆን በዚህም ምድር እውነተኛ ነፃነት ሰላምና እረፍት አይሆንለትም:: እውነተኛ ነፃነት ሰላምና እረፍት የሚሰጥ እርሱ ወንጌልና ወንጌል ብቻ ነው:: *** ወንጌል ለሰው ሁሉ ነው:: ይህም ወንጌል ሊመጣ ያለው ተስፋችን የሆነ ክርሰቶስ ነው:: በዚህ ምድር የመኖራችን የላቀው አላማ ይህን የመዳን ወንጌል ላልሰሙት ማሰማት ማወጅ ነው::
እግዚአብሔር ምህረትን በህይወታችን ከሚገልጥባቸው ሁኔታዎች አንዱ ከወደቅንበት እንድንነሳ ከሳትንበትም እንድንመለስ ሁለተኛ እድል በመስጠት ነው:: ይህን ምህረቱን የሚገልፀው ደግሞ በመንገዳችን ለሀዘናችን መፅናናት ከወደቅንበትም ለመነሳት ምክንያት የሚሆኑ ሰዎችን በመስጠት ነው:: *** ምን እንኳ የምናልፍበት ሁኔታ ብዙ ፈተና ብዙ ምሬት ያለበት ቢሆንም እኛ ለመመለስ በፈቀድን ጊዜ እግዚአብሔር ይመራል እደገና እድል ይሰጣል::
ሁለንተናውን ለእግዚአብሔር የሰጠ ያስግዛ እርሱ እግዚአብሔር አለኝ እርሱ የእኔ ነው ለማለት አይቸገርም:: እግዚአብሔርም ለራሱ መንገድ የሚያደርገው ለሌሎችም እንዲተርፍ ለበጎ ነገር የሚያዘጋጀው እንደዙህ አይነቱን ሰው ነው:: እግዚአብሔር በህይወታችን የሚያልፈው በቃሉ አማካኝነት ነው:: ሰለዚህ ቃሉ ካለን እግዚአብሔር ይገለጥናል:: ከፊታችንም ያለውን ነገራችንን አቅልሎ ያሳየናል ሀይልና ጉልበትም ይሆንልናል::
ሰው እግዚአብሔርን አሰቀድሞ አይቶ ራሱን ሲያይ ትክክለኛ ማንነቱን ደግሞም በትክክል ያለበትን ሁኔታ ያያል:: የልቡናው አይኖች ያልበሩለት አርሱ ወዴት እንደሚሄድ ምን እንደሚያደረግም አያውቅም:: በፊቱ ያለውን ብቻ በስጋ አይኖቹ ያያልና:: ስለዚህ እግዚአብሔርን ማየት የምንችልበት የልቡና አይኖቻችን ሊበሩልን ያስፈልጋል:: *** የልቡና አይኖቻችን ሲበሩልን ከምሬትና ተስፋ ከመቁረጥ ደግሞም ከክፉዉ ወጥመድ እናመልጣለን:: ከፊታችን ያለው መንገድ የቀና ይሆናል:: በምስጋናም እንሆናለን::
ሰው በእግዚአብሔር ትአዛዝ ውስጥ ሲሆን ደግሞም በፈቃዱ በሆነበት በዛ እግዚአብሔርን ካወቀበት በላይ የሚያውቅበት እግዚአብሔርም ራሱን የሚገልጥበት ነው:: እየታዘዝን በፈቃዱ ስንኖር እግዚአብሔር በዙሪያችን ያለውን ስለእኛ ያዝዛል:: ብርሃንን በጨለማው ላይ ያወጣል:: የማይቻለውን እንድንችል አይሆንም የተባለው እንዲሆን ያዝዛል:: *** አማኝ የሚኖረው በበቃበት ነገር ሳይሆን በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ነው:: እግዚአብሔር ለአሁን ደግሞም ወደፊት ለዘመኑ ሰለእርሱ ያዛል::
እግዚአብሔር ብርሃን ነው:: ይህን ብርሃን የምንካፈለው የእግዚአብሔርም ፊት የሚበራልን እኛም በቤቱ ፍርሀትና ትህትና የሚኖረን ደግሞ በቃሉ ነው:: ሰለዚህም ሰው ለእግዚአብሔር የሚሆነው ቃሉ የበራለትን ያህል ነው:: *** ቃሉ ሲገለጥ በረከትና ህይወት እንደሚገለጥ እንዲሁ ቅድስናም ይገለጣልና ቃሉ እንዲጠቅመን በብርሃኑ ውስጥ ራሳችንን ልናይ ያሰፈልጋል::
ሁኔታ ላደከመውና ላዘነው ደግሞም ነገሬ ሞቷል ብሎ ተስፋ ለቆረጠ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሁልጊዜም ተስፋ አለ:: ተስፋን የሰጠውም ጌታ እርሱ የታመነነው:: ወላጆች በልጆቻቸው እውነተኛ ተጠቃሚ የሚሆኑት በአለም ከሚደርሱበት ስኬት ይልቅ በጌታ ሲያገኟቸው ነው:: *** ከሁሉ አስቀድሞ ግን እኛ ራሳችን የራቅን ልንቀርብ ለፈቃዱም የተገዛን ልንሆን ልንመለስ ለጌታም የተገኘን ልንሆን ያስፈልጋል:: ለዚህም የሚረዳ ደግሞም የታመነ ፀጋ አለ::
በእግዚአብሔር ቃል የተሞላ በተስፋውም ያለ ሰው እርሱ አዕምሮው የተለወጠ የራሱን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ትክክል የሆነ ነው:: የተሞላነው የአግዚአብሔር ቃል አዕምሮአችንን ያድሳል ቋንቋችንንም ይቀይራል:: በጎውንም እንናገራለን መሪያችንም አርሱ ቃሉ ይሆናል:: *** አዕምሮው በቃሉ ለተሞላ ለእርሱ በዚህ አስጨናቂው አለም ዕረፍት ይሆናል ሰላምና ተስፋም ይሆናል:: ራሱንና የራሱ የሆነውን ሁሉ ለጌታ አሳልፎ ይሰጣል ደግሞም ለሌሎችም ይተርፋል::
ለአማኝ የተቀደሰው ሰፍራ የሰላም ወንጌል ነው:: በዚህ ሰፍራ መቆሙን ማስተዋልና ሊያደርግ የሚገባውን ሊያደርግ የተገባ ነው:: ይኸውም የመጀመሪያው የራስን ሸክም መጣልና የእግዚአብሔርን ሸክም መሸከም ነው:: የእግዚአብሔር ሸክም ደግሞ ሰላም የሞላበት ተስፋና መፅናናት ያለበት ነው:: የሰው ታሪክ በመለኮት ከሚተረጎምበት ቀን ጋር እስኪገናኝ ሰው በፀሎት ስፍራው ለም በዚህ አልፋለሁ ለምን ይሁ የሆንብኛል እያለ ያለቅሳል:: ለቅሶው የሚቆመው የሸክም ለውጥ የታሪክ ለውጥ ሲሆን ነው:: የእኛ ሸክም የእግዚአብሔር ሸከም ሲሆን የመለኮተ ትርጉ ሲመጣ:: *** ትክክለኛው የህይወታችን ታሪክ የሚተረጎመው ሁሉን በሚቆጣጠር በመለኮት ነው::
እስራኤል ለእግዚአብሔር በመገዛት በመታዘዝም በሄደበት በመንገዱ ሁሉ በጠላቶቹ ላይ ድል እያደረገ ተጉዟል:: ጌልጌላ አንዱ ከእግዚአብሔር ጋር ለመስማማታቸው ምልክት የሆነ ሁልጊዜም የሚያስታውሱት ሰፍራ ነው:: ዛሬደግሞ የክርስቲያን በህይወቱ የድል ብስራት የታወጀበት ቀራኒዮ ነው:: ሁልጊዜ የሚተወስ ሀይል የሚታደስበት ደግሞም ጌታንና የድሉን አዋጅ ሁልጊዜ የምንሰማበት::
በሰው ህይወት በዙ ውጣ ውረድ ደግሞም ብዙ መውደቅ መነሳት አለበት:: በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ሰው ይመለስ ዘንድ ነው: ለዚህም እንደገና እድል ይሰጣል:: *** ከመመለስ ጋር የእግዚአብሔርን ሞገስ ደግሞም በረከቱን እናያለን:: የእግዚአብሔርን አብሮነትም እለት እለት በኑሮአችን እናያለን::
በዚህ ምድር ስንኖር በቁጥር በተወሰነች ዘመናችን የመኖራችንና የሰላማችን ዋሰትና እግዚአብሐር ነው:: እረፉ እኔም አምላክ እንደሆንኩ እወቁ እንዳለ:: የእግዚአብሔር ቃል የአግዚአብሔርን ፈቃድ ሀሳቡንም የገልጣል:: በተገለጠልን የቃሉ ብርሃን ልንገኝ ሁልጊዜም በብርሃኑ ፊት ልንሆን ያስፈልጋል:: *** በሚያስፈራ ደግሞም በሚያስጨንቅ ሁኔታ ውስጥ ብናልፍ እንኳ በዚህም ውስጥ ሰላምና ተስፋ ሀይልና ብርታት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው::
ለሰው ሁሉ የጥያቄ መልስ የሚሆነው ከእግዚአብሔር ዘንድ ለሰው የተሰጠ ጨለማውንም የገለጠ እርሱ ወንጌል ነው:: ወነጌል ሁሉ ሊቀበሉት የሚገባ አስደናቂው የእግዚአብሔር መህረት የተገለጠበት ነው:: ወንጌል የእውነት ሁሉ ሚዛን ነው:: እርሱም ክርስቶስ ኢየሱስ ነው:: *** አማኝ በዘመኑ ሁሉ ሊኖረው የሚገባ የማይለወጥ ትልቁ አጀንዳ የተቀበለውን ይህን የወንጌል እውነት ለሌሎች በቃልና በኑሮ ማወጅና ማሳየት ነው::
ክርስቲያን የላይኛውን ዙፋን የእግዚአብሔርን ክብር በዚህ ምድር ለሠወከል በመጀመሪያ በላይ ያለው ክብር ሊበራለት ይገባል:: ያለበለዚያ የሚሰማውና የሚያየው ሁሉ የሚያሰፈራውና የሚያስደነገጠው ይሆናል:: ሰውን በዚህ ምድር ሊያስፈራውና ሊየሰጨንቀውና ሊያውከው የሚችለው ትልቁ ሞት ነው:: አኛ ደግሞ የተረዳነው በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን ጌታ ነው:: *** ቤተክርስቲያን ይህን ትልቁን ስልጣን እየተለማመደች ስትመጣ ለማንኛውም አንበርካኪ ጉልበተኛ የማትገዛ ትሆናለች::
እግዚአብሔር ሰውን በፊቱ እንዲሆን በንፅህና እንዲያመልከውና እንዲያገለግለው የመረጠው አለም ከመፈጠሩ አሰቀድሞ ነበር:: ይሁንጂ በአለመታዘዝ ምክነያት ሰው ከእግዚአብሔር ፊት ወጣ:: በተገለጠው የእግዚአብሔር ፍቅር በልጁ በኢየሱስ ከርስቶስ በሞቱና በትንሣኤው ወደ ወጣበት ወደ እግዚአብሐር ክብር ወደ ፊቱ ተመልሷል:: ሰለዚህ አማኝ በእግዚአብሔር ፊት ፀንቶ የሚቆመው በመንፈስ ቀዱሰ ቁጥጥር ስር የሆነውን ወፅድቁና በፀጋው የተሞላውን ያህል ነው:: በፊቱ መሆን በፀጋው ነው:: በፊቱ መፅናት ግን ዋጋ በመክፈል ነው ለአለም ለኃጢአት ለሰጋ እምቢ በማለት:: በመሞትነው::
የእግዚአብሔርን ኤልሻዳይነት መመስከር መናገር የምንችለው አይናችን ተከፍቶ እርሱን ያየነውን ያህል ነው:: የልብን አይን የሚከፍት እርሱ ራሱ እግዚአብሔር ነው:: በስጋ አይን የምናየው የምንጠይቀውም ምድራዊ የሆኑ ለጊዜው የሆኑ ደግሞም የሚያልቁና የሚጠፉ ናቸው:: የልብ አይን ሲከፈት ግን ለአሁኑ ደግሞም ለወደፊት ለዘለአለም የሆነውን ሁሉ ነው:: እርምጃችንም በመሰለኝና በተሰማኝ ሳይሆን ተረድተንና አይተን እንራመዳለን:: *** የመጨረሻው ዘመን ትልቁ ችግር በጸሎት ያለመፅናት ነው:: በመቆየት በፀሎት ፀንቶ በመቆም የእግዚአብሔር ጉብኝት ይመጣል:: ማየት ይሆናል:: ወዳዘጋጀውም ህይወትና በረከት መግባት ይሆናል::
አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ አማኝ በየእለት ጉዳይ በሚያየውና በሚሰማው አይያዝም ደግሞም አይጨነቅም:: ምክንያቱም ልቡ የተያዘው በዘላለሙ ነገር ለላይ ሰለሆነ:: ከእግዚአብሔር ጋር ስንራመድ አካሄዳችን እርሱን ደስ የሚያሰኝ እንዲሆን የሚረዳንን ፀጋና የመንፈሱንም ማፅናናት የምንቀበለው የለይኛውን ትልቁን አይታ እንዳየን መጠን ነው: *** እለት እለት በፈታችን ከሚቀመጡት እንቅፋቶች ባሻገር ዘላለማዊውን በማየት ከምሬትና ከሀዘን ደግሞም ተስፋ ከመቁረጥ እንጠበቃለን:: የምስጋና ሰዎችም ያደርገናል::
አባትነት የጀመረው የሁሉ አባ ከሆነው ከእግዚአብሔር ነው:: አባት ተብሎ ሲጠራም ቸርነቱን ለጋስነቱን ተንከባካቢነቱንና ደራሽነቱን ይገልፃል:: ሰውም አባት ሲሆን ይህን በእግዚአብሔር ዘንድ ያለው የአባትነት ባህርይ በጥቂቱም ቢሆን እንዲገለጥበት ነው:: አባት ለቤቱ መሪ ራስ ልጆቹም ደግሞ አባት ነው:: ስለዚህ የአንድ ቤት የመንፈሳዊነት ጣሪያው አባት ቤቱን ይዞ በእግዚአብሔርፊት በጸሎት በአምልኮ የመገኘቱን ያህል ነው:: እንዲሁም የቤቱ ሰላም ደግሞ የሚጠበቀው በነገሮች ሁሉ አባት ከሚኖረው የልብ ስፋት መጠንና ራሱነም ለመለወጥ ዝግጁና ፈቃደኛ የሆነው ያህል ነው:: *** በዚህ ትምህርት የአባትን በቤቱ ላይ ያለውን ድርሻና ከልጆቹም ጋር ሊኖረው የሚገባውን ግንኙነት በጥልቀት እንማራለን::
የእግዚአብሔር ሰዎች መውጣትና መግባታቸው የሚሰሩትና የሚናገሩትም በእግዚአብሔር ፈቃድ ቁጥጥር ውስጥ ራሳቸውን አሰገዝተው ሊሆን የተገባ ነው:: ሰሜትና ሁኔታ የሌሎችም ሰዎች ፈቃድ አይገዛቸውም:: ከፈቃዱ ቁጥጥር በወጣን ጊዜ የሚገዛን የስጋ የአለምና የኃጢአት ሀሳብ ነው:: በዛ ደግሞ ብዙ ኪሳራ ፍርሀትና ድንጋጤ ተሰፋ መቁረጥ ይሆናል:: *** የእግዚአብሔር ቃል የእግዚአብሔርን ፈቃድ ይገልጣል:: ሰለዚህ ለቃሉ የተከፈተ ልብ ሊኖረን ይገባል:: ለዚህም ደግሞ የሚረዳ ፀጋ አለ::
ጸሎት ከሚታየውና ከተሰማው ከምንናወጥበት ችግር አልፎ እግዚአብሔር ምን ይላል ብሎ መጠየቅና ማየት ከመትረዳውም የጌታ እጅ ጋር መገናኘት ነው:: በዙሪያው ካለው ድምፅና ጭንቀት ነፃ የወጣ እርሱ ከአርያም ያለውን ድምፅ ይሰማል:: ነገሮች ሳይለወጡም የእርሱ ህይወት በመንፈስ ቅዱስ ይለወጣል:: **** በዚህ የጸሎት ትምህርት በአንድ አማኝ መንፈሳዊ ህይወት ውስጥ የህይወትና የሸክም ጸሎት ምን እንደሚመስሉ በጥልቀት አናያለን::
ፀሎት አንዱ እግዚአብሔርን የምንማርበት ህይወት ነው:: በቃሉ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን መህረትና ቸርነት ደገሞም የማዳኑን ሀይልና ታማኝነቱን በፀሎታችንውስጥ እንማራለን:: የእምነት ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር የሚያነካካን ነው:: በእምነት ወደ እግዚአብሔር ፊት የቀረበ ሰው ከፀሎቱ በኃላ በቀደመው ማንነትና ስሜት አይሆንም:: በመፅናናትና በተሰፋ በተሞላ በሌላ ማንነት በአሜን ይነሳል:: *** ነገሮችን ሁሉ በራሳችን ከማየት ወጥተን በእግዚአብሔር አይን ስናይ ፀሎታችንም በፊቱ እነደ እርሱ ፈቃድ ይመለስልናል:: እኛም ከድንጋጤና ፍርሃት ይልቅ በምሰጋናና በተሰፋ እንሆናለን::
እስራኤል በመንገዱ ሁሉ በጠላቶቹ ፊት የማሸነፉና የመሸነፉ ጉዳይ የሚያያዘው ለእግዚአብሔር ከመታዘዙና አለመታዘዙ ጋር ነው:: ምንም እንኳ ጠላቶቻቸው አሰፈሪዎች መስለው ቢታዩም እግዚአብሔር ግን እየመጣ አትፍሩ እኔ ከእናንተ ጋር ነኘ ይላቸዋል:: ደግሞም በድል ያስኬዳቸዋል:: እግዚአብሔር ዛሬም በቃሉ የታመነ ነው:: በየእለቱ ከሚከበን የስጋ የአለምና የሰይጣነ ፈተና ከውጊያው በአሸናፊነት አልፈን በእረፍትና በሰላም እንድንሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው::
የአማኝ መንፈሳዊ ሕይወት ከሚሰፋባቸው መንገዶች አንዱ ፀሎት ነው::ፀሎትም በእግዚአብሔር ቃል ነው:: የእግዚአብሔር ቃል ደግሞ የእግዚአብሔርን ሀሳብ ፈቃዱንም ይገልፃል:: የእግዚአብሔር ቃል እነደሚያሳየንና ሸክም አድርጎ እንደሚሰጠን የማንፀልይ ከሆነ በዙሪያችን ካለው ከምንሰማውና ከምናየው ተነስተን ብቻ እነጨነቃለን:: ችግሮች የሚመሩን እንሆናለን:: በፀሎት ሕይወት እያደግን ስንሄድ በእግዚአብሔር በሆነው ፅድቅ ደግሞም እኛም መሆን ባለብን ግድ ወደሚለን ደረጃ እንመጣለን::
ሰው ሁሉ የየራሱ የሆነ ምርጫ አለው:: ነገር ግን እግዚአብሔር ልጆቹን እርሱ በፈቀደው መንገድ ይመራል:: ስለዚህ የልባችንን ፈቃድ ትተን በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ልንገባ ያስፈልጋል:: የማይመች እንዲሁም ትንሽና የተናቀ መስሎ ቢታየንም እንኳ በዛ ውስጥ የእግዚአብሔር ታላቅ ፈቃዱና ሀሳቡ እንዲፈፀም የስራው መጀመሪያ ነው:: ትንሽ ነው የተዋረደ ነው ባልንበት በዛ የእግዚአብሔር ታላቅነትና ከፍታ ይታያል:: ለእኛም መባረክና ወደ ከፍታ መውጣት ይሆናል::
የሚፀልይ ሰው ረጅሙን የእግዚአብሔርን ሀሳብና ሊሰራያለውን ዕቅዱን ያያል ደግሞም ይሰማል:: ባየውና በሰማውም በትጋት ይፀልያል:: እግዚአብሔር ሸክምን ወደ ሰው ሲያመጣ ያን ሸክም የራሱ አደድርጎ አንዲማልድ እንዲፀልይ ነው:: የሚፀልየውም በአዕመሮው እየተጨነቀ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ እየተረዳ ደሰ እየተሰኘ ይፀልያል:: *** ህይወት በዚህ ምድር በብዙ መከራና ፍርሀት የተሞላ ነው:: ነገር ግን ሰላምና እረፍት ወደ ህይወታችን የሚመጣው በፀሎት ሰንሆን ነው:: በእግዚአብሔር ፊት በፀሎት በቆየን ቁጥር ህይወት እየተሰራ ይሔዳልና::
የእግዚአብሔር ቃል ለአማኝ የህይወቱ መርህ ነው:: እለት እለት ለዚህ የህይወቱ መርህ ለሆነው ለእግዚአብሔር ቃል የሚታዘዝ ደግሞም ህይወቱ ያደረገ አማኝ እርሱ ጥልቅ በሆነ መሠረት ላይ ተመስርቷል:: ተስፋውም የፀና ነውው:: *** የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተን መታዘዝ በሆነልን ጊዜ በማንኛውም በሚያናውጥ ነገርና ሁኔታ ፀንተን እንድንቆም ዋነኛ ምክንያት እርሱ ነው::
ዛሬ አለም አጥብቃ የምትፈልገው ሰው ሁሉ የሚሻው አንድ ነገር ሰላም ነው:: እውነተኛው ሰላም ግን ከሰላም አምላክ ከእግዚአብሔር ነው:: ሰለዚህ በእየለቱ ራሳችንን ልንጠይቅ የሚገባው ጥያቄ አንዱ በአንደበታችን ከምንናገረው በላይ በህይወታችን በነፈስ በመንፈሳችን የጌታ ሰላምና እረፍት አለ ወይ? ብለን ነው:: *** አማኝ እይታው ከዚህ ምድር አልፎ እግዚአብሔር ለልጆቹ ያዘጋጀውን ዘላለማዊ እርስት የጌታንም ዳግም መምጣት ሲያይ ሰላሙና እረፍቱ የበዛ ተስፋውም የፀና ይሆናል::
የእግዚአብሔር ፈቃድ የተገለጠላቸው ሰዎች ትጉዎች ናቸው::በጸሎት በስራና በህይወት ትጉህ ይሆናሉ:: የተገለጠው የጌተ ፈቃድ ትጋትን ይጨምርላቸዋልና:: አማኝ በህይወቱ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማወቅ እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ ነው:: መንፈሳዊ ህይወቱ ትርጉም ያለው ይሆናል:: የእግዚአብሔር ፈቃድ ሲበራልን የምናልፍባቸውን ችግሮች የምናየው በተለየ እይታ ነው:: ልንደርስበት ወዳለው የጌታ ፈቃድ ለመድረስ የምናልፍባቸው አንደሆኑ እናያለን:: ሰለዚህ መንፈስ ቅዱስ በሚሰጠን ፀጋ በጸሎት የምንተጋ እንሆናለን::
የአማኝ ሰላምና እረፍት መፅናናትና ደስታ ከውጭ ፈልጎ የሚያገኘው አይደለም:: ነገር ግን በእምነት ከተቀበለው ከጌታ ኢየሱስ በውስጡም ካደረው ከመንፈስ ቅዱስ ነው::ከፀጋው ችሎት የተነሳ በውስጣችን ያለው ሰላምና እረፍት ከእኛ አለፎ ለቤታችንና ከእኛ ጋር ላሉት ሁሉ ይፈሳል:: **** የሰላማችንና የእረፍታችን ምንጭ ኢየሱስ በእምነት በእኛ ውስጥ እንደሆነ እኛም ደግሞ በእርሱ ወስጥ ልንሆን ሙሉ በሙሉ በፈቃዱ ውስጥ ልንገኝ ያሰፈጋል::
አማኝ ለብቻው ለእግዚአብሔር መገኘቱ ለመንፈሳዊ ህይወቱ ወሳኝ ነገር ነው:: ከእግዚአብሔር ደግሞም ከፀጋው ችሎት የሆነ አሸናፊነት በረከትና መንፈሳዊ ብልፅግና በህይወታችን የሚሆኑት ለእርሱ ብቻችንን ከመገኘታችን አንፃር ነው:: *** ፈፅሞ በክርስቶስ የረካ ማንነት ሊሆንልን የሚችለው ብቻችንን ለጌታ ስንገኝ ነው:: ይህም ደግሞ በክርስቶስ ሙሉ ሰው ጠንካራ ሥር የሰደደና የተተከለ ያደርገናል::
የተሰጠንን ይህን ሕይወት የምንጠብቅበት መንገዱ ጸሎት ነው
መዝ 30-15 , 1ኛ ጴጥሮስ 3-15 እግዚአብሔር ወደ ፃድቃን ይመለከታል ጩኸታቸውንም እንደሚሰማ መጵሐፍ ቅዱስ ይነግርናል:: ወደ እግዚአብሔር የሚጩህ ጩኸት ሀይል አለው::
ሩት ኑአሚንን ተከትላ ስትሄድ ምንም ተስፋ የምታደርገው የራሷ ነገር አልነበረም:: ሰው ወደ መለኮት ሐሳብ ሲገባ የራሴ የሚለው ተሰፋ የሚያደረገው ምንም ነገር ባይኖርም ህይወቱ ግን በእርካታ የተሞላ ይሆናል::
ሰው በሀጢአት ምክንያት ሲወድቅ ያጣው አንዱ ቸርነት ማድረግን ነው:: ጌታ የቸርነት መገለጫ የመጨረሻ የሆነውን ነፍሱን በመስጠት አሳይቷል:: ቸርነት ማድረግ ነገ የሚበቅልን ዘር መዝራት ነው:: በልጆች አና በዘመናት የሚታጨድ ነው::
እግዚአብሔር እኛን ማናገር ወደ ሚፈልግበት ቦታ ማድረስ ይፈልጋል:: የመለኮት ሐሳብ የሚገለጠው ሰው በፈለገበት ቦታ ላይ ሳይሆን እግዚአብሔር ሊናገር በሚፈልገው ቦታ ነው::
ትክክለኛ ፀሎት ለመፀለይ በቅድሚያ ማስተካከል ካለብን ነገሮች መካከል 7 ዋና የሆንትን እንድናይ ይርዳል
መፅሐፍ ቅዱስ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ወደ እግዚአብሔር ሐሳብና ፈቃድ የተመለሱ ሰዎችን ታሪክ የያዘ ነው:: ሰማያዊውን ነገር የሰማና የታዘዘ ሰው እርሱ የምድርን ገፅታ የሚቀይር ነው::
ሆሴ:6 እግዚአብሔር ምህረትን እንወድድ ዘንድ ጠርቶናል:: በዘመናት መካከል በጣም አስቸጋሪ ነገሮች ሲመጡ እግዚአብሔር ከእኛ የሚፈልገው ምህረትንና እርህራሔን እንድንለምን ነው::
እግዚአብሔር ባለበት የሚገኝ ሰው ነገን ያየዋል :: እርሱ ባለበት መገኝት ዋጋ ይስከፍላል::
ማሪያም እና ማርታ እየሱስ ምንም እንኳ ወዳጃቸው ቢሆንም እነርሱ በላኩበት ጊዜ ሳይሆን: ነገር ግን እርሱ በፈቀደው ሰአት መጣ:: የጌታ መምጣትና የነገሮቻችንም መለወጥ እኛ በምንፈልገው ጊዜ ሳይሆን ለጌታ ክብር በሚሆንበት ጊዜና ሰአት ይሆናል::
ለፊሊጵስዩስ ስዎች መልክቱን በሚፆፍበት ወቅት በእስር እንደነበር እና ይመልክቱ ዋና አላማ በሚደርስበትሁሉ ደስታው በጌታ እንደሆነ ይናገራል::
ሳሙኤል እሴይ ቤት ሔዶ በእውነት እግዚአብሔር የሚቀባው ይህ ነው ብሎ ኤልያብን ሊቀባው ተነሳ:: አንዳንድ ጊዜ መንፈሳዊ ነገር በውስጣችን ሲያልፍ እርግጠኛ ላልሆንባቸው ነገሮች መጋለጥ እንጀምራለን::
ጳውሎስ ይህንን መልእክት የፃፈው በሁለት ነገሮች መካከል ሆኖ ነው:: ወደ ጌታ መሔድና በዚህ ሆኖ የወንጌል ስራውን መቀጠል ቤተክርስቲያንን የመጥቀም ሀሳብ: ነገር ግን የቱን እንደሚመርጥ እንደተቸገረ ይገልጣል::
ኢየሱስ ክርስቶስ የህይወት ብርሃን ነው:: አማኞች ደግሞ የአለም ብርሃን ናቸው:: ሰለዚህ የብርሃን ልጆች ብርሃን ካልሆኑ ይህ አለም ምን ተስፋ አለው? እምነታችን በመልካም ምሳሌነት ሊገለጥ ይገባዋል:: *** የእግዚአብሔር መገኘት በመሀላችን እንዲሆን በብርሃንነታችን ልንመላለስ ደግሞም ህብረትና አንድ ልብ ሊኖረን ይገባል:: በዛም በረከትና ፈውስ መፅናናትም ይኖራል::
መፅሐፍ ቅዱስ የሗላችንን ወይንም የትኛው ትናንትናችንን ልንረሳ እነደሚገባ እንደሚነግረን እንዲሁ ደግሞ ትናንትናችንን ለምን መርሳት እንደማይገባን ይመክራል:: *** ትናንት በእግዚአብሔር አብሮነት የእርሱን ምህረትና ጥበቃ ያስተዋለ ሰው ነው ከፊቱ ያለውን ተግዳርት በድል ሊሻገር የሚችለው::
በመንፈሳዊ ህይወታችን ሚዛን ጠብቀን መኖር እጅግ አሰፈላጊ ጉዳይ ነው:: ይህ ባይሆን ግን የውስጥ ጠላት ወይንም የክርሰቶስ መስቀል ጠላቶች እንሆናለን:: በትምህርት ውስጥ በተዘረዘሩት 7 ነጥቦች ሚዛናዊ ህይወታችን የትጋ እንዳለን መመልከት እንችላለን::
ሐዋነርያው ጳውሎስ ትልቅ መንፈ ሳዊ ነገር የተቀበለ ደግሞ ያየና የሰማ ሲሆን ነገር ግን ትንሽ መሆን የቻለ ሰው ነው:: *** ጤነኛ መንፈሳዊ ህይወት በተቀበልነው ወይንም ባየነውና በሰማነው ትላልቅ መንፈሳዊ ሰጦታዎቸ ላይ ራሳችንን ትነሽ ለማድግ በተለማመድንበት ነው::
ክርሰትናን ስንጀምር የነበረው ህይወታችን: ሁሉን በጥንቃቄ የያዝንበትና : በፍቅር የተመላለስንበት እንዲሁም ህይወታችንን ከሐጢአት ለመጠበቅ የነበረው ቆራጥነት እየዋለ እያደረ እየተለወጠ መጥቷል:: በእግዚአብሔር ቤት ቆይታ እውቀት እያገኘን ስንመጣ እውቀታችን ህይወት እየሆነ ክርስቶስ ወደ ጎን እየተተወ የመጣበት ሁኔታ ነው ያለው:: -- ለሚዛናዊ ህብረት ክርስቶስን ጌታና ራስ ማድረግ ያስፈልጋል::
በክርስትና ህይወት ውሰጥ: ሚዛናዊ ህይወትና ሚዛናዊ አገልግሎት ሁለቱ የማይነጣጠሉ ዋና ነገሮች ናቸው:: ** ክርስትና የክርስቶስን ህይወት መሞላት ነው:: አገልግሎታችንም የሚመሰረተው ራሳችንን ባዶ ባደረግንበትና ክርስቶስን በተሞላንበት ላይ ነው::
እግዚአብሔር በፍቅር በመስማማትና በመቀባበል ውስጥ የሚሰራ አምላክ ነው:: ከዚህ ስንጎድል ችግር ይሆናል:: ነገር ባለበት ወንጌል አይሮጥም መገለጥ አይኖርም ሁሉ ነገር ይቆማል:: *** ብዙ የሚያናውጡ ነገርች በቤተክርስቲያን ይከሰታሉ:: ከዚህ ውስጥ የሚያመልጡ እነርሱ ወደየትኛውም ያላዘነበሉ በጌታ የቆሙ ህይወት ቀደም የሆኑና መዳን ህይወታቸውን የሞላው ናቸው::
የክርስትናን ህይወት ያለ ተስፋ መኖር አይቻልም:: ተስፋን የሚሰጥ አግዚአብሔር የታመ ነውና የተቀበልነው ተስፈ ሳይፈፀምአይቀርም:: ነገር ግን ደግሞ ከእኛም ሁኔታ ጋር የተገናኘ ነው:: *** በዚህ ትምህርት ውስጥ ተስፋችንን ለመውረስ በእኛ በኩል የሚጠበቁብን ነገሮች ተዘርዝረዋል::
በእግዚአብሔር ፈቃድና ሀሳብ ውስጥ ስንኖር በምናልፍበት ማንኛውም አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ ዛሬም በአጠገባችን የሚቆም የሚረዳንና የሚያግዘን የሚያፅናና ተስፋችንንም የሚያድስ እርሱ ትናንትን ያሳለፈን ጌታ ነው:: *** ችግርና መከራ የሚለውን ሳያይና ሳይሰማ ልቡን በእግዚአብሔር በአምላኩ ላይ ያበረታ እርሱ ይሻገራል::
የወንጌል ትልቁ በረከት ሰዎችን ወደ እረፍት ወደ ደስታና ሰላም ማሰገባት ነው:: ይህ እረፍት ወደ መንፈሳዊ የህይወት አረፍት በጌታ ፀጋ የምንገባበት ነው:: *** አማኝ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምቶ የራሱ ባደረገው ጊዜ ሰላሙ አነደ ፅድቅ ወንዝ ይፈሳል::
በአዳም ሀጢአት ምክንያት እኛ ሁላችን ከእግዚአብሔር ፊት ከክብሩም ወጥተን ነበር:: በኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሙሉ ወደሆነው የመለኮት ተቀብሎት ገባን:: ** ዛሬ በምድር የምንኖረው ህይወት በላይ በፊቱ ያለንና ያገኘነው ተቀብሎት ነፀብራቅ ነው::
Play Episode Listen Later Dec 11, 2020 29:58
የእለት ተእለት ህይወታችን እግዚአብሔር ቀደም ካልሆነ የዘመኑን ክፋት ማየት ደግሞም መዋጀት አይቻለንም:: ** እግዚአብሔርን ያስቀደመ: ፈቃዱን ያስቀደመ: መስቀሉን ያስቀደመ እርሱ ነው ለጌታ የተሰጠ በክፋት እየጨመረ የሚሄደውንም ዘመን የሚዋጅ::
ለአንድ ክርስቲያን ኑሮ የእግዚአብሔር አብሮነት ወሳኝና እጅግ አስፈላጊ ነው:: የእግዚአብሔር አብሮነት ለብርታታችንና ከክፉ ለመጠበቃችን ምክንያቱ እርሱ ነው:: *** የእግዚአብሔር አብሮነት ከእኛ ጋር እንዲሆን በቃሉ ውስጥ ልንሆንና ልንታዘዝ እንደ ፈቃዱና እንደ ሀሳቡም ልንኖርና ልንመላለስ ያስፈልጋል::
እግዚአብሔርን በሙሉ ሀይሉና ፈቃዱ በሙሉ ልቡና ሀሳቡ የሚወድ እርሱ ለእግዚአብሔር የተገዛ ነው:: እግዚአብሔር ገዢ ነውና ሰው ለእግዚአብሔር በግርማው ይገዛል ወይንም በስልጣኑ ይገዛል:: ከዚህ ውጭ የሚሆን የለም:: *** ለእግዚአብሔር በደስታ የተገዛ ሰው ነፃ የወጣ ነው:: የህይወት ሙላትም ያለው በዛ ውሰጥ ነው::
የገላትያ መልዕክት ሰለ ነፃነት ነው:: ከሀጢአት እስራት ነፃ ስለመውጣት ነው:: በሀጢአት ቀንበር ስር ያለ ሰው ለክርስቶስ መኖር አይችልም:: *** አርነት መውጣት ማለት ክርስቶስን የመኖር ብቃት ማግኘት ማለት ነው::
ሸክም አለን ማለት መደረግ ያለበት ይሁን የሚለው ነገር እንዲደረግ እኛ ውስጥ አለ ማለት ነው:: ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም አብረን እንሰራለን:: ምኞትግን ሸክም ሊሆን አይቸልም:: *** ለተቀበልነውና በውስጣችን ላለው ሸከም መሰራት ከመንፈሰ ቅዱስም ተጠቃሚ የምንሆነው በእርሱ የምንጠበቀውም በመታዘዝ ውሰጥ ብቻ ነው::
የእግዚአብሔር ቃል በህይወታችን ስፍራ ባገኘው መጠን ህይወታችንን ይነካል ወደ ውሰጥ ይገባል ያነቃቃናል ከፍ ያደርገናል ደግሞም ይባርከናል:: *** በዚህ ትምህርት ውሰጥ በህይወታችን የእግዚአብሔር ቃል ሰፍራ እነዲኖረው ማድረግ የለብንን ሰባት ነጥቦችን እናያለን::
አንድ ሰው በጌታ በኢየሱስ አምኛለሁ ሲል ለማመኑ ምልክቱ በመንፈስ ቅዱስ መሞላቱ ነው:: የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ በአማኞች ህይወት ውስጥ መቀመጡ ነው:: መንፈስ ቅዱስም ስራውን በእኛ የሚሰራው አኛ በእግዚአብሔር ላይ የታመነውን ያህል ነው:: ***ለማመናችን ምክንያቱ ሰለ ኢየሱስ የተገለጠልን እውነት ነው:: ለመዳናችን ምክንያቱ ደግሞ የተገለጠልንን እውነት ማመናችን ነው::
የህይወት ለውጥ የሚጀምረው ጌታ ራሱን ለእኛ ከገለጠበት ብርሀኑን ካበራልን ነው:: አማኝ በጌታ በኢየሱስ ሲያምን ለኃጢአት ሞቶ ለፅድቅ እንደሚኖር ይህንንም መቀበል ደግሞም መኖር አለበት:: *** ፅድቅ ባመንን እንድ ጊዜ ቦታ የሚወስድ ነው:: ሰለዚህ ሁልጊዜ በመፅደቃችን እርግጠኞች እየሆንን እለት እለት ግን ለመቀደስ እንኖራለን:: ቅድስና ኑሮ ነው::
በአለም ብዙ እውነት የሚመስሉ ነገሮች አሉ:: ነገር ግን እውነት አንድ ነው እርሱም እግዚአብሐር ነው:: ይህም እውነት የተገለጠው ወደ ሰውም የደረሰው በከርስቶስ ነው:: ከእውነት የሆነም እርሱ ነፃ የወጣ ነው:: *** እውነትን ህይወት: ኑሮ ያደረገ ነው ለመውደድ ለመማር ለመራራትና የክርስቶስን ህይወት ለመኖር ሊበቃ የሚችል::
በሰው ህይወት በተለይም በሸለቆና በምድረበዳ በሚያይልፉ ውሰጥ ብዙ ጥያቄ አለ:: ለጥያቄ ሁሉ መልስ ግን ከእግዚአብሔር በሰተቀር ከወዴትም አይገኝም:: በኃጢአት መክንያት ካልሆነ በሰተቀር የመናልፍበት አሰቸጋሪ ሁኔታ እግዚአብሔር እኛን ብቻችንን የሚያገኝበት አኛም ደግሞ ፈቃዱንና ሀሳቡን የምንረዳበት ስፍራና ጊዜ ይሆናል:: *** አግዚአብሔር አኛን በፍቅሩ ውሰጥ እንድንሆን ከእቅፉም እንዳንወጣ የያዘበት መንገድና ሁኔታ አሳምሞን ቢሆንም እነኳን ለጥቅማችን ነው::
እግዚአብሔር የበጎ ነገር ሁሉ ምንጭ ነው:: እስራኤልን በምድረበዳ መና እየመገበ ያስጓዘ ጌታ የተስፋይቱንም የምድር እንዲበሉ ታማኝነቱን አሳይቷል:: ህዝቡ ደግሞ ወደጌልጌላ ሊመጡ በዛም ከአምላካቸው ጋር ከሀሳቡና ከፈቃዱ ጋር ሊስማሙ ግድ ነው:: ***በዚህ ትምህርት እሰራኤል በእግዚአብሔር ፊት በጌልጌላ ምን እንዳደረገ ደግሞም ምን እንደተገለጠለት የምናያቸው ሀሳቦች እኛም ዛሬ የክርስትና ህይወታችን ብዙ መጋደል ላለበት ምሳሌዎቻችንና የምንማርባቸው ናቸው::
አንድ አማኝ ጌታን ተቀብሎ በእምነት በሚገኝ መዳን የእግዚአብሔር ልጅ ከሆነ በኃላ መዳኑ ሙሉ እንዳልሆነ ቢያሰብ ህግንም ለመጠበቅ ወደኃላ ቢመለስ ይህ ወደ አለማወቅ ወራት መመለስ ነው:: ከፀጋውም መውጣት ነው:: ****በክርስቶስ መሆናችን በነገር ሁሉ ራሳችንን ለእርሱና ለመነፈሱ ለማሰገዛት ለእግዚአብሔርም ነፃ ለመሆን ነው::
እምነትና ፀሎት የማይነጣጠሉ የአማኝ ህይወትና ኑሮ ናቸው:: በእምነት የሩቁን አሻግረን እናያለን:: እግዚአብሔርንም ደስ ማሰኘት በእምነት ነው:: ተስፋችንም ፅኑ እደሆነ የምናየው በእምነት ነው:: *** እምነት ካለን ተክክለኛና መሠረት የያዘ እውቀት ይመጣል:: የእምነትም መሠረት የእግዚአብሔር ቃል ነው:: ወደ ቃሉ እንመለስ::
የእግዚአብሔር ፈቃድ ሰው ለእርሱ እንዲሆን ነው:: ይህ ደግሞ ከመፈጠራችን በፊት የነበረ የእርሱ ፕላን ነው:: ይሁን እንጂ ሰው በኃጢአት ምከንያት ከዚህ የጌታ ፈቃድ ቢወጣም በልጁ በኢየሱስ ክረስቶስ ወደ ተፈጠርኖበት አላማ እንድንመለስ አድርጓል:: *** ሰው ለእግዚአብሔር ሲኖር ሰላም ይኖረዋል:: በምድረበዳ ብንሆን በሸለቆ ህብረታችን ከጌታ ጋር ስለሆነ ነፍስና መንፈሳችንን የሚያረካ የእርሱ መንፈስ ይደግፈናል::
ሰው ህግን በመጠበቅ ሳይሆን የህግ ፍፃሜ የሆነውን ኢየሱስን በማመን ነፃ ይሆናል:: ከኩነኔ ከፍርድ ነፃ ይሆናል:: በክርስቶስ ነፃ የወጣ ሰው እርሱ በእግዚአብሔር ፊት ያለነውርና ያለነቀፋ ይታያል:: እግዚአብሔር አባት ነው ብሎ በደስታ በነፃነት ያመልካልም:: *** ነፃነታችን እንደፈለግን ልንሆን ሳይሆን ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስ ሆነን ልናመልከው ነው እንጂ::
እግዚአብሔር ሁሉን ለክብሩ ፈጥሮታልና እኛን ወደ አካሉ ሲጠራን ለእርሱ ክብርን እናመጣ ዘንድ ነው:: ለእርሱ የሚገባውን ክብር ለማምጣት ደግሞ ምንጩ በክርስቶስ መሆናችንና ተፈትነን በወጣነበት ልክ ነው:: *** ራሳችንን ካጣንበት ጌታ ብቻ ማንነታችንን ከሞላበት ከዛ ከሞተው ማንነታችን ለእርሱ ክብርን እናመጣለን::
እግዚአብሔር እንዳለ እናውቃለን ደግሞም እናምናለን:: በህይወታችን የእርሱ ክብር የእርሱ ችሎት እንዲገለጥ ግን አብሮነቱ ሊበራልን ሊገለጥልን ያስፈለጋል:: ይህም ደግሞ የሚሆነው እኛ ለእርሱ ምቹ ሆነን በተገኘንበት መጠን ነው:: *** እግዚአብሔር ለእኔ አለ የሚል አብሮነቱም የተገለጠለት እርሱ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ ፀንቶ የሚቆም ደግሞም ምስጋና የሚበዛለት ነው::
ሰው በሀይሉ አይበረታም እንደሚል የእግዚአብሔር ቃል መነፈሳዊ ህይወታችንን ስንመለከት ሀቅም ባጣንበትና በደከምንበት ሁሉ እርሱ ብርታት ጉልበት ይሆናል:: በምናልፍበት በማንኛውም ሁኔታ ውስጥም ብቃት የሚሆነን እርሱ ነው:: *** የተጠራነው ለአሸናፊነት ነው:: ልናልፍበት ያለውን ሁሉ የምናልፈው ራሳችንን በሰጠንበትና እግዚአብሔርም ለእኛ በሆነልን ልክ ነው::
የእግዚአብሔር አለሁነት ፍጥረት ሊረሳው በማይችል ሁኔታ ይገለጣል:: እርሱ ፃድቅ ፈራጅ ነውና ፍርድን በማደላደል ይገለጣል:: ደግሞም በማዳን በፈውስና በማፅናናት ይገለጣል:: እውነተኛው ምስክርነት እርሱ ብሏል ማለት ብቻ ሳይሆን እኛም ደግሞ እውነት ነው እርሱ ያለው ለእኔ ሆኗል ሰንል ነው:: ደግሞም በአስፈሪውና በአስጨናቂው ፊት እርሱ ብሏልና እኔም እላለሁ ብለን ፀንተን ስንቆም ነው:: *** አንድን አማኝ እግዚአብሔር ጠንካራ ማድረግ የሚፈልገው ሲያለቅስ በመስጠት ሳይሆን ነገር ግን በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ እኔ አለሁ በሚል ነው::
እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ የሚችል አምላክ ሆኖ ሳለ፣ አንድ የማይችለውና የማይተባበረው ክሃጢያት ጋር ነው። እንዱ ትልቁ የጸሎት እንቅፋት ንስሀ ያልገባንበት ሃጢያት ሲሆን፣ ሌሎችም እንቅፋቶች በዝርዝር በዚህ ትምህርት ውስጥ ተጠቅሰዋል። እንዲሁም እነዚህን የተዘረዘሩትን የጸሎት እንቅፋቶች ካላስወገድን፣ የሚደርሱብንን ጉዳቶችና፣ እነዚህን እንቅፋቶች ለማስወገድ ደግሞ መወሰድ ያለባቸውን እርምጃዎች እንማራለን።
እውነት ሲገለጥልን ያለው እምነት
እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ ያለው በጎ ፈቃዱ በልጁ አምነው የዘላለም ህይወት አንዲሆንላቸው ደግሞም በዚህ አለም እንዲያገለግሉት ሀሳቡንም እንዲያከናውኑ ነው:: ከዘላለም የሆነው የመለኮት ሀሳቡም የሚያርፍበት እርሱ እግዚአብሔር በግል ያገኘው ሰው ነው:: በግል ለጌታ ያልተገኘ ሰው የጠራ ፍሬ ያለው የጌታ ሀሳብ በህይወቱ አይታይም:: እግዚአብሔር ብቻችንን ሲያገኘን እኛም ደግሞ ስንገኝለት ፀጋ ይጨመራል:: በእግዚአብሔር ቃል እናድጋለን አከሔዳችን የተለየ ይሆናል:: ከማያንፅ ፍሬ ከሌለው ከአለም ሀሳብና ስራ እንለያለን::
እግዚአብሔር የእርሱ የሆኑትን አይተውም እንደ ተስፋ ቃሉ ያስባል:: አያለፍንበት ያለው ህይወትና ኑሮ:: እንደጠበቅነው ወይንም እንደተባለልን ባይሆንም እንኳ ጌታ የታመነ አምላክ ነው:: ያስባል:: በጊዜውም ይመጣል:: አስበኝ ያሉ ሁሉ ታስበዋል:: *** እግዚአብሔር ህዝቡን ያስባል :: ባህርይው ስለሆነ:: በዚህም ለእኛ ያለው በጎነቱና ፍቅሩ ደግሞም ምህረትና ቸርነቱ ይገለጥበታል::
ልጆች በወላጆቻቸው ዘንድ ማደጋቸው በጉጉት የሚጠበቅና ደስ የሚያሰኝ እንደሆነ እንዲሁ በመንፈሳዊ ህይወታችን በነገር ሁሉ ማደጋችን በእግዚአብሔር ዘንድ የሚጠበቅና ደስ የሚያሰኝ ነው:: በመንፈሳዊ ህይወቱ ያደገ ሰው በፅድቅ ይገለጣል:: እግዚአብሔርን ደስ የማያሰኘውን ሁሉ ኃጢአትንና ሰጋን እምቢ የማለት ሀቅም ይኖረዋል:: *** ያደገ አማኝ በአምላኩ የሚታመን የሚመካም ነው:: በዙሪያው ከሚያየውና ከሚሰማው በላይ እግዚአብሔር ትልቅ ነው ይላል::
እግዚአብሔር ያሰበልንን የአሁኑንም ሆነ ዘላለማዊውን እርስት ለመውረስ ቀዳሚው እኛ በጌታ ልንወረስ ያስፈልጋል:: በጌታ ያልተወረሰ ለእርሱ ያልተገዛ ማንነታችን ከጌታ ለምንቀበለው ማንኛውም ነገር እንቅፋት ይሆናል:: በአመታት መካከል እስራኤልን በድንቅ የመራ የረዳ ዛሬም ለህዝቡ ጌታ ታማኝ ነው:: ይመራል: ሞገስ ይሆናል: ይባርካል: ብርታትና ጉልበትም ይሆናል:: ከእኛ የሚጠበቀው ሙሉ በሙሉ ራስን ለፈቃዱ ማስገዛት ደግሞም ጌታ ለእኛ ያሰበልንን ማየት ነው::
እግዚአብሔር ነገርን ሁሉ ውብ አድርጎ ይሰራል:: ካለንበት ሁኔታ ወይንም ከምንልፍበት ነገር ተነስተን የተረሳን የተተውን ቢመስለን እንኳ እግዚአብሔር ግን ታናሽ የተባለውን የተናቀውን ነገርና ማንነታችንን ሊጠቀም ከዘላለም በፊት በእኛ ላይ ወዳለው ሀሳቡ እኛን የሚያስጠጋበት ወደ ከፍታውም የሚያወጣበት ይሆናል:: *** እግዚአብሔር የመልካም ገር ሁሉ ምንጭ ነውና የእርሱ ጊዜ ብቻ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር መራራ የተባለውን ህይወታችንን እና ነገራችንን ወደ ጣፋጭ ሊቀይር የታመነ ነው:: እኛም ፀንተን እንጠብቀው::
ሰው መንፈሳዊ አይኑ ተከፍቶ ካለበት ሁኔታ አልፎ የእግዚአብሔርን ፈቃድና ሀሳብ ማየት ካልቻለ በእርሱ ሊሆን ካለው የጌታ ሀሳብ ጋር ይተላለፋል:: አልፎ የሚያይ አማኝ ህይወቱ በከፍታ የሆነ ከእግዚአብሔርም ጋር የተስማማ ነው:: ሰለዚህ የመንፈሳዊ ህይወታችን እድገትና ያለንበት ከፍታ አይኖቻችን ተከፍተው በዙሪያችን ካለው ሁሉ አልፈን የጌታን ፈቃድና ሀሳብ ያየነውን ያህል ነው:: ***አማኝ በእምነት ፀንቶ ሊቆም ደግሞም በአምላኩ ሊታመን የሚችለው ካለበት ሁኔታና ነገሮች ባሻገር አልፎ የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃሉን በማየት ነው::
ትዳር ማለት መውሰድ እንዲሁም ደግሞ መወሰድ ማለት ነው:: ከፈጥረት መጀመሪያ አዳም ሄዋንን ከእግዚአብሔር እጅ ተቀብሎ እንደወሰዳት እነዲሁ ዛሬም አንዳችንን ለአንዳችን የሚሰጥ ትዳርን የሚሠራ እርሱ እግዚአብሔር ነው:: ሰለዚህ የተወሰደ አይመለስም:: ምክንያቱም ሁለቱ ተጣብቀዋልና:: አንድ ስጋ ሆነዋልና:: ትዳርን የሚጠብቀው ሁለቱም በመንፈሳዊ ህይወታቸው በሁለት እግራቸው የቆሙና በብርሃን ውስጥ መሆናቸው ነው:: *** - በግል ህይወቴ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት በፅድቅና በአውነት አለሁ ወይ ? - አልሆነችልኝም ወይም አልሆነልኝም ሳይሆን እኔ ሆኜለታለሁ ወይ ? ወይም ሆኜላታለሁ ወይ ? ብሎ መጠየቅ ከሁለቱ የትዳር አጋሮች ይጠበቃል:
በሰው ህይወት ውስጥ መስማትና ማየት ትልቁን ሰፍራ ይይዛል:: ሰለዚህ ሰው መስማትና ማየት ያለበትንና የሌለበትን በጥንቃቄ ሊለየው ይገባል:: ምክንያቱም ሰው በሚሰማውና በሚያየው ይወድቃል ከበረከትም ይጎድላል:: እንዲሁም በሚሰማውና በሚያየው ይታነፃል ሀይልና ብርታት ይሆንለታል:: አማኝ ሁልጊዜም ሊሰማው የሚገባው አንድ ድምፅ አለ:: እርሱም የመንፈስ ቅዱስ ድምፅ ነው:: እርሱም የትናንትናን ያሳስባል የነገውንም ይናገራል:: እንዲሁም ደግሞ ሊያየው የሚገባው እርሱን በሁሉ ላይ ስልጣን ያለውንና ታዳጊውን ጌታ ነው:: በዚህም ውስጥ ሰላም ደግሞም ሀይልና ብርታት ይሆንልናል::
በመንፈሳዊ ህይወታችን መታደስ ማለት ከእግዚአብሔር ጋር የነበረንን ግንኙነት ከደከምንበት ከራቅንበት ወደ እርሱ መለስን ያመለክታል:: ለመመለስ እምቢ ባልን መጠን ከጥበቃውና ከቸርነቱ እንርቃለን:: ከእርሱ እየራቅን በሄድን ልክ ደግሞ ወደ ክፉው ወጥመድ እየገባን እንሄዳለን:: ይህ ሲሆን ሰላም ይርቃል በረከትና ሞገስ ይሸሻል:: *** እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር የሆና በስፍራው ያለ ሰው ታላቅ ሰላምና እረፍት ይሆንለታል:: እግዚአብሔር ለእርሱ ክብር ነው:: ሞገስም ነው:: እርሱ ክብር የሆነለት አማኝ በህይወቱ ትልቅ ለውጥ ይሆናል::አንደበቱ በፀጋ ቃል የተሞላ ደግሞም በሞገስ የሚወጣ የሚገባ ይሆናል::
የእግዚአብሔርን ቃል መስማት እጅግ መልካም ነው:: ነገር ግን ቃሉ የሚጠቅመን ደግሞም ፍሬ የምናፈራው የሰማነውን ቃሉን ለመጠበቅ ደግሞም ለተነገረን ቃል ለመታዘዝ ዝግጁ ስንሆን ነው:: ስለዚህ የአማኝ መንፈሳዊ ህይወት ጉልበትና ጥንካሬ ደግሞም በረከቱ የእግዚአብሔን ቃል ሰምቶ የጠበቀውን ያህል ነው:: እኛ ባልነው ሳይሆን ጌታ እርሱ ባለው ቦታና ሁኔታ ይገኛልና ሰምተን የምንጠብቀው ቃል ሰላምና እረፍት ይሆንልናል:: ተስፋን ያድሳል ቸርነቱና በጎነቱ የሚገለጠውም በዚሁ ነው::
የአማኝ ህይወት ድል የመንሳት ህይወትና ኑሮ ነው:: በኃጢአትና በስጋ ላይ ደግሞም በአለምና በሰይጣን ላይ:: ድል የመንሳት ህይወትና የአሸናፊነት ኑሮ የሚጀምረው ራስን ለጌታ ለፈቃዱና ለሀሳቡ በማሰገዛት በመሸነፍ ነው:: *** ለጌታ የተሸነፈ አርሱ በሚይልፍበት ሁሉ በጌታው ላይ የሚደገፍ በእምነት ፀንቶ የሚቆምና ደግሞም በፀሎት የሚተጋ ነው::ሰለዚህም በድል አድራጊነት ይጓዛል::
አማኝ በህይወቱ በብዙ ከፍታና ዝቅታ ውስጥ ያልፋል:: በዚህን ጊዜ በተለይም በምናልፍበት አሰጨናቂና ከባድ የፈተና ጉዞ ለምን? ደግሞም እስከ መቼ? በሚሉ መልስ በሚፈልጉ ጥያቄዎች ሁለንተናችን ይያዛል:: እግዚአብሔር ግን አሰጨናቂው ጊዜ ያልፋል:: ደግሞም ጨለማው ይነጋል ይላል:: *** እኛ በቃሉ ስንገሰፅ ስንመከርና ስንታዘዝ እሺ እንበል እራሳችንንም አዋርደን በፊቱ እንሁን እንጂ: ጨለማው ይነጋል:: ሲነጋም ነገር ሁሉ ይቀየራል:: ጠላት ወዳጅ ይሆናል:: የራቀው ይቀርባል:: ሀዘንም ይሸሻል:: ሰላምና ደሰታ ይሆናል:: ምስጋናም ይበዛልናል::
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሲጠራን በመነግስቱ ውስጥ ልንተጋ ደግሞም እሰከፍፃሜው ድረስም እንድንሄድ ነው:: ለዚህም ከእርሱ ዘንድ የሚረዳ ፀጋ አለ:: እሰከ ፍፃሜው የመሄጃው መንገድ ጠባብ መንገድ ነው:: ወደ ኃላ የሚጎትተንን በፍፃሜውም ከሚኖረን እረፍት ሊያሰቀረን የሚታገለንን ሁሉ ወደኃላ እየጣልን ወደ ፊት ብቻ የምንሄድበት መንገድ ነው:: ደግሞም ጌታም አብሮን የሚጓዝበት የመንፈስ ቅዱስም መፅናናት ያለበት ነው::
ናቡከደነፆር ያየው ህልምና ዳንኤል የተረጎመው የምሰሉ ምስጢር እኛ አስካለንበት ደግሞም እስከ ጌታ ዳግም መምጣት ድረስ የሚዘልቅ ነው:: የዳንኤል መፅሐፍ የአለምን ሁኔታ እስከ ዘመን ፍፃሜ የሚሆነውን የሚገለፅ መፅሐፍ ነው:: በምድር ላይ ሊሆን ያለው የመለኮት ፈቃድ መተርጎሙ ትልቅ ነገር ነው:: ወደ ፈቃዱና አመራሩ መምጣት ደግሞ ታላቅ በረከት ነው:: እግዚአብሔር ገዢ ነው:: ደግሞም መሪ ነው:: እርሱ ሲመራን መንፈሱ ወደ እውነተኛ ንስሀ ይመራናል:: በፊቱም ትሁት እንሆናለን::
አማኝ በዚህ አለም ሲኖር እንደፈለገው ሊወጣና ሊገባ በተሰማውና ባየው የሚሰራና የሚናገር ሳይሆን ህይወቱን በመርህ የሚመራ ነው:: የእግዚአብሔርን ቃል መርሁ ያደረገ ነው:: *** የእግዚአብሔርን ቃል መርሁ ያደረገ አማኝ በመጀመሪያ የእምነት ሰው ነው:: በነገር ሁሉ ወስጥ የእግዚአብሔርን ታላቅነት ያያል:: ደግሞም እንደ ቃሉ ይፀልያል በትህትናና በፅድቅ እግዚአብሔርን በመፍራት ይመላለሳል::
ዳንኤልና ጓደኞቹ በልጅነታቸው የተቀረፁበትና ያደጉበት የእግዚአብሔር ቃል (የህጉ መፅሐፍ ) ለዛሬው ህይወታቸው ፅኑ መሰረት ነው:: እኛም ለልጆቻችን የወደፊታቸውን ቀን ወይም ዘመን መፍጠር አንችልም:: ነገር ግን ለነጋቸው የሚያበቃቸውን የእግዚአብሔርን ቃል ልንሞላባቸው በዚህም ልናሳድጋቸው ያስፈልጋል:: የነገ ዋስትና ጌታ ብቻ ነው:: *** በምድር ላይ ብዙ ነገሮች ልናገኝ እንችላለን ነገር ግን ማምለጫው በአንድ አቅጣጫ ብቻ ነው:: ለእግዚአብሔር በተገዛንለት በኩል:: የህ ደግሞ የእርሱን ታላቅነትና ክብር ወደ ምንገልጥበት ከፈታ ያመጣናል::
በዚህ አለም ብዙ እውቀት ጥበብና ሥልጣኔ አለ:: ደግሞም እየጨመረ ይሄዳል:: ነገር ግን ይህ ሁሉ የአለም ጥበብ አውቀት በእውነትና በፅድቅ እግዚአብሔርን ለሚያመልከው ህዝብ ለቤተክርኝቲያንም ፈተና የሚሆን ዋጋም የሚያስከፍል ይሆናል:: በዳነኤልና ጓደኞቹ ዘመን የሆነውና ተጽፎ የምናገኘው ለዛሬ ደግሞም ወደፊትም ሊሆንና ሊገለጥ ላለው ጥላ ነው:: ሰለዚህ በዚህ ትምህርት ውስጥ ናቡከደነፆር ያየውን ህልምና የህልሙን ፍቺ ከእኛ ዘመን ጋር ያለውን ዝምድና እንማራለን::
በሁሉ ላይ ገዢ የሆነው እግዚአብሔር ደግሞም መሪ የሆነው እግዚአብሔር እርሱ ታዳጊም ነው:: በዳንኤልና ጓደኞቹ ህይወት የተገለጠውም ይኸው ነው:: ከእሳት ሲታደግ ከአንበሳም ሲያሰመልጥ:: ሀአማኝ ህይወት የእግዚአብሐር ገዢነት መሪነቱና የሀይሉ ችሎት የሚገለጠው እኛ ለእግዚአብሔር በሆንለት በተገዛንለትና በተገኘንለት መጠን ነው:: *** በአለም ያለው ጨለማ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አይሄድም:: ነገር ግን እግዚአብሔር በዘላለም እቅዱ ለእርሱ በሚገኙለት የክብር ዐቃዎች ሉአላዊነቱን ክብሩንና ብርሃኑን እለት እለት ይገልጣል::
ኑኃሚንና ሩት ተቀናጅተው በፍፁም መሰጠትና ፍቅር እርስ በአርሳቸው እየተመካከሩ መራመድ የጀመሩት ህይወት ጥንቃቄና ጥበብ የሞላበት አካሔድ እንደሆነ እናያለን:: በቤት ቢሆን በቤተክርስቲያን አብረን ህይወት ጎዳና ከምንጓዘው ወይንም አብረን በቤቱ ከምናገለግላቸው ወገኖች ጋር ስንቀናጅ የመጀመሪያው በፍፁም መሰጠት በታማኝነትና በፍቅር ለመመካከር ደግሞም ለመታዘዝ ዝግጁ መሆን ነው:: *** በህይወታችን ታማኝ መሆን ደግሞም ታዛዥ መሆን ለመባረካችንና ለመፈወሳችነ ደግሞም ለመንገዳችን መቃናት መሠረት ነው::
ዘመኑ እየከፋ በሔደበትና የምናያቸውና የምንሰማቸው ነገሮች በሙሉ አስጨናቂና ተስፋ የሚያስቆርጡ በሆኑበት በዚህ ጊዜ የልቡናችን አይኖች ሊከፈቱና አርቀንም ልናይ ያስፈልጋል:: የልቡናችን አይኖች ሲበሩ ተሰፋችን ከምድር ላይ ተነስቶ የዘላለም ህይወት ተስፋ ላይ ይሆናሉ:: *** ሀአማኝ ህይወት ላይ የተጠራበት የዘላለም ህይወት ተስፋ ገዢ ሲሆን እለት እለት የሚያወራውና የሚናፍቀው ደግሞም በዝግጅት የሚኖርለት ይሆናል::
የሮሜ መልዕክት. 10: 14-17 , 11: 1-11
እግዚአብሔር ፈቃዱን ደግሞም ክብሩን በቃሉ ይገልጣል::የእግዚአብሔር ቃል ለመምከር ለመገሰፀ ደግሞም ለመባረክ ወደ ሰው ይመጣል:: ከወረድንበት ጥልቅ ጉድጓድ ከተስፋ መቁረጥ ያወጣናል:: ለቃሉ በህይወታችን ሰፍራ እየሰጠን በመጣን መጠን የጌታ ብርሃን ወደ ህይወታችን ይበራል አማኝ በቦታው ሲገኝ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጉብኝት ይሆናል:: የእርሱ ጉብኝት ደግሞ ወደ ክብር ያወጣል: የህይወት መታደስ ይሆናል:: ጨለማው በብርሃን ይሞላል:: ልምላሜና በረከትም ይሆናል::
አማኝ ለበራለት በትክክል ለተረዳውና ላመነው ጌታ ራሱን መሰዋዕት እሰከማድረግ ድረስ ፀንቶ ለመቆም የጨከነ ነው:: ይህም ደግሞ የፀጋውን ችሎት የሚያሳይ ነው:: የዳንኤል ህይወት ለዚህ ድነቅ ምስክር ረው:: ነገሮች በዙሪያችን ክፋታቸው በዝቶ ጫፍ ሲወጣ ሊያጠፉን የደረሱ እስኪመስል ድረስ ሊያስጨንቁን ይችላሉ:: ነገር ግን ይህ ሁኔታ አግዚአብሔር ፅድቁን የሚገልጥበት እኛም ክብሩንና ታላቅነቱን የምናይበት ይሆናል:: እግዚአብሔር ይናገራል አሁንም ይናገራል:: ሰውም ሰምቶ እስኪመለስ አብዝቶ ይታገሳል:: ደግሞም በፅድቅ የሚፈርድ ሰለሆነም በፍርድ ይገለጣል::
አማኝ ባለው ሥልጣን እውቀትና ሀብት እግዚአብሔርን ለማምለክ ራሱን ባያዋርድ ለመውደቅ ለመዋረድ ምክንያት ይሆናሉ:: ሥልጣን ድፍረትን እውቀት ትእቢትን አንዲሁም ሀብት ደግሞ ትምክህትን ያመጣሉና:: የእግዚአብሔር ልጆች እኛ ያለን ሁሉ ከእግዚአብሔር እንደተቀበልን ደግሞም የተቀበልነውን እርሱን በማክበር የምንጠቀምበት ሊሆን ይገባል:: በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን ጠላት ሰጋና አለም በብዙ ቢፈትኑንም ፈተናውን ሳንፈራ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ በፀጋውም ጉልበት ድል እያደረግን እንጓዛለን::
አማኝ በዚህ አለም ሲኖር ከሚያልፍበት ፈተናና መከራ ባሻገር ያለውን የዘላለም ህይወት ተስፋ እያየ በአሸናፊነት መራመድ የሚችለው መደገፊያውና መታመኛው እግዚአብሔር ን ያደረገውን ያህል ነው:: *** እግዚአብሔር ለሚታመኑበት ጋሻ ነው:: በእርሱ የታመነ የተደላደለ ነው:: ብዙ ስራም የበዛለት: በመከራ ጊዜ እረፍተና መፅናናት በአሰጨናቂውም ሰአትና ሁኔታ ሰላም ሀይልና ብርታት ይሆናል::
አማኝ ሊመስል የሚገባው ማንን እንደሆነ የእግዚአብሔር ቂል በግልፅ ይናገራል:: ሁላችን ክርስቶስ ኢየሱስን እንመስል ዘንድ ተጠርተናል:: ልጅ ወላጆቹን እንደሚመስል እንዲሁ ኢየሱስን በማመን የእግዚአብሔር ልጆች የሆን እኛ ሁላችን ጌታን እመስላለን:: *** የእግዚአብሔር ልጆች በእውነትና በፅድቅ እርሱን በመምሰል ስንንኖር ዋጋ ሊያሰከፍለን ግድ ነው:: ይሁን እንጂ ዋጋችን በጌታ ፊት እጅግ የከበረ ነው:: እለት እለት እርሱን ለመምሰል ራሳችንን እናስለምድ:: ጌታም የሚረዳ ፀጋውን ይሰጠናል::
ይህ አለም ጅማሬ እንዳለው ሁሉ ፍፃሜም ያለወ ነው:: የዳንኤል መፅሐፍ የትነቢቱ ፍፃሜ ይህንኑ የሚገልፅ እስከ ዘመን ፈፃሜ እሰከ ጌታ ዳግመኛ በክብር መገለጥ ድረስ የዘለቀ ነው:: ይህ ደግሞ ከሰው እውቀት የመነጨ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለሆነ በጥንቃቄ የምንመረምረው ደግሞም በመንፈስ ቅዱስ እንዳታ የምንረዳው ነው:: *** በአለም ያለው ክፋት እየጨመረ ጨለማውም እየከበደ እንደሚሔድ የተገለጠ እውነት ኀው:: ቤተክርስቲያን ግን እየታደሰች አማኞችም በመከራ ውሰጥ በፀጋው ኃይል በድል ነሺነት ለመሻገር የሚተጉበት የሚዘጋጁበትም ዘመን ነው::
በእግዚአብሔር ላይ የታመነውና መደገፊያውንም እርሱን ያደረገ ዳንኤል በፊቱ ቅንነት ተገኝቶብኛል አነዳለ አማኝ የእግዚአብሐርን ክብሩንና ሉአላዊነቱነ የሚያይበት መንገዱ ቅንነት ነው:: ይህ ደግሞ አንዱ የጌታ ባህርይ ነው:: ቅንነት ባለበት በዛ ንፁህ ህይወት ይገለጣል:: ትእግስት የበዛለት በእውነትና በፅድቅ የሚኖረው ፀጋም የሚበዛለት እርሱ በቅንነት የሚሄደው ነው:: *** አማኝ ከቅንነት ከጎደለ ህሊናው ንፁህ አይሆንም:: በቅንነት የሚራመድ እርሱ ግን ከእግዚአብሔር ጋር ይራመዳል:: የዛሬን ብቻ ሳይሆን የወደፊት ዘመንም አሻግሮ ያያል
በሰማይ ቢሆን ሀምድር ያለ እግዚአብሔር ፍቃድ የሚሆን አነዳች ነገር የለም:: የሚሆነው ሁሉ ከላይ እንደ ተፃፈው ይሆናል:: ዳንኤል ይህን ረጅሙን ዘመን ተሻጋሪውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ነው ያየው::ይህ ደግሞ የእግዚአብሔር ህዝብ አይኑን በምድር ላይ ከሚሆነውና ከሚፈራረቀው ነገርና ሁኔታ ላይ አንስቶ ከአግዚአብሔር ሀሳብ ጋር እንዲስማማ ነው::: ***ከእግዚአብሔር ጋር ረጅሙን መንገድ የሚራመዱ እነርሱ የሚያስተውሉ የተናገራቸውንም ቃል ደግሞም መንፈሱን የሚጠብቁ ናቸው::
በምድር ላይ ብዙ ጥሩና መልካም የሆኑ የሚያፅናኑ ምክሮች ይኖራሉ:: ነገር ግን በመከራና በችግር ሁሉ ውሰጥ አልፎ ማስኬድ የሚችል እውነተኛው ምክር ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው:: እግዚአብሔር በምክር ግሩም ነው ተብሎ እንደ ተፃፈ:: ደግሞም እርሱ በምናልፍበት ሁሉ አብሮን አለ:: ሁኔታዎች መልካም ባይሆኑምና ተስፋ በይሰጡም እንኳ በዚህም ውስጥ እግዚአብሔር አለ:: ይህንን ማየትና በእርሱ ላይ መታመን ይህ የአማኝ ትልቁ ሀብት ነው:: በመንፈስ ቅዱስ የሆነ መፅናናትም ለእርሱ ይሆናል::
በህይወት መንገዳችን ነገሮችን እያገጣጠመ በእኛ ሁኔታ ፈቃዱን የሚፈፅም እርሱ እግዚአብሔር ነው:: እርሱ በስውር የጠየቅነውን በግልፅ በአደባባይ የሚመልስ የሚባርክ ነው:: እኛ በስፍራችን በእምነት እንጠብቅ እንጂ:: እኛ የምንንቀሳቀስበት ጊዜ አለ ደግሞም በስፍራችን ሆነን በእምነት ዝም ብለን ጌታን የምንጠባበቅበት ጊዜም አለ:: የምናልፍበት መንገድ ላይገባን ይችላል:: ነገር ግን ጌታን መጠበቅ ወደ ፍፃሜው እድንደረስ ፍሬውንም ወደ መብላት ያደርሳል::
አማኝ ይህን አለም ማየት ያለበት አለማውያን ከሚያዩት በተለየ መንገድ በተከፈቱ መንፈሳዊ አይኖች ነው:: ይህ ሲሆን በዙሪያው ካለው ደግሞም ከሚያልፍበት ማንኛውም አስጨናቂ ሁኔታ ባሻገር ያለውን የዘላለም ተስፋ ያያል:: ደግሞም የክብር ተስፋ ያለው ጌታ ከእርሱ ጋር መሆኑን ያያል:: *** አይኖቹ የተከፈቱለት አማኝ ከእግዚአብሔር የሆነውንና ከአለም ወይም ከስጋ የሆነውን ለመለየት አይቸገርም:: በፈተናም ውስጥ የፀና ምስጋናም ደግሞ የበዛለት ነው::
ዳንኤል አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያቀና ሰው ነው:: በህልምና በራዕይ በመሰተዋል በእግዚአብሔር ፊት ያደገ ነው:: እግዚአብሔር በህይወት ዘመናችን ሊገልጥልን ያለውን ነገር የሚገልጥልን እራሳችንን በሰጠንበትና አካሔዳችንን ከእርሱ ጋር ባቀናንበት አካሄድ ነው:: *** እግዚአብሔር የተናገረን ቃል ህይወታችን ይሆን ዘንድ ደግሞም የቃሉ ትርጉም የኛ ሀሳብና ስሜት ሳይሆን የራሱ የጌታ ሀሳብ እንዲሆን የተሰበሰበ መንፈስና የሚያስተውል ልብ ሊኖረን ያስፈልጋል::
የአማኝ ትክክለኛው ፀሎት የሚጀምረው እግዚአብሔርን ፃድቅ በማድረግ ነው:: ደግሞም ራሱን በማዋረድና ዝቅ በማድረግ :: የዳንኤል ፀሎትም የሚያስተምረን ይህንኑ ነው:: እግዚአብሔር ለምን? ተብሎ አይጠየቅም:: እርሱ ፃድቅና እውነተኛ አምላክ ነውና:: ነገር ግን በምናልፍበት ሁኔታ ውስጥ ሁሉ የእርሱን ፈቃድና ከመከራው ባሻገር ምን እንዲሆን ማየትና መስማት ይሆንልን ዘንድ በማስተዋል በፊቱ ልንሆን ያስፈልጋል::
በእግዚአብሔር ፊት በፆምና በፀሎት መሆን አስፈላጊና ከእርሱ ዘንድ ወደ እኛ የሚመጣውን ፈቃዱን የምንሰማበት ወደፊትም ያለውን ሀሳቡን የምንቀበልበት ነው:: እግዚአብሔር በማንኛውም ሁኔታ ውስጥና ጊዜ ሊያናግረን ለጸሎታችንም መልሰ ሊሰጠን ይችላል:: ነገር ግን አዕምሮአችንና ልባችን በእርሱ ቁጥጥጥ ስር መሆን አለበት:: *** በክፉው ወጥመድ እነዳንያዝ የጌታንም ድምፅ ከመስማት እንዳንከለከል በዙሪያችን ከምናየውና ከምንሰማው ልንጠበቅ ያስፈልጋል::
እኔ በልቤ የዋህና ትሁት ነኝ እንዳለ ጌታ እንዲሁ አማኝ ከአለምና ከኃጢአት ነፃ ያወጣውን ጌታ ኢየሱስን ሊመስል ተጠርቷል:: ከአለም ስንወጣ አለምን እንመስል የነበረበትን ሁለንተና ጥለን ነው:: *** ሰው የውጭውን ያያል እግዚአብሔር ግን የውስጥ ማንነታችንን ያያል:: በእግዚአብሔር ፊት የልጁን መልክ መስለን እንታይ ዘንድ በቃልና በሰራ በእውነት በተለወጠ ማንነት ልንመስለው ይገባል::
ዳንኤል በእግዚአብሔር ፊት በፀሎት ሲተጋ በብዙ ዝቅታና ራስን በማዋረድ በብዙ ትህትና ሆኖ ነው:: ስለዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ ያገኘው መልስ የራሱን ዘመን አልፎ እስከ ዘመን ፍፃሜ ያለውን የሚያሳይ ሆኗል:: በፀሎታችን ውስጥ የሚረዳን የጌታ መንፈስ እንዳለ ሁሉ ከትክክለኛው የፀሎት መንፈስ ሊያወጣን የሚዋጋን እንዳለ ልናስተውል ይገባል:: አማኝ የክፉውን ውጊያ ሊያሸንፍና ፀሎቱም ከጌታ ዘንድ መልስ የመጣ ዘንድ በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ በጎ ህሊና ሊኖረው የተገባ ነው::
ሰው ፈቃዱና ሀሳቡ ስጋዊ ወደ ሆነውና ወደዚህ አለም አመፅ ባዘነበለ ጊዜ ለክፉው መጠቀሚያ ይሆናል:: በተቃራኒው ደግሞ ሰው ራሱን ቀድሶ እግዚአብሔርን ለማገልገልና ለማስከበር ቀናውን ነገር ሲያስብ ለእግዚአብሔር የሚጠቅም የክብር ዕቃ ይሆናል:: ዳንኤልም አንዱ የእግዚአብሔር የክብር ዕቃ ነው:: በመሆኑም ከሩቅ ዘመን ሆኖ የዘመንን ፍፃሜ የሚገልጥ ሆኗል:: በዚህ ትምህርት ነገር ሁሉ ወደ ፍፃሜው እየፈጠና አሰቀድሞ የተነገረውም ሁሉ እየተፈፀመ መሆኑን እናያለን:: በዚህ ሁሉ ግን አሁንም ወንጌል የምስራች ነው::
በዚህ የዳንኤል መፅሐፍ አንዱና ዋናው ጎልቶ የሚታየው ሀሳብ ይህ አለም ወደ ፍፃሜው እየፈጠነ መሆኑ ነው:: ስለዚህ እለት እለት ለኃጢአትና ለአመፅ እየሞትን ለፅድቅና ለእውነት እንኖር ዘንድ እጅግ አስፈላጊ ነው:: *** እግዚአብሔር የሚጠቀምበት የክብር ዕቃ እርሱ ሰባራ ማንነት ያለው ረሱን ዝቅ ያደረገና ትሁት ደግሞም የፍቅር ሰው ነው::
የመፅሐፍ ቅዱስ ትምህርት የትንሳኤ ትምህርት ነው:: ይኸውም ትንሣኤና ህይወት እኔ ነኝ ያለውን ጌታ በማመን የሚገኘውን የክብር ትንሣኤና የዘላለም ህይወት:: የዳንኤል መጽሐፍም ከብዙ ዘመናት በፊት ይህንኑ አስቀድሞ ይገልጣል:: ምንም እንኳን በዚህ ምድር እየሆነ ባለው ሁኔታ ብዙ ብንፈተንም ነገር ግን ትንሣኤ ሙታን ደግሞ ከጌታ ጋር አብሮ መገለጥ የመሆኑ ተስፋ ፅኑ ነው:: በፈተና ውስጥም የሚያ ፅናንና የሚያበረታን የነፍሳችን መልሕቅ ነው::
እግዚአብሔር ቸርና መልካም አምላክ ነው:: የሚያይና የሚሰማ ደግሞም የሚናገር ነው:: ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ በምናልፍበት ሁኔታ ውስጥ የሚያፅናና ደግሞም ለፀሎታችን መልስ የሚሆን ድምፁን ከማሳየት ይዘገያል:: በራሱ ጊዜ የከበረውን ሀሳቡን እስከሚገልጥበት ሰአት ድረሰ አና እንዲሁም ነገን ሊናገረን ሲፈልግ ዛሬ ዝም ይለናል:: የእግዚአብሔር መዘግየት በራሱ ጊዜ ሊገለጥ ካለው ነገር ጋር የተያያዘና ደግሞም ከእምነትና ከህይወት ምስክርነት ነገ ሊሆን ካለው ነገር ጋር የተያያዘ ነው::
ሰዎች በሚያልፉበት ወይንም በድካማቸውና በውድቀታቸው ልንፈርድና ራሳችንንም ልናፀድቅ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም:: ፍርድ የእግዚአብሐር ነው:: እኛ ግን እግፈዚአብሔርን በመፍራትናበትህትና ልንኖር ያስፈልጋል:: እውነተኛ ነስሃ ልብን በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድና ዝቅ በማለት ይጀምራል:: ደግሞም መፀፀትና ማዘን ብቻ ሳይሆን ንስሃ አቅጣጫ መለወጥና የንስሃ ፍሬ ማፍራትን ይጠይቃል::
አንዳንድ በህይወታችን የሚያልፉ ሁኔታዎችና ነገሮች በማስተዋል ከመረመርናቸውና ካዳመጥናቸው ወደ ጌታ አንድንመለስ የሚናገሩ መልዕክቶች ናቸው:: መመለስ ዋጋ ያሰከፍላል ነገር ግን በረከትና ፈውሱ ብዙ ነው:: መመለስ ከልብ ወደ ጌታ ሀሳብ ወደ ጌታ ፈቃድ መመለስ ነው:: ከጌታ ርቀን ዙሪያችን ሰላምና ደሰታ ቢመስለን አንታለል:: ለጊዜው ሰለሆነ:: እግዚአብሔር ግን እንድንመለስ በተለያየ ሁኔታ ድመፁን ሲያሰማን ደግሞም ሲጠብቀን ለአሁን ህይወታችን ደግሞም ለዘላለም ለሆነው ሰላምና ደሰታ ነው::
በአማኝ ህይወት መንፈሳዊ ውጊያ የሚጀምረው ጌታ ኢየሱስን ህይወቱ ካደረገበትና መንፈሳዊ ሰው ከሆነበት ቀን ጀምሮ ነው:: የእያንዳዳችን የመንፈሳዊ ውጊያ የጦርነቱ ምክንያትና ደረጃ እንዳየለንበት መንፈሳዊ እድገት ደረጃ ይለያያል:: *** በዚህ ትምህርት በመንፈሳዊ ህይወታችን ለምን እንደምንፈተን የፈተና አይነትና ከፈተና መውጫውም እንዴትና በምን እንደሆነ እንማራለን::
በእግዚአብሔር ፊት ተቀብሎት (ሞገስ) ያገኘነው በፊቱ እናመልከውና እናገለግለው ዘንድ ወደ እግዚአብሐር ፊት ካስገባን ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳ ነው:: እለት እለት መውጣትና መግባታችን በእርሱ ሞገስ ነው:: *** በእርሱ ፊት ሞገስ ያገኘ እርሱ:- - እግዚአብሔር ለሰላሙ ይጠነቀቅለታል:: - ቢፈተንም በአሸናፊነት ወደ ፊት ይሄዳል:: - በጨለማው ላይ እግዚአብሔር ትዕዛዝ ያወጣለታል:: - መነገዱ ሁሉ በፅድቅና በእውነት ይሆናል::
ወንጌል:- - ከሰው ልጅ ውድቀት ጀምሮ ረጅም ዘመናትን የተሻገረ የእግዚአብሔር የማዳን ሀሳብ ነው:: - የእግዚአብሔርን የማዳን ሀሳብ የምስራች እንደያዘ እንደዚሁ ደግሞ ፍርድንም የሚናገር ነው:: - ለሰው ሁሉ የሆነ ሁሉን ያካተ ለኃጢአተኛ የተሰጠ ነው:: *** ወንጌል አንዱን ጌታና አዳኝ እየተናገረ ነገር ግን የተለያዩ ስሞችን ይዟል:: ከእነዚህም ውሰጥ:- - የእግዚአብሔር ወንጌል , የክርስቶስ ወንጌል , የመዳን ወንጌል , የፀጋ ወንጌል , የትነሳኤ ወንጌልና የዘላለም ወንጌል ሌሎችም:: *** በዚህና በሚቀጥሉት ተከታታይ ትምህርቶች ዝርዝር ሀሳቦችን እንማራለን::
እግዚአብሔር ሁልጊዜ ከህዝቡ ጋር ነው:: የልመናቸውንም ድምፅ ይሰማል ይመልሳልም:: ነገር ግን አማኝ አንዳንድ ጊዜ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለፀሎቱ መልስ የማያገኝበት ደግሞም የጨለማ መንገድ በሚመስል ሁኔታ ውስጥ ያልፋል:: ይሁን እንጂ አሁንም በእግዚአብሔር መታመን ደግሞም በትዕግስት መጠበቅ ያስፈልጋል:: ጌታ የሚምር የሚራራም ነውና በራሱ ጊዜና ሁኔታ ይመጣል ይገለጣልም:: እግዚአብሔርን ከመጠበቅና በእርሱም ከመታመን ይልቅ የራሳችንን አማራጭ መውሰድ ፍፃሜው ምሬትና ድካም ኪሳራም ይሆናል::
የክርስቶስ ባለጠግነትና ሁሉን ቻይነት ለሰው ሁሉ የተገለጠው በወንጌል ነው:: በዚህም ወንጌል ሰውን ሁሉ ኃጢአተኛ እንደሆነ የሚያሳየው የእግዚአብሔር ፅድቅ ደግሞም እግዚአብሔር የሁሉ አምላክና ጌታ እንደሆነና ለሁሉ የሆነውም ምህረቱ ተገልጧል:: *** ሰው ከኃጢአተኛ ማንነቱ በፀጋው ነፃ ሊወጣና ሊቀደስ ይገባዋል:: እንዲሁም ደግሞ ለክፉ ተግባሩ ከጌታ ዘንድ ምህረትን ሊቀበልና ሰላምን ሊያደርግ ይገባዋል:: ይህም ስለሆነ ወንጌል ለኃጢአተኛው ፅድቅን እነዲሁም ቅድስናንና ሰላምን ያውጃል::
በወንጌል የተገለጠው አንዱና ዋናው የእግዚአብሔር ፀጋ ነው:: ይህ ፀጋ ከኃጢአተኝነት ነፃ የሚያወጣ ብቻ ሳይሆን በዚህም ምድር የሚያኖርም ነው:: ሰለዚህ ከወንጌል የተነሳ በዚህ አለም ያሉትን ሰዎች ለሁለተ ከፍሏል:: በራሳቸው ጥረትና ግረት የሚኖሩ እኔ ሰራሁት አደረኩት የሚሉ የዚህ አለም ልጆች እና ከእኔ ምንም የሆነ የለም የሚሉ በፀጋው የሚኖሩ አማኘ:: *** እግዚአብሔር ራሱን የገለጠው በወንጌል አማካኝነት ነው:: ስለዚህ በወንጌል በኩል እግዚአብሔር ሳይበራለት እግዚአብሔር ቢል የራሱ መረደት እንጂ በመንፈስ የሆነ መገለጥ አይደለም:: *** የአማኝ መንፈሳዊ መረዳት መጠኑ በአዕምሮው ላይ ባለው እውቀት ሳይሆን በወንጌሉ ፀጋ የበራለትን ያህል ነው"
አማኝ ሁልጊዜ ሊረዳውና ላይዘነጋ ከሚገባው ነገር አንዱ ካለበት የከበረ ህይወት ሊያወጣው ወደ ቀደመው የጨለማ ህይወት ለማስገባት የሚጎትት የሚፈትን ጠላት እንዳለው ነው:: በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ወደ ዘላለም ህይወት ወደ መንግስቱም ገብተናል:: ልጆቹ የተስፋውም ወራሾች ሆነናል:: ይህንንም በማመን አዲስ ፍጥረት ሆነናል:: ይህ ደግሞ ታላቅ መዳን ተብሎ ተጠቅሷል:: የአማኝ ትምክህትም ይኸው ነው:: አንዳች የጎደለን እንዳለ እያሳየ ወደኃላ የሚጎትተን እንዳይኖር እንጠንቀቅ:: ታላቅ ብድራት ያለውንም ድፍረታችንንና ትምክህታችንን አናቃልል::
ስፍራውን ለማስለቀቅ በአማኝ ህይወት ዙሪያ ብዙ የሚያስጨንቁና የሚያናውጡ ነገሮች ይኖራሉ:: ይሁን እንጂ ሰው እግዚአብሔርን እንዳወቀ በእርሱም እንደታመነና እንደተመካ ደግሞም እንዳረፈ የእምነቱ መጠን የሚለካው በጊዜውም አለጊዜውም በስፍራው ፀንቶ መጠበቁ ነው:: በስፍራው በጌታ ዐጋ ፀንቶ የቆመ እርሱ የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ ይሆናል:: ደግሞም አርሱ ለቤቱና ለሀገሩ ለትውልዱም የሚተርፍ ይሆናል:: *** ሰፍራችን በሆነበት ቦታ በዛ በእግዚአብሔር እጅ ተይዘናል::
መለኮታዊው ነገር ከላይ የሆነ ደግሞም መንፈሳዊ ከመሆኑ የተነሳ የሰው አውቀት ሊደርስበት አይችልም:: በቀላሉም ሊረዳውና ሊቀበለው የማይቻለው እውነት ነው:: ሰለዚህ የአማኝ መንፈሳዊ ከፍታ ኢየሱስን ያወቀውንና ለቃሉም በእምነት የታዘዘውን ያክል ነው:: *** እግዚአብሔርን ደግሞም የቃሉን እውነት ሰምተው ለሚያምኑትና ለሚታዘዙት ለእነርሱ ወደ ፊት የሚራመዱበት ጉልበት ያገኛሉ:: ለሌሎችም በረከት ይሆናሉ::
የእግዚአብሔር ፈቃድ ሰው ከመንገዱ ይመለስና ለፈጠረው አላማ ይኖር ዘንድ ደግሞም የይድን ዘነድ እንጂ ሰው ይጎዳ ደግሞም ይጠፋ ዘንድ ፈቃዱ አይደለም:: እኛ የእግዚአብሔር የባህርዩ ተካፋዮች ነንና ከእኛ ዘንድ አንድ ነገር ማየት ይፈልጋል:: ምህረት ማድረግን:: ከምህረት የጎደለ እርሱ ከእግዚአብሔር ጋር መራመድ አይችልምና:: *** አካሔዳችንን መመርመር የየእለት ተግባራችን ሊሆን የተገባ ነው::
አማኝ እግዚአብሔርን ለመምሰል ደግሞም እግዚአብሔርን እንደ ቃሉ ወደ ማወቅ ማንነት ያድግ ዘንድ የሚሰራበት መንገድ አንዱ የእግዚአብሔር መዘግየት ነው:: በእግዚአብሔር መዘግየት ውስጥ ትክክለኛው ማንነትችን ደግሞም ያለን መንፈሳዊ ደረጃና መረዳት ደገለጣል:: በእግዚአብሔር መዘግየት ውስጥ ትዕግስትንና ትህትናን ዝቅ ማለትን እንማራለን:: *** በእግዚአብሔር መዘግየት ውስጥ በምስጋና ሆነው በትዕግስት የሚጠብቁ እነርሱ በፀጋው ውስጥ ናቸው:: ነገር ግን ከምስጋና ርቀው በማጉረምረም ያሉ እነርሱ ከፀጋው የወጡ ናቸው::
የወንጌል ዋና ተልዕኮ ሰዎችን ከተበላሸ አካሄድ ማረም ወይም ማስተካከል አይደለም:: እንዲሁም ፈውስና ተአምራቶች ምልክቶች እእጂ ዋና ነገር አይደሉም:: የወንጌል ዋና ተልዕኮ ወይም ትኩረት ሰለ ህይወት ነው:: ይህም ህይወት ወደ ሰው ሁሉ የመጣው ሊቀበለውም የተገባው ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው:: *** ኢየሱስ:- ከሞት ፍርሀት ያድናል - ከዘላለም ፍርድ ያድናል - ከጨለማ ፍርሀት ያድናል - ከዚህ አለም ያድናል - ከኃጢአት ያድናለ - ከዘላለም ሞት ያድናል::
እሺታና እምቢታ በሰው ህይወት ውስጥ የሚታዩና የማነነታችን አንዱ መገለጫ የሆኑ ተቃራኒ ነገሮች ናቸው:: እምቢታ የኃጢአት የአመፅና የእልከኝነት ፍሬ ነው:: እሺታ ግን ከእግዚአብሔር የሆነና ሰውን ወደ በጎና መልከም ወደሆነ መንገድ የሚመራበት ነው:: ዳዊት " በእሺታ መንፈስ ደግፈኘ" ብሎ እንደፀለየ:: የእኛን እሺታ የሚፈልጉ ነገሮች በእኛ ሚዛን ሲመዘኑ ፈፅሞ ስፍራ የማንሰጣቸው የተናቁ ሊሆኑ ይችላሉ:: ነገር ግን እሺ ብለን ብንታዘዝ ለፈውሳችንና ለበረከታችን መለቀቅ ምክንያቶች ሊሆኑ ይችላሉና:: ንዕማን እሺ ብሎ እርሱ በናቀው ውሃ ውሰጥ ገበቶ ፈውሱን እንደተቀበለ:: *** ነገሮች በእኛ ፊት የተናቁና ክብደት የሌላቸው ወይንም ደግሞ አሰፈሪዎችና እንዴት ይሆናል የምንለው ቢሆን እንኳ የእኛን እሺታ እሰከፈለጉ ድረስ በጌታ ፀጋ ልንዘረጋ የተገባ ነው::
በአማኝ ህይወት ውስጥ ወንጌል እየበራ አየጨመረ ሲመጣ እኔ ከሚለው ከማንኛውም መመካት አውጥቶ በእግዚአበሔር ወደ መታመንና መመካት ፈፅሞ ሁሉን በእርሱ ላይ ወደ መጣል ከፍታ ያደርሰዋል:: የሰማነውና ወደ ዘላለም መንግስት የጠራን የወንጌል እውነት በእኛ ዘንድ ፀንቶ ፍሬ ይታይብን ዘንድ በመንፈስ ቀዱስ ሀይል በብዙ መረዳት በፀጋው ልናድግ ያስፈልጋል::
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱና በትንሣኤው በማመን ወደ መንግስቱ የገባን ሁላችን የልጁን መልክ ልንመስል የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው:: እውነተኛ ተከታይነታችንም በቃልና በስራ ሊገለጥ የተገባ ነው:: *** ጌታ በመከራ ሁሉ እንደታገሰ በክፉ ፈንታ ክፉንም እእዳልመለሰ እንዲሁ በእኛም ህይወት ይህና ሌሎችም የጌታ ባህርያት ሊንፀባረቅ ያስፈልጋል:: *** ፈፅሞ ጌታን መከተል ዋጋ የሚያስከፍል ለስጋም የተመቸ እንዳልሆነ የተገለጠ ነው:: ነገር ግን ከጌታ ዘንድ ለዚህ የሚሆን ፀጋና ሽልማት እንዳለው በማየት በታማኝነት ልንከተል ይገባል::
እግዚአብሔር ሊሰራ ያለውን የማዳን ስራ አስቀድሞ ተስፋን የሰጠበትና በአባቶች እንዲሁም በነቢያቱ የተናገረበት እርሱ የተስፋ ወንጌል ወይም የእግዚአብሔር ወንጌል ተብሎ ይጠራል:: ይህ የተስፋ ወንጌል ደግሞ የተፈፀመበትና ማዳኑ የተገለጠበት እርሱ የክርስቶስ ወንጌል ተብሎ ተጠርቷል:: ስለዚህ ሰው ሁለቱንም በመስማት ሙሉ ሊህን ይገባዋል:: *** በዚህ ትምህርት ይህንን እና ከዚሁ ጋር ተዛማጅ የሆኑ ሀሳቦችን በጥልቀት እንማራለን::
የዛሬው ጥያቄዎች 1. ስለምንወስደው ዕብስትና ፅዋ (የጌታ ሥጋና ደም) 2.የክርስቶስ ደም ለእኛ የሠራው ሥራ 3.እየሱስ ሕዝቡን በደሙ መቀደሱና በበር ውጭ መከራን ስለመቀበሉ
የመጀመሪያው የወንጌል መልዕክት ለእግዚአብሔር መኖር ነው:: እስራኤል ከግብፅ ሲወጣ እግዚአብሔርን ሊያመልክና ለእርሱ ሊኖርም እነደሆነ ሁሉ ሰው በክርስቶስ በማመን ከአለም ሲወጣ በፀጋው ለጌታ እንዲኖር ነው:: *** እግዚአብሔር በምህረቱ ባለጠጋ ስለሆነ ከሰው ጋር ይኖራል:: ሰው ደግሞ በፀገው ወደ እግዚአበሔር የሚቀርብ ሆነ::: ይህም ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ተከናውኗል:: እግዚአብሔር በምህረቱ በክርስቶስ ወደ እኛ መጥቷል:: ፅድቅና በጎነት የሌለን እኛ ደግሞ በክርስቶስ በፀጋው ወደ እግዚአብሔር ቀርበናል:: *** አማኝ ሁሉ ይህ የወንጌል ዕውቀት ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ደግሞ ሁልጊዜ የሚያነቃቃና ስላልዳኑት የምስክርነት ትጋት የሚሰጠን የዚህ የወንጌል መንፈስ ሊኖረን ይገባል::
ከሰው በህርይ አንዱ ዛሬ ላይ ቆሞ ሰለ ነገ ማሰብና መጨነቅ ነው:: አማኝ ግን ጌታን ከፊቱ ያሰቀድማል:: እግዚአብሔር ከፊት የሚቀድምለት አረሱ በጌታ ፈቀድ የተሞላ እርሱንም የሚፈልግ ደግሞም በፈቃዱ የወጣና የሚመራ ነው:: ሰለዚህ በነገር ሁሉ ጌታን ይጠብቃል ደግሞም የሰቀድማል::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ቅባት ምንድን ነው? በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ እና ሙላት ምን ማለት ነው? 2. ቤተ ክርስትያን የጌታ መንግሥት መገለጫ ናትን? 3. በጌታ ኢየሱስ ስም መጠመቅ ምን ማለት ነው? 4. በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት እንዴት ነው መጸለይ ያልብን?
ሰው ኃጢአተኛና ከእግዚአብሔር ክብር የጎደለ ከመሆኑ የተነሳ በራሱ መልካም መሆንና ጽድቅንም መፈፀም አይችልም:: ሰለዚህ የሆነውና እያደረግንም ያለው በጎና መልካም ነገር ሁሉ ሁኑ ካለን ደግሞም እንደፈቃዱ እንድንሆን የሚረዳንን ፀጋ ከሰጠን ከእግዚአብሔር ነው:: ጌታ የበዛውን ኃጢአትና ድካማቸንን አልፎ ነው የረዳን ነፃ ያወጣን:: አግዚአብሔር በእኛም ህይወት ይህንን ለሌሎች መሆንን መድረስን ማየት ይፈልጋል:: ከእግዚአብሔር የተቀበልነው ደግሞም ወደ ፊቱ በቀረብን ጊዜ ሁሉ የሚሰጠን ፀጋ የልጁን መልክ እንድንመስል የሚያሰችል ፀጋ ነው::
አማኝ በዚህ ምድር ሲኖር የሚኖርለት ምክንያት አለው:: በሚገባን ደግሞም በማይገባን ሁኔተ እግዚአብሔር ወዳየልን ልናከናውን ራሱንም በእኛ ሁኔታ ሊገልጥ ወደ ወደደው ወደ ተጠራንበት ሊያደርሰን ወደመሆንም ያመጣናል:: የምናልፍበት ሁኔታ እኛ ያለመረጥነው ደግሞም ያልተጠባበቅነው ሊሆን ይችላል:: ይሁን እንጂ ሀጢአትና አመፅ የሌለበት እርሱ እኛ የምንሰራበት ወደ ፈቃዱና ሀሳቡ ለመድረስ የምነጓዘበት ነው::
እግዚአብሔር ይናገራል:: መናገር አንዱ ባህርይው ነውና:: ነገር ግን ሲናገር በራሱ መንገድ ደግሞም በወደደው መንገድ ነው:: ምናልባት የምናልፍበትንና ጌታ እንደተናገረን ራሳችንን በእግዚአብሔር ፀጋ ውስጥ ስናይ ፈፅሞ የማይገጣጠም ነገር ሊሆን ይችላል:: ይሁን እንጂ እግዚአብሔር የተናገረውን በህይወት ሒደት ውስጥ ይፈፅማል:: *** እግዚአብሔር የተናገረውን ለመፈፀም የኛን አብሮ መራመድና በእርሱ መደገፋችንን ይፈልጋል::
እግዚአብሔር ለላቀ ክብር የለያቸው ሌዋውያን በምድረ ርስት የተካፈሉት ርስታችን የሚሉት መሬት አልነበረም:: እግዚአብሔር እርሱ ራሱ ርስታችሁ እኔ ነኝ::ብሏቸዋልና ለጌታ ለመሆን ከወሰንበት ቀንና ሰአት ጀምሮ የእኛ እድል ፈንታ ርስታችን አርሱ ራሱ ጌታ ነው:: በዚህ ምድር ተስፋ የምናደርገውና የምንናፍቀው ነገር የለንም:: ይሁን እንጂ ይሄና ያ ጎደለብኝ ብለን የምናማርር የምናንጎራጉርም ከሆነ የርስታችንን ክብርና ታላቅነት አጥርተን እንዳላየን ያመለክታል:: አማኝ በዚህ ምድር እንደ መፃተኛ ሊኖር ደግሞም ተስፋው የከበና የታመነ እንደሆነ በቃልና በኑሮ እየመሰከረ ሊኖር የተገባ ነው::
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰራውና የገለጠው መዳን እጅግ ታላቅ ነው:: ሰው በራሱ ጥረትና ድካም የሚያገኘው ሳይሆን እንዲሁ በፀጋው በነፃ የሚቀበለውና የሚቀደስበት የሚኖርበትም ድንቅ ስጦታ ነው:: *** የአማኝ ድፍረት በመስቀሉ ላይ የተሰራው የደህንነት ሥራ ነው:: ከሞት ወደ ህይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን የመጣበት ደግሞም በእግዚአብሔር ፊት ያለነውርና ያለነቀፋ ሊቆም የቻለበት:: *** ይህ ታላቅ መዳን አለንና ሁልጊዜ ራሳችንን ከአለም እድፍ እየጠበቅን በእርሱ ላይ ያለንን ድፍረት ሳንጥል በፊቱ በእምነት ፀንተን ልንቆም የተገባ ነው::
እግዚአብሔር እንደ ተስፋ ቃሉ እንደተናገረውም ነው:: ይሁን እንጂ አማኝ ብቻውን እእደሆነና ችግሩና እርሱ ብቻ የተፋጠጡ ተስፋ የሰጠውም ጌታ በአጠገቡ እንደሌለ እስኪሰማው ድረስ በታላቅ ፈተና ውስጥ አንዳንድጊዜ ሊያልፍ ይችላል:: ጌታ ደቀመዛሙርትን ወደ ማዶ እንዲሻገሩ ግድ ካለቸው በኃላ ራሳቸውን በታላቅ ማዕበል ውስጥ እንዳገኙት:: *** ይህ አይነቱ ጉዞ ጌታን ካወቅነው በላይ የምናውቅበት ደግሞም የሚያፀናና ወደ እምነት ከፍታ የሚያወጣንን ድመፅ የምንሰማበት የህይወት ጉዞ ነው:: *** እግዚአብሔር የተናገረን ይሆናል:: ጊዜውን የሚያውቅ እርሱ ነው ደግሞም በራሱ መንገድ ይመጣል:: እኛም እንደተናገረ አንዲሁ እንጠብቀው::
የእግዚአብሔር ህዝብ የእግዚአብሔር ምስክር ነው:: ማዳኑን ታላቅነቱንና ድንቅ ስራውን የሚመሰክር:: እግዚአብሔር እስራኤልን በድንቅና በተአምራት ከባርነት ነፃ ሲያወጣ የእስራኤል አምላክ ተብሎ ታላቅ ስሙ በህዝቡ ላይ ተጠርቷል:: በዚህ አለም የመኖራችን አንዱና ዋናው ምክንያት ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃኑ የጠራንን የማዳኑንም ሥራ ልንናገር በቃልና በሰራ ምስክር ልንሆን ነው:: ለዚህም የሚሆን የሚረዳ የሚያግዝ የእግዚአብሔር ፀጋ አለ::
በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ልጆች ላደረገን ለአኛ እግዚአብሔር ያወረሰን ርስት እርሱን ራሱን ነው:: ይኸውም የክብር ሙላት ያለው ጌታ ፀጋንና እውነትን ተሞልቶ በእኛ ማደሩ ነው:: አይኖቻችን ተከፍተው ያለን ርስት ክብሩና ታላቅነቱ ምን ያህል እንደሆነ ልናይ ያስፈልጋል:: ሐዋርያውም ሰለዚሁ ጉዳይ ነው እፀልይላችኃለሁ ያለው:: የክብር ተስፋ ያለው ጌታ ከእርሱ ጋር እንደሆነ አይኖቹ ተከፍተው ያየና የተረዳ አማኝ እርሱ በሚሞት ስጋ ውስጥ ቢሆንም ነገር ግን በሞት ላይ አሸናፊ ካደረገው ጌታ የተነሳ ከሞት ባሻገር ክብር በሞላበት የዘላለም መንግስት በክብር እንዲኖር ይረዳል:: ደግሞም በብዙ ችግርና ፈተና ውስጥ ቢያልፍም እንኳ ታላቅ ሰላምና ደስታን የተሞላ የእውነትም አገልጋይ የሆናል::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ወንጌልን ለስዎች እንዴት ነው ማድረስ የምንችለው? 2. በቅዱሳን ላይ ሽንፈት የሚመጣው ለምንድን ነው? 3. ወንጌልን ለመናገር ብዙ የቃሉ ሙላት ያስፈልጋል ወይ? 4. አማኝ በእድል መደገፍ ይችላል ወይ? 5. ፀጋ ተቀብለን ለሌሎች የምንሆነውና የማንሆነው እንዴት ነው?
የእግዚአብሔር ቃል ፀንታችሁ ቁሙ እንደሚል መቆም ማለት በጌታ ሆኖ እግዚአብሔርን የእኛ ማድረግ ማለት ነው:: ጌታን ደግሞ የእኛ ማድረግ ማለት በህይወታችን ሁሉ በመባትና በመውጣት ሁሉን በፀጋው ችሎት ማለፍ ማለት:: በመንፈሳዊ ጦርነት አንዱ ጠለትን ድል መንሻ መቆም ነው:: በሰላም ወንጌል ተጫምታችሁ ቁሙ ተብሎ እንደተፃፈ:: በእለት ተእለት ህይወታችን የምናልፍባቸው የተለያዩ ችግሮች ይኖራሉ:: ይሁን እንጂ እኛ የምንጠነክርባቸው በጌታ ሆነን የምንገለጥበት በእርሱ በፀጋው ችሎት መደገፋችን ::የሚታይበትነው::
የእግዚአብሔር ድምፅ ህይወት ነው:: የሚቀድስ የሚያጠራ ደግሞም የሚፈውስ ድምፅ:: ብዙ ግራ የሚያጋቡ የሚያውኩና የሚያስቱ ድምፆች እጅግ በበዙበት በዚህ ዘመን የጠራውን የጌታን ድምፅ ማግኘት መስማትም ዋና ነገር ነው:: እግዚአብሔር በአንድም በሌላ ነገር ይናገራል::የተናገረውም ደግሞ ይሆናል:: የሚከለክልም የለም:: ጌታ በእኛ ሁኔታ ሲናገር ምንም እንኳ በብዙ ፈተና ውስጥ ብንሆንም እንኳ ድምፁ ለህይወት ለፈውስና ለበረከት ነፃ ለማውጣት ይመጣል::
እግዚአብሔር ሂድ ውጣ አድርግም ብሎ በተናገረን ማንኛውም ነገር ስንታዘዝ ስንዘረጋ እርሱ ቀድሞ ከፊት ነው:: ጨለማ ነው ተራራ ነው ባልነው እርሱ ይቀድማል:: ብርሃንና ደልዳላም ይሆናል:: የማይቻለውን እንዲቻል የማይሆነውን እንዲሆን ያደርጋል:: ከፊት ወጥቷልና:: *** የእግዚአብሔር ምክር ባለበት እርሱ ቀዳሚ ነው:: ጌታ ደቀመዛሙርቱን ወደ ማዶ ተሻገሩ ብሎ ሲልካቸው እርሱ ቀድሞ እንደተገኘ:: *** እግዚአብሔር ሲቀድም እርሱ ከኃላም ነው::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ለወንጌል ዋጋ መክፈል የምንችለው እንዴት ነው? 2. የሚመጡትን መልዕክቶችና የጌታን ድምጽ የምንለየው እንዴት ነው? 3. ወንጌልን ተቀብለን ለምን እንለወጥም? ከዚህስ ነገር እንዴት ነው የምንወጣው? 4. የጌታን ትእዛዝ እና አብሮነት እንዴት ነው የምናውቀው?
እግዚአብሔር ድንቅ መካር ነው:: የእግዚአብሔር ምክር ባለበት ህይወታችን የተጠበቀ ነው:: ከክፉውም የምንሰወረው ምክሩ ባለበት ነው:: ይሁን እንጂ ከዚህ ድንቅ መካር ጋር የሚያጋጥመን የሚያስማማን ደግሞም ተጠቃሚ የሚያደርገን ግን ተመካሪ ልብ ካለን ብቻ ነው:: *** መመከር ባላየነውና ባልጠበቅነው በኩል ያለውን እይታ እውቀት የምናገኝበት እድል ነው:: ደግሞም በመመከር ቤትን ለማቆም ከጉዳት ለመታደግ ከዚህ አልፎ ለሀገር ለህዝብ መትረፊያ ይሆናል::
በየትኛውም ዘመንና ጊዜ የሰይጣን ተቀዳሚ አላማ እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔር የሆነውን መተካት ነው:: ይህን ለማድረግ ደግሞ እጅግ ረቂቅ ደግሞም የተገለጡ ዘዴዷዎችን ይጠቀማል:: ይህን አሰራሩን ደግሞ የተቀበሉ እነርሱ የክፋቱ መጠቀሚየ ይሆናሉ:: የክፋት የረኩሰትና የሀሰት ምንጭ እርሱ ነው::ሰለዚህ አማኝን ማርከስ በክፋት መሙላት አመፀኛ ማድረግ ወዘተ ... የዘወትር ተግባሩ ነው:: ወደ እግዚአብሔር ያልተጠጋ በፀሎትም ያልተከደነ ለክፋቱ የተጋለጠ ይሆናል:: *** ሰይጣን እኛን በቀጥታ ማግኘት አይችልም:: የምናመልከው ጌታ ታማኝ ነውና ከጥበቃው አልፎ ወደ እኛ የሚመጣ ሊኖር አይችልም:: ነገር ግን ወደ ስጋዊነት ባመዘንንና ከፀሎትና ከቃሉ በራቅን ጊዜ ለሰይጣነ ጥቃት የተጋለጥን እንሆናለን:: ***ለአማኝ እግዚአብሔርን መፍራት ዋናው ከክፉ ሁሉ መጠበቂያው ነው::
መነፈሳዊ ጦርነት ሰይጣን ወደ አማኝ ህይወት ኑሮና ማንነት ከሚልከውና ሊፈፅም ከሚፈልገው ክፉ ስራው ጋር መጋጠም ነው:: ሰይጣን ክፉ የሆነ ስራውን አላማውን ለመፈፀም ለማሳካት የተለያዩ መንገዶችን ይጠቀማል:: በሚያሰፈራና በሚያስጨንቅ ሁኔታ ወይም ደግሞ መልካም በሚመስል በሚሸነግል ማታለያ መንገድ ይመጣል:: *** የሰይጣን የመጀመሪያውና ዋናው ውጊያው ከህልውናችን ጋር ነው:: ለሰይጣን ትልቁ ችግር የክርስቲያን መኖር ሰለሆነ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ አማኝን ማጥፋት ተቀዳሚ አላማው ነው:: *** አማኝ መንፈሳዊ በሆነ ጊዜ ሁሉ ጌታ እነደሚጠቀምበት ስጋዊ በሆንን ጊዜ ደግሞ ለሰይጣን ክፉ ሀሳብ መጠቀሚያ እንሆናለን:: የእግዚአብሔር ቃል እነደሚመክረን በአዕምሮአችን መታደስ ልንቀደስ ደግሞም ዘወትር መንፈሳዊ ልንሆን ዋናና አስፈላጊ ጉዳይ ነው::
ሰው እግዚአብሔርን በፅድቅና በቅድስና እንደ ቃሉ የሆነ ህይወት አእንዳይኖር ለማሰናከል በአምላኩም ላይ እንዲበድል ዘወትር ያለ እረፍት የሚተጋ ጠላት አለበት:: አርሱም የፅድቅ ጠላት አሳች የተባለው ሰይጣን ነው: አማኝ ዘወትር ራሱን በጌታ ውስጥ እንደሆነ እርግጠኛ ሊሆን ይገባል:: ሰይጣን እኛን ለማሳት ለመዋጋት በርና እድል ፈንታ የሚያገኘው ራሳችንን በጌታ ውስጥ ሆነን ባልተገዛንበት በኩል ነውና:: አማኝ በእግዚአብሔር ቃል አዕምሮው ካልተቀደሰና ነፃ ካልወጣ በመንፈስ ቅዱስም ህይወቱ ካልተያዘ ለሰይጣን ፍላፃና ለስህተት አሰራሩ የተጋለጠ ይሆናል:: *** ክፉው እኛን የሚፈትንባቸውና የሚዋጋባቸው መንገዶች:- - እግዚአብሔርን በምንበድልበት በኩል - በምንታበይበትና በምንዳፈርበት በኩል - በምንፈራበትና በምንሰጋበት በኩል - ቃሉን ባዛባንበትና በእምነት ባልቆምንበት በኩል ... ወዘተ ነው:: ሰለዚህ እግዚአብሔርን በመፍራት በፀጋው ችሎት ችግራችንን ማወቅና ባወቅነው ችግርም ላይ እርምጃ ልንወስድ ይገባል::
ሰው እግዚአብሔርን በፅድቅና በቅድስና እንደ ቃሉ የሆነ ህይወት አእንዳይኖር ለማሰናከል በአምላኩም ላይ እንዲበድል ዘወትር ያለ እረፍት የሚተጋ ጠላት አለበት:: አርሱም የፅድቅ ጠላት አሳች የተባለው ሰይጣን ነው: አማኝ ዘወትር ራሱን በጌታ ውስጥ እንደሆነ እርግጠኛ ሊሆን ይገባል:: ሰይጣን እኛን ለማሳት ለመዋጋት በርና እድል ፈንታ የሚያገኘው ራሳችንን በጌታ ውስጥ ሆነን ባልተገዛንበት በኩል ነውና:: አማኝ በእግዚአብሔር ቃል አዕምሮው ካልተቀደሰና ነፃ ካልወጣ በመንፈስ ቅዱስም ህይወቱ ካልተያዘ ለሰይጣን ፍላፃና ለስህተት አሰራሩ የተጋለጠ ይሆናል:: *** ክፉው እኛን የሚፈትንባቸውና የሚዋጋባቸው መንገዶች:- - እግዚአብሔርን በምንበድልበት በኩል - በምንታበይበትና በምንዳፈርበት በኩል - በምንፈራበትና በምንሰጋበት በኩል - ቃሉን ባዛባንበትና በእምነት ባልቆምንበት በኩል ... ወዘተ ነው:: ሰለዚህ እግዚአብሔርን በመፍራት በፀጋው ችሎት ችግራችንን ማወቅና ባወቅነው ችግርም ላይ እርምጃ ልንወስድ ይገባል::
ካሌብ በእግዚአብሔር ላይ ፍፁም የሚደገፍ ራሱንና አካባቢውን ወይም ሁኔታን ሳይሆን የተደገፈውን የእግዚአብሔርን ብርቱ ክንድ ብቻ የሚያይ ሰው ነው:: ስለዚህም ከስለላ መልስ በከተማይቱ ውስጥ ካያቸው ረጃጅምና ሀያላን ሰዎች ይልቅ በህዝቡ ሁሉ ፊት ታላቅና የሀያላን ሀያል የሆነውን አግዚአብሔርን ሲያውጅ እናያለን:: የምናልፍበት ሁኔታ የሚያደክመን የያዝነውን ተስፋ ሊያስለቅቀን የሚታገል ቢሆን እንኳ በእምነት ፀንተን ተስፋችንን መያዝ ደግሞም አለመናወጥ የምንችለው ብርቱ የሆነውን ጌታ በማየትና ታላቅነቱንም በሚያስጨንቀን ሁሉ ላይ በማወጅ ነው:: እግዚአብሔር በልጁ ወደ ገለጠልን ሙሉ በረከት እንገባ ዘንድ መነገዱ ይኸው ነው:: በነገር ሁሉ ውስጥ ጌታን ማየት በፍፁም ልብም እርሱን መከተል:: ብንደክምም እርሱ ሀይልና ብርታት ይሆንልናል:
በማንኛውም ሰአትና ቦታ የምንናገረውንና የምናደርገውን ካልተጠነቀቅንና በእምነትና በፀሎት ከእውቀትና እንደ እግዚአብሔር ቃል ካልሆነ ለጠላት ፍለፃውን መወርወሪያ ምክንያት ለውጊያውም ሜዳ ያገኛል:: *** ከእኛው ወጥቶ እኛን ራሳችንን የሚዋጋበት መንፈሳዊ ጦርነት :-- -- እንደበራልን ካልተናገርን -- በመንፈስ ቅዱስ ካልተከለልንበት -- በመሰለን ከጌታ ቃል ያልሆነ በተናገርንበት -- መራራነት ተሞልተን በተናገርንበት -- ከፀሎት በፊት የፍርድ ቃል በተናገርንበት -- ተቃራኒ ነገርን ባሰብንበት እና ልባችንን ባጠነከርንበትና ሌሎችም... በዚህ ትምህርት በጥልቀት አንማራለን:: በምንሰማውና በምናየው ነገር በመጀመሪያ በውስጣችን ብቅ የሚለው እርሱ የእኛነታችን ትክክለኛው መገለጫ ነው:: በመጀመሪያ በውሰጣችን ሊከብድ የሚገባው ምህረት ነው:: ይቅርታና ሰላም ያለበት ፍቅርና በጎነት ያለበት ነው:: ከእነዚህ ተቃራኒ ከሆነ ጠላት የሚጠቀምበት ሰለሆነ ልነጠነቀቅ ይገባል::
በኢየሱስ ክርስቶስ በማዳኑና በፀጋው የተካፈልነው ህይወትና ኑሮ ታላቅ ብድራት ያለው በእውነትና በፅድቅ ደግሞም በጥንቃቄ ልንኖረው ልንጠብቀውም የሚገባ ነው:: በክርስትና እምነት ውስጥ ካሉት ታላላቅ እውነቶች አምስቱን በዚህ ትምህርት እንማራለን:-- - መዳናችን እጅግ ታላቅ ነው:: ከሞት ወደ ህይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የመጣንበት:: - የጌታ እረኝነት:: ነፍሱን ሰለ በጎቹ አሳልፎ የሰጠ መልከምና ታላቅ እረኛ:: - የጌታ የሊቀ ካህንነት ሥራ:: ፍፁም የሆነ የዘላለም ሊቀካህን:: - ታላቅ ብድራት:: ጌታን በማመን የምናገኘው ብድራት እጅግ ታላቅ ነው:: - ታላቅ መጋደል:: በነፃ የተቀበልነው የክርስትና ህይወት ታላቅ መጋደል ያለበት መፅናትንም የሚጠይቅ ነው:: ክርስቶስ የሰራውና እኛም የእርሱ የሆንበት ነገረ እጅግ ታላቅ ነውና ከዚህ ሌላ ተመክህት አይኖረንም:: ሰለዚህ ትምክህታችንን አንጥልም ብድራቱ እጅግ የላቀ ነውና::
እግዚአብሔር ሰውን ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃኑ ወደ ልጅነት ያመጣው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱና በትንሳኤው ነው:: ይህም የዘላለም ተስፋ አስተማማኝነቱ በራሱ ችሎት የተሰራ በመሆኑ ነው:: እውነተኛ መንፈሳዊ ህይወት እግዚአብሔር ወዳቀደልን ልጁን ወደ መምሰል እንድናድግና በምድርም ላይ የእርሱ ምስክር እንድንሆን የምንኖረው እንጂ በዚህ አለም ማትረፊያ እንዲሆነን አይደለም:: - የተቀበልነው አዲሱ ህይወት በአለም ካለው ክፋት ጋር መደበላለቅንና አብር መቆምን አይፈቅድም::ይልቁንም በጨለማው ላይ የጽድቅና የእውነት ብርሃን እያበራን የምንኖርበት ህይወት ነው:: - ህይወቱ በትጋት ደግሞም በፀጋው ችሎት የሆነ አማኝ ፍፃሜው የዘላለም መንግስት በክብር መሆን ነው:: ይህ ፍፃሜ ደግሞ አስተማማኝ ተስፋ ያለው ነው:: ሰለዚህ ከፊት ይልቅ አብልጠን እንትጋ:: ተስፋን የሰጠ እርሱ የታመነ ነው::
እግዚአብሔርን ጠብቆ የከሰረ ወይም ያፈረ ማንም የለም:: ነገር ግን የጌታ መምጫው በእኛ ሰአትና ፍላጎት ሳይሆን በራሱ ጊዜና ሰአት በወደደው ሁኔታ ነው:: በመጠበቅ ውስጥ ብዙ ፈተና ደግሞም የጠላት ውጊያ አለ:: በስፍራችን ሆነን እንዳንገኝ የሚዋጋ ጠላት:: ይሁን እንጂ ፀጋን የሚሰጥ ጌታ እርሱ የታመነ ነው:: እግዚአብሔር ባስቀመጠን ሰፍራ መገኘት በዛም ቆይቶ መጠበቅ ደግሞም ልንፈፅምና ልናከናውን የሚገባንን የእርሱን ፈቃድ በመፈፀም መገኘት ያስፈልጋል:: ዋጋችን በታመነው ጌታ እጅ ነው::
በረከት ማለት ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቶ በሰው ህይወት ኑሮና ዘር ላይ የሚገለጥ የእርሱ ቸርነት ነው:: ይህ የእግዚአብሔር ቸርነት በተስፋ ቃልና እንዲሁም ደግሞ አካሔዱን ከእርሱ ጋር ያደረገውን ሰው በመባረክ ይገለጣል:: በክርስቶስ አምኖ የዳነ ሰው በአንድም ወይም በሌላ ከራሱ ድካም ኃጢአትና በደል የተነሳ ሊፈተንና ተፅእኖ ውስጥ ሊገባ ቀንበርም ሊሆንበት ይችላል:: ነገር ግን እርግማን በአማኝ ላይ ፈፅሞ አይሰራም ደግሞም አይከተለውም:: ይልቁንም አማኝ ሊባርክ ተጠርቷል:: በረከት በክርስቶስ ኢየሱስ በአማኝ ራስ ላይ ነውና::
1.በጊዜ አገልግሎታችንን ካላደረግን ችግር አለው ወይ? 2. በአዕምሮ ላይ ያለው መንፈሳዊ ተፀዕኖ ምንድን ነው? 3.የጠላት መጠቀሚያ ላለመሆን ምን እናድርግ?
እግዚአብሔር አርሱ ቸር አምለክ ነው:: ቸርነቱም በረከት በመስጠት ይገለጣል:: የአማኝ በረከትም እግዚአብሔር እርሱ በሆነለት ነው:: እግዚአብሔር ሆነልን ማለት: እርሱ ሰላማችን ይሆናል ሀብትና እውቀታችንም ይሆናል ሀይልና ጉልበት ብርታታችንም የሆናል:: ሰለዚህ ለአማኝ በረከት ባከማቸው ሀብትና ባለው እውቀት ደግሞም በራሱ ትጋትና ሩጫ አይደለም ነገር ግን ለእርሱ ከሆነለት ከእግዚአብሔር ነው እነጂ:: የአማኝ በረከት እግዚአብሔር ባለው ውስጥ ደግሞም ከእርሱ በሆነው ነው::
1. ማቴ 26፡36 እነርሱ ቢተጉ ኖሮ ይሆን የነበረው ምንድን ነው? ነገሮች ይለወጡ ነበር? 2. እርግማን ከደኅንነታችን ጋር የተያያዘ ነው ወይስ ከበሽታችን ጋር ነው የሚያያዘው? 3. እኛ የጌታ ሆነን ልጆቻችን ሳይሆኑ መርገም ያገኛቸዋል ወይ? 4. 1ቆሮ 5፡5 “ሥጋውብ ለጠላት ይሰጥ” ሲል ምን ማለት ነው? ይህ መርገም ነው ወይ? 5. ዘፍ 12፡2 አብርሃም በረከት ለማግኘት ያደረገው የራሱ አስተዋፅኦ አለ ወይ? 6. የተሻረው እና ያልተሻረው ሕግ የትያው ነው? 7. ዘፍ 39፡5 ይህ በረከት እኛ በምንሠራበት ቦት ለሰዎች ይደርሳል ወይስ ለዮሴፍ ብቻ ነው? 8. ከእግዚአብሔር ውጭ የምናስበውን ጠላት ይጠቀምበታል የሚለው ምን ማለት ነው?
አማኝ ሁሉ በዚህ አለም ሲኖር መከራ አለበት:: ይሁን እንጂ በመለኮት ጥበቃ ውስጥ ሆኖ ነው:: የሚያፀናችሁ ከክፉም የሚጠብቃችሁ የታመነ ነው ተብሎ እንደተፃፈ እግዚአብሔር ህዝቡን በታማኝነት ይጠብቃል:: ደግሞም ይጠነቀቃል:: ክፉው የመለኮትን ጥበቃ አልፎ በእኛ ላይ ምንም ማድረግ ስለማይችል ክፉ መሻትን ወደ እኛ ውሰጥ በመወርወር በራሳችን ክፉ መሻት በመታለል እኛው ራሳችን በኃጢአት እንድንጠላለፍ ያደረጋል:: ያን ጊዜ በሁከት እንሞላለን ለወጥመዱም የተመቸን እንሆናለን:: እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር የሆነ አማኝ እርሱ በፈተና ውስጥ ቢያልፍ እንኳ በሰላም የተሞላ ነው:: የመለኮት ጥበቃ ከበራለት በላይ ጠላትንና አሠራሩን አቅልሎ የሚያይ የለም::
እግዚአብሔር ለዘላለም አይቆጣም እንደገና ይመለሳል:: ምህረትንም ያደርጋል:: ይፈውሳል ተስፋንም ያድሳል:: የረዘመች ተስፋ ነፍስን ታዝላለች እንደሚል ነፍሳችን ዝላ ተስፋ እንዳንቆርጥ የእግዚአብሔርን ባህርይ ማሰብ ይጠቅማል:: መሀሪነቱን ደግሞም የመመለስ የመፈወስና የመጎብኘት ጊዜ እንዳለው:: ይህን ማሰብ ሀይልና ብርታት ይሆንልናል:: - እርሱን በመምረጥ በትህትና ከልብ በመመለስ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ከህዝቡ ፊት እንባን ማበሱ አይቀርም:: - አንዳንድ ነገሮች በጣም የሚያስጨንቁ ነፈስንም የሚያዝሉ እስከመቼ የሚያስብሉ ይሆናሉ:: ነገር ግን ነውጡ ባየለ ጊዜ አዲስ ነገርን ሊያስከትል የእግዚአብሔርም ክንድ የሚገለጥበት ይሆናል::
በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ከዚህ አለም ከተያዝንበት ከጨለማው አሰራርና ከኃጢአት ከዘላለምም ፍርድ አምልጠን ወደ መንግስቱ ሲያፈልሰን በሚመጣው አለም ብቻ ሳይሆን ዛሬም በዚህ ምድር በሙላት ልንኖር የአግዚአብሔር ፈቃድ ነው:: በተሰጠን ማመስገንና መርካት ቀዳሚ ሲሆን ሌላው ደግሞ ፈፅመን ለጌታ ያላስገዛነውን ወይንም ያላስወረስነውን ማንነታችንን ልናይና ሙሉ በሙሉ ለእርሱ ልናስገዛ ይፈልጋል:: በጥቂቱ መታመን የበለጠውን ለመቀበል የመዘጋጀት ምልክት ነው:: የጌታም ፈቃድ ባለን ታምነን ሰለ ጥቂቱ እንድናመሰግን ነው:: እርሱ በጥቂቱ የታመነውነ በብዙ ይባርካልና::
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ወደ መንግስቱ እንድንገባ ብቃት ሆኖናል:: ደግሞም ወደዚህ ወደ ከበረው የዘላለም መንግስት መግባታችን በሙላት እንዲሆንም የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው:: - ወደ እግዚአብሔር መንግስት የገባንና የከበረ ተስፋ ያለን አኛ ሁልጊዜ ልናስብና በተግባርም ልንኖርበት የሚገባን አራት ዋና ዋና ምክሮችን በዚህ ትምህርት በጥልቀት እንማራለን:- 1 - ከቅዱሳን ጋር ያለንን አንድነት በመጠበቅ ፀጋን መካፈል:: 2 - ወደ ኃላ የሚጎትተንን ሸክምና ኃጢአት በየእለቱ በማስወገድ መሄድ:: 3 - እግዚአብሔርን በመፍራትና በማክበር በፍቅር በፅደቅና በቅደስና በሰላምም መኖር:: 4 - ከስህተት ትምህርት መጠበቅ:: ከተቀበልነው የከበረ ተስፋና እውነት ከሚያወጣና ከሚያዝል ከሚያደክም ትምህርት መጠበቅ:: የዳንበትንና የተመሰረትንበትን የእግዚአብሔር ቃል እውነት ጠንቅቀን ልናውቅ የከበረውንም ተስፋ አጥብቀን ልንይዝ ያስፈልግል::
እግዚአብሔር በህይወታችን ላለው አላማ ስንኖርና ሰንጓዝ ጉዟችንን ለማሰናከል ሰይጣን ወጥመድ ማዘጋጀገቱ የማይቀር ነው:: ይህ የእርሱ የአለት ተእለት ተግባሩ ነውና: ለወጥመዱ የምንጋለጠው ወይም ምቹ የምንሆነው :- - ብዙ ተመክረን ወይም ተገስፀን አንመለስ በልንበት በዛ ወጥመድ አለ:: - በችኮላ ባለማስተዋል ዘለን የምንገባበት ሁኔታ ለወጥመዱ ምቹ ነው:: - ያለ ንፅህናና ያለ ቅድስና ያለ እውነትና ያለ እምነት ባልሆንበት:: - ጌታን በርቀት መከተል እንዲሁም የማይገባ ክብርና ዝና ወደ ወጥመዱ ስበው ይከቱናል:: በህይወት ጉዟችን ከክፉው ወጥመድ የምንሰወረው ወይም የምናመልጠው :- - እግዚአብሔርን መፍራት ዋናው ከወጥመዱ ማምለጫ ነው:: - ለመንፈስ ቅዱስ ምቹ በሆንበት - ቅድስናና ፅድቅ በመረጥን ጊዜ አንዲሁም የቃሉን እውነት ትህትናን እና አውነትን...ወዘተ በመረጥን ጊዜ ወጥመዱን እናመልጣለን::
አማኝ ተስፋውን አፅንቶ እንዲይዝ ደግሞም በሰማው ህያው ቃል ላይ በእምነት መቆም ይሆንለት ዘንድ የመንፈሳዊ አይኖቹ መከፈት ዋና ነገር ነው:: መንፈሳዊ አይኖቻችን ሲያዙ:- - ኢየሱስን ከሙታን መንደር እንፈልገዋለን:: ህያውነቱ ይሰወርብናል:: - ከሰማነው ህያው ቃል እሩቅ እንሆናለን:: - በእምነት ሳይሆን ስጋዊ አይኖቻችንና እውቀታችን በሚመሩን ብቻ እንጓዛለን:: - ከአድናቆት ያለፈ ህይወት አይኖረንም:: - ተመራማሪ እንሆናለን:: አይንን የሚከፍት እርሱ ጌታ እግዚአብሔር ነው:: ከእውነተኛው መአድ በመካፈልና በመመገብ አይን ይከፈታል:: ወደ እውቀት ወደ መረዳትም ያመጣናልና::
አማኝ በህይወት ጉዞው ውስጥ ፍፁም በእግዚአብሔር ሥልጣን ስር መሆኑና መገዛቱ የሚገለጠው በመታዘዝ ነው:: መታዘዝ በሌለበት ህይወት አያልፍም:: የጌታ ኢየሱስ ህይወት ወደ ሚያምኑት ሁሉ ያለፈው ከመታዘዙ የተነሳ ነው እስከ መስቀል ሞት የታዘዘ ሆኗል :: እግዚአብሔር የተናገረው የበረከት ቃሎች ወደ ህይወታችን የሚያልፈው እለት እለት በታዘዝንበት በኩል ነው:: በአለመታዘዝ ምክንያት ወደ ህይወታችን ከመፍሰስ የቆመውን በረከት በፆምና በፀሎት ማግኝት አንችልም:: የእኛን መታዘዝ የሚጠይቁ ናቸውና በአለመታዘዝ ምክንያት እስራኤል በምድረ በዳ እንደቀሩ ሁሉ እኛም በዚህ መንገድ እንዳንሄድ ህያው ቃሉ ይመክረናል:: - ለጌታ የመገዛታችን ፍሬ መታዘዛችን ነው::
በአማኝ የህይወት ጉዞ ውስጥ ብዙ መሰናከል ብዙ ወጥመድ ብዙ ፍርሀት አለ:: ነገር ግን ወደ ፊት ሂዱ ደግሞም ተሻገሩ ያለ ጌታ እርሱ የታመነ ነው:: ያሻግራል:: አላሳልፍ ያለ ማዕበል ጌታ ሲመጣበት ፀጥታ ይሆናል:: ከማዕበሉ በላይ የሆነው ጌታ ይራመድበታል:: እኛንም ያራምዳል:: - መሻገር አይቀርም ጌታ ከእኛ ጋር ስለሆነ:: ነገር ግን ለመሻገር መመሪያ መጠበቅ የግድ ነው:: በራሳችን እውቀትና መንገድ መሔድ ወደ ኪሳራ ያመራል:: - ለመሻገር መቀደስና ራስን ለፈቃዱ ማስገዛት ደግሞም በእምነት መሆን የስፈልገናል::
1. አንድ አገልጋይ ፀጋው እንዲለቀቅ በተገለጠበት ፀጋ ብቻ መወሰን የለበትም ማለት ነው? 2. ከእግዚአብሔር የሚመጣውንና በአለመታዘዝ የሚመጣውን መከራ እንዴት እንለየዋለን? 3. የወደቀውን ለማንሳት የደከመውን ለማበረታታት ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? 4. ራሳችንን ለማግኘት ምን እናድርግ? 5. ከወጥመድ ለመውጣት ቃሉን ምንበብና መፀለይ አለብን ወይ?
በአማኝ ህይወት ውስጥ የእርሱ በረከት መጠኑና ስፋቱ ለሌሎች ለመሆን ለመትረፍ የመቻሉም ጥልቀቱ ያለው መታዘዙ ላይ ነው:: ሙሉ መታዘዝ:: ይኸውም ሰለ ጥቅም ወይም ከመታዘዛችን የተነሳ ስለምናገኘው ወይም ስለሚሆንልን የምንታዘዘው አይደለም:: ደግሞም ስለቀለለን የምንፈፅመው ስይሆን ነገረ ግን ራሳችንን ሰጥተነ የእግዚአብሔር ፈቃድና ሀሳብ በፀጋው በእኛ እንዲፈፀም የምንታዘዘው ነወ:: - መታዘዝ ዝቅ ማለት የእግዚአበሔር የአገዛዝ መዋቅር ነው:: ኢየሱስ እርሱ ከእግዚአበሔር ጋር እኩል ሥልጣንና ክብር ያለው ጌታ ሲሆን ሳለ ለአባቱ ያለው መታዘዝ የተገለጠው ራሱን ዝቅ በማድረግ ደገሞም እስከ መስቀል ሞት ድረስ በመታዘዝ ነው:: ውጤቱም እጅግ የከበረ ለሰው ሁሉ መዳን ምክንያት የሆነ ነው:: - በአማኝ ህይወት ውስጥ በረከት ፈውስና መፅናናት ወደ ህይወቱም ሆነ ለሌሎችም መትረፊያ መንገዱ በመታዘዙ ውስጥ ነው::
ሰው ትክክለኛ ማንነቱን ሊያይና ራሱን ሊያዋርድ የክርሽቶስን ህይወት እንዳይኖር መሰናክል የሆነውን በውስጡ ያለውን እርም ማስወገድ የሚችለው የእግዚአብሔር ብርሃን በበራለት መጠንና በብርሃኑ ውስጥ ራሱን ባየበት ልክ ነው:: ይህ ሲሆን ከማይበቃ ማንነታችን ውስጥ በእርሱ ፀጋ የሚበቃውን አዲሱ ማንነታችን ይወጣል:: አዲሱ ሰው የሚታዘዝ ነው:: አካሄዱ ከእግዚአብሔር ጋር ነውና:: የእርሱ ክብር ሞገስና በረከትም ያለው በመታዘዝ ውስጥ ነወ:: እንደ እግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረው አዲሱ ሰው የጌታ ብርሃን የበራለት እርሱ ስጋን ይከለክላል:: ሰራውንና ሀሳቡን ይቃወማል:: የመግዛት ሀቅሙም የጨምራል:: በመከራ ውስጥም ለማለፍ በዚህም ውስጥ እንኳ ለመታዘዝ የሚበረታ ነው
1. ወደ ወጥመድ እንደገባን እንዴት ነው የምናውቀው? ለመውጣትስ ምን ማድረግ አለብን? 2. በልምምድ ህይወትን መምራት ክስረት ነው ወይ? 3. እኛ እውነት በመሰለን ነገር መንፈስ ቅዱስ አይወቅሰንም ወይ? 4. በህይወታችን ያለውን አረም እንዴት ነው የምናስወግደው?
የመንፈሳዊ ህይወታችን የአድማስ ስፋት ሰውን ሁሉ በክርስቶስ ፍቅር የማየታችንና የመቀበላችን መጠን ህሊናችን ኀፁህ የሆነውን ያህል ነው:: ነፃ ባልወጣንበትና ባልተፈታንበት በዛ የክርስቶስ ህይወት ወደ ሌሎች አያልፍም:: በህይወት ጉዞአችን ውስጥ ያዘንበት አልፎም የተጎዳንበት ህሊናችንም ያልነፃበት ጊዜዎች ሁኔታዎችና ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ:: ይሁን እንጀ በክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር የተቀበልነው ፀጋ ይህን ሁሉ ልናልፍ በወጥመዱም እንዳንያዝ እንድናሸንፍ የሚያበቃ ፀጋ ነው:: - ህሊናው ንፁህ የሆነና የተፈታ እርሱ እጆቹን ወደ እግዚአብሔር ለማንሳት ደግሞም ለመፀለይና ለማምለክ ነፃ ነው::
እግዚአብሔርን በአንድ ላይ ስናመልክና ስናገለግል በመንፈሳዊ ህይወታችን ከሚያስፈልገን ነገር አንዱና ዋናው እርስ በእርስ መቀባበል ነው:: በዚህ መቀባበል ውስጥ አንዱ ለሌላው መንፈሳዊ በረከት ይሆናል:: ይህ እንዲሆን ደግሞ እይታን ማስተካከል የግድ ነው:: ይኸውም ሰውን በተላንትና ድካሙና ባልበቃበት በኩል ያለውን በመቁጠር ሳይሆን እግዚአብሔር እንደሚያይ አይቶ በመልቀቅ ነው:: ሰለዚህ ሌሎች በእኛ ህይወት ውስጥ መነፈሳዊ በረከት ሊሆኑን የሚችሉት እኛ የለቀቅናቸውን ያህል ነው:: እኛም ለሌሎች መንፈሳዊ በረከት መሆን የምንችለው እንዲሁ ሰዎች እኛን በለቀቁን መጠን ነው:: - አማኝ በውስጡ ያለው ፀጋ ጎልቶ እንዲወጣ እንዲጠቅምና ለበረከትም እንዲሆን ሊለቀቅ ያስፈልጋል::
ጌታ ወደ ህይወታችን ወደ ነገራችን የሚመጣው ለጥየቄያችንም መልስ የምናገኘው እኛ በፈለግነውና በራሳችነም እየተጋን ባለንበት ሳይሆን ነገር ግን በራሱ ጊዜና ሁኔታ ይመጣል:: በተለይ በራሳችን የሆነውን ጥረት ባቆምንና ረዳት በፈለግንበት ወቅት:: ጌታ ወደ እኛ ሲመጣ አይኖቻችንን ይገልጣል: :ለጌታ ያለን ፍቅር ይታደሳል:: ከለፋንለት ነገር ይልቅ የእርሱን ታላቅነትና ምሪት እናያለን:: በእርሱም በረከት እንሞላለን:: ጌታ በእኛ ህይወት ዋናው አላማ ፈፅመን እንከተለው ዘንድ ነው:: በዚህ ውስጥ :- - ለጥያቄ መልስ ይገኛል:: - ከእርሱ ጋር ህብረት ማድረግ ይኖራል:: - እውነተኛ ፍቅር በተሞላን መጠንም እንዲሁ ጌታን ፈፅሞ መከተል ይሆንልናል::
የእግዚአብሔር ፅድቅ ሰውን ከገነት እንዳስወጣው የእግዚአብሔር ምህረትና ፍቅር ደግሞ ሰውን ከወደቀበት ለማንሳት ከኃጢአት ከክፉ ከአጋንንት እስራት ደግሞም ከህይወት እስራት ነፃ ሊያደርግ ሊፈታው ወደ ምድር ወርዷል:: ጌታ እኛን ሁኑ ያለን እርሱ ለአኛ የሆነልንን ነው::ምህረትንና ፍቅርን እንደተቀበልን እኛም ልንሰጥ:: ነፃ ነኝ የሚል የተፈታ እርሱ ፍቅርና ምህረት የተሞላ ነው:: የሚሰማውንና የሚያየውን ሁሉ በፍቅርና በምህረት ውስጥ ያያል:: - ወንጌል ነፃ ያላወጣው እርሱ ራሱ አልተፈታምና ሌላውን መፍታት አይችልም::
ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን ወደ እግዚአብሔር መንግስት የገባ ሁሉ የህይወት ጉዞው እግዚአብሔር እንደወደደና ፈቃዱም ባለበት ነው:: ሰለዚህ በህይወታቸን አጋጣሚ የምንለው ወይም በአጋጣሚ የሚሆን ነገር አይኖርም:: ይህንንም ማወቅና መረዳት ሰለ ራሳችን ያለንን አተያይ የስተካክላል:: - እግዚአብሔር በእኛ ላይ ያለውን መልካሙን አላማና በእርሱ ዘንድ ያለንን ክብር እናያለን:: - ክርስቶሰ በእኛ ውስጥ አለና ልዩነት ያለው እልፍ ያለ ህይወትና ኑሮ እንደተሰጠን እናያለን:: - በክርስቶስ ትምህርት የመኖር ህይወት እንደተሰጠን እናያለን:: - በቃሉ የሚታዘዝ ህይወት እንደተሰጠን እናያለን:: በአጠቃላይ በዚህ ምድር ስንኖር እልፍ ባለ ህይወትና ኑሮ ለወንጌል ስራ እንድንኖር ይህ በእኛ ላይ ያለው የእግዚአብሔር አጀንዳ ነው::
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ማዳኑን ከገለጠ ጊዜ ጀምሮ አለም የሰው ዘር በሁለት ተከፍሏል:: ይኸውም በፀጋው የሚኖር ህዝብና ያለፀጋው በራሱ ጥረትና ግረት የሚኖር እንደፈለገውም የሚወጣና የሚገባ በፍረድ ስር ያለ ህዝብ:: - በፀጋው የሚኖረው ህዝብ ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ እንዲሁም የሚያደርገውንም ሁሉ እንደ እግዚአብሔስ ፈቃድ ለእግዚአብሔር ክብር ይንቀሳቀሳል ያደርጋልም:: ስለዚህም በሚገባበት ስፍራም ሆነ በሚሰራው ሁሉ የጌታ በረከትና ሞገስ ከእርሱ ጋር ይሆናል:: - ያለ እግዚአብሔር አንቀሳቃሽነት የምናደርገው እንቅስቃሴና የምንሔድበት ስፍራ ከበረከቱና ከሞነሱ የጎደለ ነው:: ይሁን እንጂ በመመለስና በንስሀ እንደገና ከራሳችን ልንወጣ ወደ ሞገሱና በረከቱ ልንገባ የጌታ ፈቃድ ነው::
የሁኔታዎች አለመስተካከል እና ድርብርብ የሆኑ ችግሮች በላያችን ላይ መብዛታቸው ነገራችንን የሚያጨልሙ ቢመስሉም እግዚአብሔር ግን በዚህ ከባድ ሁኔታ ውስጥ ከማይቻል ነገር ውስጥ መፍትሄን ማዘጋጀት እንደሚችል ማሳየት ይችላል፡፡ ለዚህ ነው በመጽሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ ባለቀ ነገር ላይ የተገለጠ የእግዚአብሄርን የዝግጅት ችሎታውን እናነባለን፡፡ እኛ አንድን ነገር ማዘጋጀት ብንችል እንኳ ባለ ነገር ላይ እንጂ በሌለ ነገር ላይ ምንም ማዘጋጀት አንችልም እግዚአብሔር ግን በባዶ ነገር ላይ ተገልጦ ሁሉን ማዘጋጀት ይችላል፡፡
እግዚአብሔር ዓላማውን እና ሃሳቡን ባስቀመጠባቸው ሰዎች ላይ ያን ጊዜ ሰይጣንም የክፋት ኢላማውን ያደርጋቸዋል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ዓላማውን ባደረገባቸው ልጆቹ ላይ ጥበቃውን እና ማዳኑን ያበረታል፡፡የእግዚአብሔር እጅ በዳዊት ላይ እንደነበረች ሁሉ የንጉሱ ሳኦል እጅ ደግሞ በዳዊት ላይ ነበረች፡፡ ዳዊት በሳኦል ክፋት እና ተንኮል ዳዊት ህይወቱ ያድግ ይሆን እንጂ ዳዊት በሳኦል እጅ አይጠፋም፡፡ እግዚአብሔር በምናልፍበት ሁኔታ ውስጥ የሚያድገውን ማንነታችንን ማየት ያስደስተዋል ምክንያቱም በተለያዩ ሁኔታዎች ውስጥ ስናልፍ በኛ ህይወት ማደግ እግዚአብሔር ይከብራል ስለዚህ ማንኛውም ነገር እኛን እንዲያጠፋን ሳይሆን እኛን እንዲያሳድገን ጌታ በማዳን እና በጥበቃው ውስጥ ጋርዶን ያሳድገናል፡፡
የሐዋርያት ሥራ - ምዕራፍ 10:36-48 ክፍል 42
አማኝ በሚያልፍበት በማንኛውም ፈተናና አሰጨናቂ ሁኔታ ውስጥ ፀንቶ የመቆሙና በችግሩ አስፈሪነት ያለመናወጡ የሚለካው መንፈሳዊ አይኖቹ ተከፍተው የእግዚአብሔርን የሀይሉን ታላቅነት ባየበትና ባወቀበት ልክ ነው:: የእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነትና የሀይሉ ታላቅነት እውቀት ሆኖ ሲገዛንና የተስፋ ቃሉን ከችግሩና ከፈተናው በላይ ማሰብና ማመን ስንጀምር ጌታ በነገሮቻችን ላይ መልስ አለው:: ምስጋናም ይበዛልናል:: ይህ የእግዚአብሔር የሀይሉ ታላቅነት ተፈትኖ የተገለጠ ነው:: ይኸውም በኢየሱስ ከርስቶስ ትንሣኤ ሞትንና የሞትን ሀይል ድል በማድረግ የሚያምኑትንም በህይወት ለዘላለም አንዲኖሩ ይህን ታላቅ ተስፋ በመስጠት ነው::
እስራኤል ከግብፅ ባርነት ነፃ ወጥተው ወደ ተስፋ ምድር ሲጓዙ ብዙ ጊዜ ከእግዚአብሔር ከአምላካቸው ፈቃድ ሲወጡ ከሚመራቸውም ከሙሴ ጋር ሲጋጩ ይህም እንቅፋት ሲሆንባቸው እናያለን:: አብዛኛው መሰናክሎች ከውጭ ሳይሆን ከውስጥ ከራሳቸው የሆነ አንቅፋት ነበር:: በግብፅ ሳሉ ይበሉትና ይጠጡት የነበረውን መናፈቃቸውና የእግዚአብሔርን መግቦት መናቃቸው ነው:: - ዛሬም ቤተክርስቲያንን የሚፈትናት ትልቁ እንቅፋት መከራ ሳይሆን ከውስጥ የሆነ የአለምና የስጋ ምኞት ነው:: በክርስቶስ ያገኘነውን ቤዛነት ደህንነትና ነፃነት አክብረን ልንይዘው ይገባል:: ለስጋና ለአለም ምኞት ለፈቃዱም እምቢ ለሚል ለእርሱ የሚረዳ የሚያግዝ ፀጋ ከጌታ ዘንድ አለ:: አርሱ የታመነ ነውና::
የእግዚአብሔር ህዝብ በህይወት ጉዞው ላይ ሊጠነቀቅ ከሚገባቸው ነገሮች አንዱ ቸልተኝነት ነው:: ቸልተኝነት የተነገረውን ሰምቶ ከማድረግ ለከናወን የሚገባውን ከማከናወን መዘግየት ወይም እንደ ቀላል ቆጥሮ አሳንሶ ማየት ...ወዘተ ነው:: የክርስትና ህይወትና ኑሮ የድል የመሻገር ወደ ፊት የመራመድ ህይወት ነው:: ሰለዘህ በአንደዚህ አይነት ህይወት ቸልተኘነት ሰፍራ ሊኖረው አይገባም:: በመሆኑም እለት አለት ቸል ያልኩት ምን አለ? እያልን ራሳችንን እየጠየቅንና እየመረመርን የምንኖረው ኑሮ ነው:: - ከቸልተኝነት ስንላቀቅ ማምለክ እንደሚገባን እናመልካለን:: መፀለይ እንደሚገባን እንፀልያለን:: ማገልገል እንደሚገባንም እናገለግላለን:: ምንም በድካም ብንሆን የሚያበረታ ጌታ ፀጋን ሊሰጠን ከቸልተኝነት ወጥተን በትጋት እንድንሆን ሊረዳን የታመነ ነው::
የሐዋርያት ሥራ 16:40 ,17:1-3ክፍል 66
ላላገቡ ወገኖች የተዘጋጀ ልዩ ፕሮግራም ክፍል 1
ላገቡ ወገኖች የተዘጋጀ ልዩ ፕሮግራም ክፍል 2
እግዚአብሔር ወደ እውነት የሚመራን በመንፈስ ቅዱስ አማክኝነት ነው። በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ሰው የሞተ ብቻ ነው።
እግዚአብሔር መንፈሳዊ ነገራችንን የሚሰፍረው በመታዘዛችን ነው ምክንያቱም መታዘዛችን እግዚአብሔርን የማመናችን ውጤት ስለሆነ። መታዘዝ የምንችለው ስንሞትና ስንገዛ ነው።
መንፈሳዊ ሰው በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የሚመራ ነው:: ይህ ምሪት ለሰው ከመዳኑ ከበረከቱ ከጥበቃው ጋር እና ለፈቃዱ ከመኖሩ ጋር የተያያዘ ሲሆን የእግዚአብሔርን ሰዓት ይመለከታል:: በመንፍስ የሚመራ ሰው በእምነትና በመታመን እያደገ በሕይወት ይኖራል:: ሆኖም ሰው ከራሱ መንፍስ ከሚሰማው ልምምድ ብቻ ያደገ ሆኖ በእምነት እና በመታመን ላያድግ ይችላል:: የዚህም ኪሳራ በፍሬው ይታወቃል:: አለማመን ወይንም አለመታመን ለእግዚአብሔር ዘላለማዊ ሀሳቡን ከማከናወን አያግደውም :: እግዚአብሔርን በማውቅ በፀጋ እና በእውቀት ለማደግ ለፈቃዱ የተሰጠ አይምሮ እና ልብ ሊኖርን ይገባል::
ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት መካከል የነበርው በስራው የዓሳ አጥማጅ የነበርው የዮና ልጅ ስምዖን ጴጥሮስ በአዲሱ ስያሜው ኬፋ (ዓለት) ከጌታ እንደ ተነገርው ወንጌልን እያበሰር ነፍሳትን ያጠምድ ነበር:: ጴጥሮስ ቤተክርስቲያንንከጥፍትና ከተበላሸ አስተምሮት እየጠበቀ ፈቃዱን ጥሎ የተሰጠውን ፀጋ እና እምነቱን ጠብቆ በሞቱም ጭምር ክርስቶስን በመምስል ጌታውን አክብርዋል ::
እግዚአብሔር የሰጠንን አደራ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ መፈጸም ።
የመንፈሳዊ ትልቁ ጣራ ሰው ተነስቶ እኔ የጌታ ነኝ ሲል እግዝያብሄር ደግሞ ያንን ሰው የኔ ብሎ ሲጠራው ነው ።
በሂወታችን ለምን ብለን ለምንጠይቃቸው ጥያቄዎች መልሱ ከፊታችን ነው ያለው።
ትክክልኛውን የሰውን አጠቃላይ ማንነት አይምሮው ይገልፃዋል:: ከእግዚአብሔር የተቀበልነውን ፀጋ በቃል በሥራ እና በኑሮ ለመተግብር በቅድሚያ አይምሮአችን መታደስ ይኖርበታል:: እንዲሁም አሁን ያለንበትን የውስጥ አቋም የሚገልጥልን ህሊናችን ሲሆን ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝው እና ከእርሱ የምንሰማው በመንፈሳችን ስለሆነ የጠራ የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመስማት መንፍሳችን ምንግዜም የነጻ ሊሆን ያስፈልጋል:: እነኝህ ሶስቱ የተያያዙ ሲሆኑ ከእነዚህ አንደኛው ቢቆሽሽ ወይንም ቢበላሽ ሁሉም በአንድላይ ይቆሽሻሉ ወይም ይበላሻሉ:: ስለዚህ ትክክለኛ እና የጠራ ህይወት እንዲኖረን በእግዚአብሔር ቃል ህይወታቸንን ከጠበቅን እነኝህ የተቀደሱ እና የነጹ ይሆናሉ::
እምነት በተገለጠልን ዕውቀት የምንወስደው እርምጃ ነው። እምነት ፩ኛ ከልብ ፍቃድ የወጣ እርምጃ ፪ኛ የፍቃድ እርምጃ ፫ኛ የእውቀት እርምጃ ነው። እምነት ካለን በእግዚአብሔር ዘንድ ፀጋን ተቀብለናል በወልድ ዘንድ እዳችን ተወስዶ ታዳጊያችን ሆነ በሰው ዘንድ ደግሞ ወደ ፀጋው ዙፋን ገባን።
የነገር ሁሉ መጠቅለያ ጌታን ማስከበር ነው፤ ይህም ብምናገለግልበት ጸጋ ብቻ ሳይሆን በምንኖረውም ሕይወት ጭምር ነው
እግዚአብሔር በመንገዱ ለሚሄዱት ጻድቃን ለበርከት ሊጎበኝ ይመጣል፤ በሌላ በኩል ደግሞ እግዚአብሔር በሰጣቸው እድል ሳይጠቀሙና እርሱን ያቃለሉትን ለመቅጣት ሊጎበኝ ይመጣል
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ወደ መንግሥቱ በጠራው በህዝቡ ላይ ራሱን ይገልጣል:: ደግሞም በግል ህይወታችን እለት እለት በመግባትና በመውጣት በኑሮአችን በስራችን ሆነ በንግግራችን ጌታ በእርግጥ የኛ ጌታና መሪ መሆኑ የታወቃል:: በዚህ መልዕክት እግዚአብሔር በህዝቡ ላይ የሚገለጥባቸውን ሁኔተዎች:- - የአመፅንና የክፋትን ጉልበት በመስበር - ለወንጌልና ለወንጌል ስራና አላማ የቆረጡ በቃሉና በፀሎት የተጉ ሰራተኞችን በመጨመር እና - ህዝቡን የእርሱ ማደሪያው በማድረግ ሲሆን ሌሎችንም በስፋት እንማራለን::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሌሎችን ከመፍታታችን በፊት መፍታት ያለብን ራሳችንን ነው ወይ? 2. ከአልተፈታ ህይወት እንዴት ነው መውጣት የምንችለው? 3. ካልተለቀቀ ህይወት እንዴት ነው መውጣት የምንችለው? 4. እኛ ለቀን ሰዎች ካልለቀቁን ምንድን ማድረግ ያለብን? 5. ለበደሉን ሰዎች ክፉ ሲደርስባቸው ባንፀልይላቸው በደል ነው ወይ? 6. ሰዎች የምንሰራውን ሥራ ከጌታ መሆኑን እንዲያምኑልን ምን እናድርግ? 7. ሰው የተጠራው የራሱን ሸክም ይሸከም ዘንድ ነው የሚለው ይብራራልን። 8. በረከታችን ያለው እግዚአብሔር ባስቀመጠን ቦታ ስንቀመጥ ነው የሚለው ይብራራልን።
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን ሁሉ ለህይወት ጠርቷል:: ጥሪውን ተቀብለን ምላሽ ለሰጠን በመንግስቱም በአገልግሎት ለተጠመድን ለእኛ የኑሮ መለኪያ አለን:: እርሱም የክርስቶስ ህይወት ነው:: ብፅዕና ያለው ህይወት:: በዚህ መልዕክት የኑሮ መለኪያዎችን በዝርዝርና በስፋት አንማራለን::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ኮከብ ቆጣሪዮች በአዲስ ኪዳን አሉ ወይ? ከዋክብት ዘመንን መናገር ይችላሉ ወይ? 2. የሙሴ አማት ኢትዮጵያዊ ነው ወይ? 3. ይሁዳ የተፈጠረው ጌታ ኢየሱስን ለመሽጥ ነው ወይ? ባይሸጠው ኖሮ ጌታ ይሞት ነበር ወይ? 4. በደቀመዛሙርቱ ላይ የደረሰው ስደት ጌታ “ወደ አለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ስበኩ” ሲላቸው እነርሱ ግን በኢየሩሳሌም ስለነበሩ ወደ አለም እንዲሄዱ የመጣ ስደት ነው ወይ? 5. ወንጌልን ለሌሎች እንድናደርስ በእኛ ላይ ስደት ሊመጣ ይችላል ወይ? 6. ወንጌልን ለመመስከር አቅም የምናገኘው እንዴት ነው? 7. ሰዎችን ይቅር ስንል (ስንፈታ) የበረከት ተካፋዮች ይሆናሉ ወይ?
እግዚአብሔር በቤቱ በህዝቡ መካከል ከሚገለጥባቸው መንገዶች አንዱ ሞገስ በመሆን ነው:: ጌታ ለህዝበ ደግሞም ለግለሰብ ሞገስን ይሰጣል:: ሞገስ በእግዚአብሔር ፊት ተተቀብሎትን ማግኘት ነው:: ይህ ሞገስ በክርስቶስ ኢየሱስ ለሚያምኑ ሁሉ የሚሆን ነው:: ለሚታዘዘው በፈቃዱ ለሚሄድ በእርሱ ላይ ለታመነውና ለተደገፈው ሞገሰ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆንለተል:: እግዚአብሔር ሞገስ እንደሚሰጥ እንዲሁ ደግሞ ከፈቃዱ ከወጡና ካልታመኑት ካልታዘዙትም ላይ ሞገሱን ያነሳል:: ይህ ሲሆን በረከት ይጎላል:: ሰላም ይጠፋል:: ለፀሎት መልስ አይመጣም:: ቋንቋ ይቀየራል:: ህይወት በፍርሀትና በድካም ይሞላል:: - በመመለስ ራስንም በፊቱ በማዋረድ ሞገሱን ልንቀበል የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው::
በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ያመንነው ደግሞም በመከተል ላይ ያለነው ምክንያቱ ምንድን ነው? ይህ መልዕክት በስፋትና በዝርዝር የሚመልሰው ጥያቄ ነው:: እያለፍንባቸው ባሉት ነገሮችና ሁኔታዎች የተነሳ በዝለትና በድካም ደግሞም በብዙ ጥያቄዎች ተሞልተን ይሆናል ነገር ግን ስፍራን ባለመልቀቅ በተናገረን ላይ በተዕግስት ፀንተን ልንጠብቅ ነገሮች ባይገቡን እንኳ በምስጋና ሆነን በፊቱ ልንቆይ የጌታ ፈቃድ ነው:: በዚህም ውስጥ ህይወትን በክርስቶስ ውስጥ ሆኖ የመኖርን ትርጉምና ፍሬ እናያለን::
በአማኝ ህይወት ውስጥየእግዚአብሔር ፅድቅ ከሚገለጥበት አነዱ ጣልቃ መግባቱ ነው:: ለማዳን ከጥፋት ለመመለስ ደግሞም የክፉውን ስራ ለማፍረስ:: በምናልፍበት የትኛውም ፈተናና መከራ በእግዚአብሔር ዘነድ ገደብ አለውና ከገደቡ እንዳያልፍ እርሱ ጣልቃ ይገባል:: - ለእግዚአብሔር በህይወታችን ጣልቃ መግባት የኛ በፅድቅ መቆምን በእውነትና በቅድስና ደግሞም በንፅህና መሆንን ይጠይቃል:: የን ጊዜ ካልተጠበቀ ስፍራና ሁኔታ የእርሱን ጠልቃ መግባት ያሳያል:: - አንዳንድ ጊዜ በህይወታችን ጌታ ጣልቃ የመግባቱ ሁኔታና አደራረጉ ላይገባን ይችላል:: ደግሞም ነገሮች አንደምንጠብቃቸው ላይሰካኩ ፍፁምም ሊፈራርሱ ይችላሉ:: እግዚአብሔር ጣለቃ ሲገባ እኛ እንደምናየው የዛሬን ወይም ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ወደፊት ሊሆን ያለውን ከማወቁና ለእኛም ከሚጠቅመን አንፃር ነው::
ሰው በህይወቱ የእግዚአብሔር ምሪት የሚገለጠው በመንፈስ ሲመራ ነው:: በእግዚአብሔር መንፈስ ለመመራት የመጀመሪያውና ዋናው ከራስ ፈቃድ መውጣት ነው:: በራሳችን መንፈሳዊ ነው ያልነው ወይም ያደረግነው ሁሉ መንፈሳዊ አይደለም:: እግዚአብሔር ባለን ውስጥ ራሳችንን የምናገኝበት እርሱ ነው የመንፈስ ምሪት :: ይህን በሚመለከት ጥልቀት ያለው ትምህርት በዚህ መልዕከት እናገኛለን::
እግዚአብሔር የህዝቡ ጠባቂ ነው:: ደግሞም እውነተኛና ፅኑ መሸሸጊያና ማምለጫም ነው:: ከሞተ ፍርሀት ያድናል:: ከዘላለም ፍርድ ይታደጋል:: ከኃጢአት ጉልበትና ከአለም ደግሞም ከክፋቱ ያድናል:: - የመማፀኛ ከተሞች ከበቀለኞቹ ብቸኛ ማምለጫ እንደሆኑ ለኃጢያተኛው በዘላለም ፍርድ ስር ላለ ብቸኛው ማለጫ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ነው:: - ጌተ ኢየሱስ እርሱ ስለ ሀጢአተኛው ራሱን መስዋዕት አድርጎ ያቀረበ ደግሞም የዘላለም ሊቀ ካህን ወደ እርሱ ለሚሸሹ ሁሉ ፅኑ መማፀኛና እውነተኛ መሸሻና መዳኛ ነው::
የአማኝ ህይወት በምድር ላይ ጌታን በማመን ብቻ የሚቆም ሳይሆን ነገር ግን የጌታ ተከታይ ደቀመዝሙር በመሆን የሚቀጥል ነው:: የክርስትና መንገድ ኢየሱስን እያየን የምንሄደው የመከራ ደግሞም የተስፋና የበረከት የሰላም መንገድ ነው:: ኢየሱስን መከተል:- - በራስ ላይ መፍረድን የራስን መተው ይጠይቃል:: - አሰቀድሞ ዋጋ መተመንን ይፈልጋል:: - መጣል ያለብንን መጣል መውጣት ካለብንም መውጣት የግድ ነው:: -ባልተከፈለ ልብ ፍፁም እኛነታችንን ሙሉ በሙሉ መስጠትን ይጠይቃል:: - ጌታን ስንከተል እርሱን እያከበርንና ለእርሱ ምስክሮች በመሆንም ነው:: - መከተል እስከፍፃሜ መሄድ ነው:: በምናልፍባቸው በማንኛውም ነገርና ሁኔታ ውስጥ ፀንቶ መከተል ነው::
ወደፊት መመልከት እድንችል ያለፈውን ታሪካችንን እየረሳን በተፈወሰ ማንነት ወደኋላ ማየት እስከሚያቅተን ድረስ እግዚአብሄር ነጻ ያወጣናል ይቀይርልናል ከኛ የሆነ መፍትሄን ለማግኘትም ብዙ ብንጥርም መፍትሄን ስለማናገኝ የእይታ ለውጥ ያስፈልገናል፤ ህይወታችን ተቀይሮ እይታችን ካልተቀየረ ፈውስ ልናገኝ አንችልም ያለፈውን እያስታወስን ለምን ሆነብኝ እያልን በባለፈው ዕይታ ነገን ለምንመለከት እግዚአብሄር ጣልቃ ይገባልንና ንጻ ያውጣናል ስለዚህ ካለፈ ነገር ስንፈወስ ነገን በተስፋ መጠባበቅ እንችላለን ነጋችንን ስናይ በትላንቱ እይታ ማየት ወደክስረት ስለሚወስደን የእይታ ለውጥ ማግኘት ዋና ነገር ነው
አማኝ በሁለት ጉዳዮች ላይ ሊያተኩር ይገባዋል አንደኛው በክርስቶስ ያገኘው መዳን ላይ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ያንን ያገኘውን የዘላለም ሕይወት መጠበቅ ናቸው። ስለዚህ እነዚህን ሁለት ነገሮች እያጣ የመጣ አማኝ በህይወቱ ውስጥ፡ሊስተካከል በማይችል ጥልፍልፍ ነገር ውስጥ ሊገባ ስለሚችል መጠንቀቅ አለበት። ሐናንያ እና ሰጲራ ጌታን ያገኙ መንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ናቸው ድነዋል መንፈሱን ተሞልተዋል ግን መዳናቸውን እና ያገኙትን ሕይወት አጥብቀው ባለመያዛቸው እና ለምኞታቸው ታልፈው ስለተሰጡ ባገኙት ህይወት መቆምላይ ጸንተው መቆም ባለመቻላቸው ሊያጠፋቸው ቻለ። ይህንን እና የመሳሰሉትን ቁምነገሮች በዚህ መልክት ውስጥ እናገኛለን።
በክርስትና የህይወትጉዞ ከተካፈልነው መንፈሳዊ ህይወት ውስጥ አንዱ ቤተሰብነት ነው:: የእግዚአብሔር ቤተሰብ:: ይህ ቤተሰብ የሆንበት የእግዚአብሔር ቤት ለምን ለማንና እንዴት እንደምንኖር በማወቅ የምንኖርበት ቤት ነው:: - በሞቱና በትንሣኤው የተገለጠው የክርስቶስ ፍቅር በቤቱ ቤተሰብ ልንሆንና ልንኖር ምክንያት እንደሆነን በማወቅ:: - ለእኛ ለሞተውና ለተነሳው ለእርሱ እንኖር ዘንድ ለአለም ለስጋና ለኃጢአት የሞትን መሆናችንን በማወቅ:: - በመስቀል በተወገደው በአሮጌው ሰውና በክርስቶስ በሆነው በአዲሱ ሰው መካከል ያለውን ልዩነትና ማንነት ለይቶ በማወቅ:: የምንኖረው ኑሮ ነው::
እግዚአብሄር ታማኝ መሆኑን በግለሰብ ህይወት፣ በጠራው ህዝብ ላይ፣ እና በሚሰራቸው ተአምራት ታማኝነቱን ገልጧል፡፡ የእግዚአብሄር ታማኝነትን እኛ አመነው አላመነው እርሱ የታመነ አምላክ ነው፡፡እግዚአብሄር ለተናገው የተስፋ ቃል ታማኝ ነው፡፡ በርሱ የሚታመኑትን በሚገባ ያውቃቸዋል እና ፈጽሞ አይጥላቸውም፡፡ በእግዚ ታማኝነት ላይ ያለን እምነት እና መደገፍ ትልቅ ቢሆንልን በብዙ እንጠቀማለን፡፡ባያድንውንም እንኳ ለቆመው ምስል አንሰግድም ያሉትን ታማኝ ልጆቹን የማያሳፍር አምላክ ነው፡፡ በምድርምሆነ በሰማይ እግዚአብሄርን የሚያህል ታማኝ መቼም አናገኝም፡፡
በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር መንግስት ሰንገባ ከምንቀበላቸው የመዳን በረከቶች አንዱ የነፍስ እረፍተና ሰላም ነው:: በዚህ ምድር እረፍት ለማግኘት ሰዎች በብዙ ይደክማሉ:: ስጋን ከማሳረፍ ያለፈ ነፍስን የሚያሳርፍ ግን ምንም ማንም የለም:: ነገር ግን ሰላሜን እሰጣችኃለሁ እኔ የምሰጠው ሰላም አለም እንደሚሰጥ አይደለም ያለው እርሱ ጌታ ኢየሱስ ብቻ የነፍስን እረፍትና ሰላም ይሰጣል:: - ይህም የጌታ ሰላምና እረፍት ቃሉን በመስማት እርሱ የተናገረንን በእምነት በመቀበልና እንደ ፈቃዱም በመሆን አነዲሁም ሁልጊዜ በእርሱ ፊት በመሆን በቃሉና በፀሎት በመትጋት ወደ ነፍሳችን ይፈሳል::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በዛሬ ጊዜ መልአክት የመስማት ልምምድ ሊኖር ይችላል ወይ? መልአክት ያነጋግሩናል ብለን መጠበቅ እንችላለን ወይ? 2. እግዚአብሔርን ወደ መስማት የፀሎት ልምምድ ውስጥ እንዴት ነው የምንገባው? 3. እምነት ከሰማነው ከእግዚአብሔር ቃል ነው የሚለው ቢብራራ። 4. ጌታን ታምነን ግን ለጥቅማችን የምናልፋቸው ችግሮችን ለመረዳት እንዴት ነው የምንችለው? 5. ሳዖል የተለየው ሞገስ ነው እንጂ ስልጣኑን አይደለም የሚለውን ብታብራራልን። ሞገስ ከእኛ የሚለየው እንዴት ነው? 6. ሞገስ ሲመጣ ከእድል ፈንታችን ጋር ያገናኝናል፤ በክብሩ ባለጠግነት ይሞላናል ከሞገሱ ከጎደልን ግን ዋጋ ያስከፍለናል የሚለውን ብታብራራልን። 7. የተጎዳንበትን ነገር እንዴት መርሳይ እንችላለን?
ከእግዚአብሔር የአባትነት ባህርይ አንዱ መጋረድ ወይም መሰወር ነው :: የእርሱ የሆኑትን ልጆቹን ከጥፋት ደግሞም ከመከራ ይሰውራል:: ከአመፀኛው አመፅና ክፋት ከጥፋቱም የሰውራል:: "በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ሰውሮኛል" እንዳለ ዳዊት በዘመናት መካከል የማይለወጥና የማይቀያየር ጌታ ዛሬም አካሄዱን ከእርሱ ጋር ያቀናውን ህዝቡን በፈቃዱና እርሱ ባለው የተገኘውን ዛሬም ከጥፋት ከመከራ የሰውራል::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ስንፀልይ “መንፈስ በማይናገ መቃተት ይማልዳል” የሚለው በልሳን መፀለይ ነው ወይ? በአንዳንድ ሁኔታ መፀለይ ሲከብደን በልሳን መፀለይ አለብን ወይ? 2. 1ዮሐንስ 2፡27 “ማንም ሊያስተምራችሁ አይገባም” የሚለውን ብታብራራልን። 3. የእግዚአብሔርን ሞገስ ለማግኘት የእኛ ድርሻ አለ? ካለስ ምን ማድረግ ነው ያለብን? 4. ፊሊ 3፡13-16 በጌታ እንዳንረካ የሚያደርጉን ነገሮች ምንድን ናቸው? 5. ለተቀበልነው ወንጌል ራሳችንን እንድንሰጥ የሚረዳን ምንድን ነው?
ይህንን ትምህርት ሲያዳምጡ የተለየ መረዳትን ያገኛሉ በተለይም ጠላት በህይወታችን ውስጥ በመንፈስ ቅዱስ ሃይል እንዳንኖር ለማቋረጥ የሚጠቀምባቸውን ልዩ ልዩ ዘዲይዎችን እንዴት እንደሚያቀናብርና ልንደርስ ካለው መንፈሳዊ ብቃት እንደሚያስተጓጉል፡ ከቃሉ በሆነ አቅም ውስጣችን ሲሞላ ግን የማያቋርጥ መነቃቃትን ውስጣችን ይጨምራል ከመንፈስ ቅዱስ የሆነን በረከት እንዴት መጠቀም እንዳለብን እንድናውቅ ና በእውነትኛ መርህ እንድንኖር የሚየደርገንን ማስተዋል ያገኛሉ
አይኖቻችን ያሉበት ህይወታችንን ይወስናል:: በየትኛውም ችግርና ፈተና ውስጥ ብንሆን አይኖቻችን ተከፍተው ጌታን ስናይ ፍፁም ለውጥ ይሆናል:: ነገሮቻችን ባይለወጡ እንኳ የኛ መለወጥ ግን እርግጥ ነው:: እግዚአብሔርን ማየት ሁለንተናን ይፈውሳል:: ከክፉዉ ዘመንና ጥፋቱ ማምለጫው ይኸው ነው:: ጌታን ማየት:: ጌታን ስናይ መፅናናት ሰላምና እረፍት ይሆንልናል:: በምንሰማውና በምናየው አንናወጥም አነደነግጥምም ይልቁን ምስጋናና ምህረት ባርኮትም ይበዛልናል:: እረጅም መንገድ የመጓዛችንም ሀቅም አይኖቻችን በጌታ ላይ በተተሉበት መጠን ልክ ነውና: አይኖቻችን ማንንና ምን ላይ እንደሆነ ራሳችንን ልንጠይቅ ያስፈልጋል
እግዚአብሔር ለህዝቡ የማይለወጥ ፍፁም ፍቅር አለው:: እርሱ ለእኛ ያለው ይህ መውደድ የሚገለጠው ግን እኛ በጠበቅነውና በእኛ መንገድ ሳይሆን ለእኛ በሚጠቅመን እርሱንም በምናከብርበት መንገድ ይገለጣል:: እግዚአብሔር እንደሚወደን በቃሉ ተፅፎልናልና እንደ ቃሉ እንደምንወደድ ልናምን አስፈላጊና ዋና ነገር ነው:: አለበለዚያ ለጊዜው ከሚከሰቱ ሁኔታዎች ተፅዕኖ ስር አንሆናለን:: በእግዚአብሔር ለመወደዳችንም ተጠራጣሪዎች ያደርገናል:: ይህ ደግሞ ሰላማችንን የሚጎዳ ጌታንም ደስ የማያሰኝ ህይወት ይሆናል:: እግዚአብሔር አመፀኛውን እንደሚቀጣ የእርሱን ጉብኝት በተዕግስት የሚጠብቀውን ፃድቁን በመከራ ውስጥ ይጠብቀዋል:: ፅድቁን በሚገልጥበትና በሚሰራበት ጊዜ ገንዘቡ የሆናል:: ከችግሩ በላይ በእርሱ ላይ ያለውን የጌታ መውደድ አይቷልና::
በዚህ ትምህርት የጌታን ማዳን በህይወታችን እንዴት ልናገኝ እንደምንችል ከኛ የሚጠበቅብንን ያላስትዋልነውን ፈውሳችንን ያዘገየብንን የችግራችንን ቁልፉን እንድንረዳና አቅጣጫችንን እንድንለውጥ ያደርገናል:: አልፈንም ወደ ትክክለኛ መረዳትና ውሳኔ ያደርሰናል::
በዚህ ትምህርት እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ቃል ከገባላቸው የቀረ ምንም እንዳልነበረ ሁሉ በመደበላችው ሁሉ መኖር የሚገባቸውን አይነት ኑሮ እንዲኖሩና ርስት ያልነበረውን ህዝብ ባለርስት ካደረገ እንዲሁ ዛሬም ለክብሩ የተለየን ሰማያዊ ርስት የተሰጠን እንደሆንን እንድንገነዘብ ይረዳናል::
እግዚአብሔር ዛሬም ሰውን ይጠራል:: ከኃጢአት ከበደል ከአመፅ ስፍራ ይጠራል:: እርሱ ከማይከብርበት ደስም ከማይሰኝበት ስፍራ ይጠራል:: ሲጠራንም ሊወቅሰን ወይም ሊፈርድብን ሳይሆን ነገር ግን ለበረከትና ለፈውስ ነው:: እግዚአብሔር ከጠራን በኃላ በቀደመው ማንነታችን እንድንቀጥል አይደለም:: በህይወታችን ለውጥ ይሆናል:: ለፈቃዳችን ሳይሆን ለፈቃዱ ልንኖር እንጀምራለን:: ተስፋችን ከምድር ላይ ተነስቶ የጠራን ጌታ ባለበት በሰማይ ይሆናል:: ሰላምና እረፍትም ይሆንልናል::
ጌታ ኢየሱስ በምድር ላይ ሲመላለስ የመስቀል ጉዞ ነበር የተጓዘው:: የመስቀል ጉዞ ደግሞ በመጀመሪያ ራስን ዝቅ ማድረግን ይጠይቃል:: ራሱን ባዶ አድርጎ በስጋው ወራት የተመላለሰበት የጌታ ህይወትና ኑሮ ዛሬ እኛ የእርሱ ተከታዮች ልንኖረው የሚገባውን ኑሮ ያሳያል:: እውነተኛ ደቀመዝሙር ኢየስሱን በቃልና በስራ በህይወቱ የሚያሳይ ሲሆን የመስቀሉንም ጉዞ ሲጓዝ ብቻውን ሳይሆን ነገር ግን ታላቅ ተስፋን ከሰጠው አሸናፊ ከሆነው ጌታ ጋር በመሆን ሌሎችን ደቀመዝሙር ለማድረግ የሚተጋ ነው::
ሰው በህይወቱ የሚያርፈው በጌታ ልቡ ሲጠበቅለት ነው፤ ያላረፈ ሰው ልቡ ሙሉ ለሙሉ በጌታ ያላረፈ ሲሆን ነው፤ ሰው የሚፈልገውን ማግኘቱ እረፍት አይደለም እረፍት አገኝበታለሁ ብሎ የሚገባበት ነገር እረፍት የሚነሳው ይሆንበታል ፤ ከሁሉም በላይ የነፍስ እርፍት ክርስቶስ የኛ ሲሆን ነው እርሱ ካላሳረፈን ምንም አያሳርፈንም፤
የአማኝ መንገድና ህይወት የእለት ተእለት ኑሮውም እነደ እግዚአብሔር ቃል የሆነ ደግሞም እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሊሆን ይገባዋል:: እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ማንነት እንዲኖረን ደግሞ ምርጫችን ሁልጊዜ በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ መሆን ዋናውና የመጀመሪያው ነው:: በዚህ መልዕክት የአማኝ ህይወት በእግዚአብሔር ፊት እና እግዚአብሔርን በሚወዱ ሰዎች መካከል ምን ሊመስል እንደሚገባ እንማራለን::
መታዘዝ ባለበት በዛ ዋጋ መክፈል አለ:: ይህንን ደግሞ ራሱን አሳልፎ ለመስቀል ሞት እስኪስጥ ድረስ አባቱን በታዘዘውና የመታዘዝ ፍፁም ምሳሌያችን በሆነው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናያለን:: ከመታዘዝ የጎደለ ህይወትና ማንነት ያለው እርሱ ከእግዚአብሔር የተስፋ ቃልና ከበረከቱ ደግሞም ከፀጋው የራቀና የጎደለ ነው:: ከምንም በላይ በእግዚአብሔር ላይ ማመፅና ለጌትነቱ የሚገባውን ክብር አለመስጠት ነው:: - መታዘዝ የእውነተኛ ደቀመዝሙር ህይወት ነው:: ስለዚህ ጌታን እንከተላለን እያልን ከዚህ ህይወት ጎድለን እነዳንገኝ ልንጠነቀቅ ይገባል::
እግዚአብሔር በመንገዱ ፃድቅ የሆነ እውነተኛ አምላክ ነው:: ስለዚህም ሰውንም በእርሱ መንገድ እንዱሄድ ይፈልጋል:: የሰው በረከት ፈውሰና ጉብኝት ያለው በእግዚአብሔር መንገድ ላይ በሆነበትና በተገኘበት መጠን ነውና:: በዋጋ ተገዝተናልና የራሳችን አይደለንም:: ስለዚህ መንገዳችን ደግሞም በረከታችን ያለው የጌታ መንፈስ በሚመራንና በሚያስኬደን በኩል ነው::ከዚህ የወጣ ለጊዜው መልካምና በረከት የሞላበት ይምሰል እንጂ ፍፃሜው ኪሳራና ውድቀት ነው:: በእግዚአብሔር መንገድ እንሁን እንጂ ነገሮች ያልተሳኩ ደግሞም ጉድለትና እጥረት ያለበት ኑሮ ቢመስልም እንኳ የጌታ ጉብኝትና በረከት በራሱ መንገድ በጊዜው ይሆናል:: በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን ሰላምና እረፍት እምነትና ተስፋ የሞላው ህይወት ይሆንልናል::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ከምናለቅስበት ለመፈወስ የምንጎበኝበትን ቀን መቼ እንደሆነ የምናውቀው እንዴት ነው? 2. ሥፍራ ወደ አለመልቀቅ የምንደርሰው እንዴት ነው? 3. በህይወታችን ውስጥ የሚፈራረቁበትን ቀኖች እንዴት ነው የበረከት ይሁኑ አይሆኑ የምንለየው? 4. የጌታ ቀን ወደ እኛ ሲመጣ እንዴት ነው የምናውቀው? 5. ስለ ጌታ የምንቀበለውን መከራ ከሌላ መከራ ለይተን በህይወታችን የምንቀበለው እንዴት ነው? 6. ሰው በችግር ውስጥ ሲያልፍ ለመርዳት ያንን ችግር እንዴት ነው የምናውቀው?
የአማኝ ህይወት በምድር ላይ የመስቀል ጉዞ ነው:: በመስቀል ጉዞ ውስጥ የሰይጣን ውገያና ፈተና አለ:: ደግሞም በዙሪያችን ባሉ ሰዎች መገፋትና መጣል አለ:: መከዳትና መተውም አለ:: በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የማይናወጥ ዋስትና አለን:: የሚያበረታን ጉልበትና በመከራ ውስጥም ፅናት የሚሆነን ጌታ እርሱ ከእኛ ጋር ነው:: እስከ አለም ፍፃሜ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ የሚለው የተስፋ ቃሉ በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ የማይናወጥ ፅኑ የተስፋ ቃል ነውና::
እግዚአብሄርን ማመስገን በፈቃዳችን የሚሰጥ ነገር ቢሆንም እግዚአብሄርን ማመስገን ግን የርሱ በጎ ፈቃድም ጭምር እንደሆነ ማወቅ እንዳለብን ይህ ትምህርት ያሳስባል። በሁሉ ማመስገንን በተለየ መልኩ የምንማርበት መልዕክት ነው። አንዳንድ ስዎች በተለያዩ ችግሮች ውስጥ እያለፍኩ ነው እንዴት አድርጌ ነው እግዚአብሄር የማመሰግነው ብለው ይጠይቃሉ። ነገር ግን በዚህ ትምህርት ውስጥ እንዴት እያለፍንበትን ያሉትን ነገሮች ለክብሩ በምስጋና እየቀረብን ድልን እንደምናገኝ ያስተምረናል።
እግዚአብሄር የጠራን ለድል ስለሆነ በሃጢያት በበደለኛነት ከመኖረ ሊታደገን ለሚጣራን ፈቃደኛ ባለመሆን በቸልታ ስንመላለስ ሀይወታችን እግዚአብሄርን የሚያሳዝን ስለሚሆን ከሃጢያት ሸሽተን ማምለጫ ተዘጋጅቶልናል ይህ ማምለጫ ሮጦ ለሚመጣ ሁሉ መደበቂያ ይሆናል ስለዚሀ የተዘጋጀልንንማምለጫ እንዳናጣው ልንጠነቀቅ ይገባናል፤
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በሐዋርያት መመስረት እና ከሐዋርያት ትምህርት ከእውነት ከክርስቶ ትምህርት መውጣት ነው የሚለው ይብራራልን። 2. ሐዋርያት በክርስቶስ ስም አጥምቀዋል ጌታ “ኢየሱስ በአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ እያጠመቃችሁ” ብሏል። በኢየሱስ ማጥመቅ የሚለው ምን ማለት ነው? 3. ደዌ እና ህመም የሚለው ቃል ይብራራልን። 4. የድሮ ባህሪያችን ተለውጦ በድሮ ባህሪያችን የሚያውቁን ሰዎች ፊት እንዴት ነው ወንጌል ለመመስከር የምንችለው? 5. ህይወታችን ተቀይሮ እመለክታችን ላይለወጥ ይችላል? ወደ እዚህስ እንዴት ነው የምንመጣው?
ሰው ይብዛም ይነስ የኔ የሚለው የሚቆጥረው የሚኮራበት ልቡንም የሚጥልበት ደግሞም የሚመካበት ነገር አለው:: እውቀት ሀብትና ውበት እንዲሁም ዘመድ የቅርብ የምንለው ሰው ወዘተ... በአንድም በሌላ ሰው ከሚመካባቸው ጥቂቶቹ ናቸው:: እነዚህ ሁሉ ግን እንድ ቀን የሚክዱን ደግሞም ተስፋ የማይደረግባቸው ይሆናሉ:: በጊዜውም አለጊዜውም የማየከዳና የማያሳፍር ፅኑ መመኪያ ግን እርሱ ጌታ እግዚአብሔር ብቻ ነው:: እግዚአብሔርን በተመካንበት በዛ ሰላም ይኖረናል:: ተስፋችንም እውን ይሆናል::መፅናናት ሀይልና ብርታትም ይሆንልናል::
አላማ ሲኖረን የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል እንደዚሁም በቤቱ ስንኖር ዋጋ ስንከፍል ደስ ይለናል፤ በቤቱ ውስጥ ስንመላለስ ኑሮአችን አላማ ያለው ይሆናል ለምን በቤቱ እንደምንኖርና እንዴት እንደምንኖር እናውቃለን፤ ሊመጣ ያለውን ተስፋችንን እየጠበቅን አላማ እንዳለው ሰው የምንኖርለት ጌታ ሊመጣ ስለሆነ ተዘጋጅተን እንጠብቀው::
እግዚአብሔር እርሱ መልካም እረኛ ነው:: ሰለዚህ ለእያንዳንዳችን ግድ ሰለሚለው በሰው ሁሉ ዘንድ የተጣልንና የተተውን በሆንንና ብቸኝነት በተሰማን ጊዜ ከጎናችን የሚቆም ካለንበት ሊያወጣን ሊፈውሰንና እደገና ጨለማችንን ሊያበራ ተስፋችንንም ሊያድስ የታመነ ጌታ ነው:: ጨለማው የበራለት እስራቱም የተፈታለትና ተስፋው የታደሰለት እርሱ ኢየሱስ ወደ ህይወቱ ገብቷልና ጌታን ለመከተል አይቸገርም:: ደግሞም ህያው ምስክር ይሆናል:: በዚህ መልዕክት ይህንን በስፋት እንማራለን::
ጌታ ያለበትን መምረጥ ከክፉው ወጥመድ ማምለጫ ነው:: ጌታን የመረጠ ባህርይውንም መርጧል:: ይኸውም ራስን ዝቅ ማድረግ :: ራሱን ባዶ አድርጎ ሥጋን ለብሶ የተገለጠው ጌታ የከፍታ የማሸነፍና የፀጋው መቀበያ መነገዱ ዝቅ ማለት እንደሆነ አሳይቶናል:: ሰው ዝቅታውን ባልመረጠበት በዛ ጌታን አያገኘውም:: ከከፍታ ሩቅ ነው:: ከአሸናፊነት ከፀጋውም ሩቅ ነው:: የዝቅታ መንገድ ለስጋ አይመችም ለሰይጣንም እንዲሁ:: ነገር ግን ለጌታና ለፀጋው ቅርብና ምቹ ነው:: ሰለዚህ ምርጫችንን ልናስተካክል ያስፈልጋል::
አማኝ በዚህ ምድር ላይ ሲኖር በእግዚአብሔር ፊት ራሱን በማዋረድና ዝቅ በማድረግ ነው:: ይህ በእግዚአብሔር ቤት ያለው የህይወት መርህ ነው:: በዚህ መርህ የሚኖር አማኝ ደግሞ እግዚአብሔርን ይሰማልና እርሱ ከፍ ያደርገዋል:: ሰለዚህ የአማኝ ከፍታ በህይወቱ የጌታ ፈቃድ የሚፈፀምበትን ቃሉን የሰማውን ያህል ነው:: ቃሉ ይመራል ይጠብቃል ያኖራል ደግሞም ከፍ ያደርጋል:: በምንሰማው የእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ራሳችንን ስናይ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፈቃድ እንረዳለን:: በዙሪያችን ያለው የሚያደክምና ባዶ ሆኖ ቢታይ እንኳ በቃሉ ውስጥ ሆነን ስናይ ግን ሀይል ይሆንልናል እንበረታለን:: እምነት ይሆንልናል ተስፋችን ይታደሳል:: በፊቱም ያለን ብልፅግናና ከፍታ ይታየናል::
አማኝ ዝቅ ብሎ የመኖርን ህይወት በመረጠበት በዛ ውስጥ በምንም አይነት ሁኔታ ይለፍ ጌታ ከእርሱ ጋር ይሆናል:: ድምፁን ይሰማል:: ማፅናናቱንም ያያል:: የዝቅታን ህይወት መርጠን መጓዝ ስንጀምር ያ ጌታ ሊያመጣን ወዳለው የህይወት ከፍታ የመሄጃ ጅማሬ ነው:: በየትኛውም ጉድለትና መከራ ውስጥ እናልፍ ይሆናል ነገር ግን እይታችን ይለወጣል:: የእግዚአብሔርን ትልቅነት እናያለን:: በእምነትና በምስጋና የተሞላ የብርሃን ህይወት ይሆንልናል::
ይህንን ርዕስ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ አስተማሪዎች ተምራችሁት ይሆናል በዚህ መልዕክት ውስጥ ግን በሌላ አቅጣጫ መታዘዝ የሚለውን ርዕስ ትማሩታላችሁ። በዚህ ትምህርት ውስጥ ከተነሱት ዋና ዋና ነገሮች አንዱ መታዘዝ የጽድቅ ምንጭ ሲሆን አለመታዘዝ ደግሞ ከአመጻ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ያስተምራል
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በህይወታችን የሚያልፉት መከራዎች ጌታን የሚያከብሩና የማያከብሩ መሆናቸውን እንዴት እናውቃለን? 2. በመንፈሳዊ ህይወታችን አድገናል ብለን በጌታ አንዳንዴ መመካት ሌላ ግዜ ደግሞ አለመመካት እንችላለን ወይ? 3. በህይወታችን በሚያልፈው ሁሉ በጌታ መመካት አለብን የሚለው ቢብራራ። 4. መንፈሳዊ ህይወታችን ሳይዛባ መቆም እንዴት ነው የምንችለው? 5. ሁል ጌዜ በህይወታችን ዝቅ ማለት የምንችለው እንዴት ነው? 6. ጌታን ስንከተል ትችኛውን መምረጥ ያለብን ለምንድን ነው? 7. በእምነት ከመፀለይ ወደ ልምምድ የፀሎት ህይወት መግባት ይቻላል? 8. ከምንሰማው ሚድያ ተነስተን ወደ ትክክል ፀሎት ለመምጣት እንዴት ነው የምንችለው? 9. እጅ መንሻ ሕግን ያዛባል የሚለው ቢብራራልን።
እግዚአብሔር ማንንም አይጥልም:: ምክንያቱም ይህ የእርሱ ባህርይ አይደለምና:: እርሱ የቃል ኪዳን አምላክ ደግሞም የተናገረውን ሊፈፅም የታመነ ነው:: ነገር ግን ከምናልፍበት ሁኔታ የተነሳ ደግሞም የፀሎታችን መልስ የመጎብኘታችንም ጊዜ በዘገየና ሁኔታችንም ባስጨነቀን ጊዜ እግዚአብሔር እንደተወን እንደጣለንም እናስባለን:: እግዚአብሔር ግን ጊዜ አለው:: በምንም ሁኔታ ውስጥ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው ወደሚል የእምነት ከፍታ እንድንመጣ የእርሱ ፈቃድ ነው:: × አልለቅህም ከቶም አልተውህም ያለ ጌታ የታመነ ነው::
መንፈሳዊ ከፍታችን መለኪያው በእኛ ሁኔታ እግዚአብሔር ራሱን ለእኛ የገለጠበትና በተገለጠልንም እኛ የተካፈልንበት ህይወት ነው:: በእርግጥ እግዚአብሔር የበራለት እርሱ በቀደመው ማንነትና መንገድ ላይ አይገኝም:: እግዚአብሔር ራሱን በገለጠለት የብርሃን ህይወት ውስጥ ስለሚሆን የሚያየውም የሚሰማውም ከዚሁ ብርሃን ውስጥ የሚወጣውን ነውና:: የአማኝ መንፈሳዊ ህይወት እግዚአብሔርን እንደ አምላክነቱ ቃሉንም እንዳለው ባመነውና በተቀበለው ልክ ከከፍታ ወደ ከፍታ የሚያድግ ህይወት ነው:: የልጁን መልክ ልንመስል ተጠርተናልና::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. እግዚአብሔር የሚፈልገው በሥፍራችን እንድንሆን ነው የሚለው ይብራራልን። 2. እግዚአብሔር በሰጠን አገልግሎት ሳይሆን እኛ በምንፈልገው አገልግሎት ብናገለግል እግዚአብሔር አያውቀንም ማለት ነው? 3. እግዚአብሔር በህይወታችን የሚሰራው በሰጠን ህይወት ነው ተብሎ ተምረናል። ወደ ዚህ ህይወት እንዴት ነው የምንመጣው? 4. እንዴት ነው ይቅርታ የምንጠይቀው? ይቅርታ የጠየቅነው ሰው ይቅርታ ስንጠይቀው ይቅር ብያለው ማለት አለበት? 5. የእግዚአብሔር መገኘት ከህይወታችን ልናጣው (ሊጠፋብን) ይችላል? 6. መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናት ከየት ነው መጀመር ያለብን? እንዴትስ ነው ማንበብ ያለብን? 7. መንፈሳዊ ህይወት መለቀቅ አለበት የሚለው ይብራራልን። 8. መንፈሳዊ ሰው ነፍሱን ማዳመጥ ሲጀምር እግዚአብሔር ሩቅ ይሆንበታል፣ የተተወ የተጣለ ይመስለዋል የሚለው ይብራራልን።
የኣማኝነት ታማኝነት በአግዚአብሄር መታመን ነው። አምነት ደግሞ ከመስማት ነው መስማትም ከአግዚአብሄር ቃል ነው። የአግዚአብሄርን ቃል ስንሰማ በአርሱ አየታመንን አንሄዳለን አርሱ ደግሞ ጋሻችን አንደሆነ አንረዳለን። በአግዚአብሄር ላይ ያለን የአረፍት መጠን፣ የሰላሙ መጠን አና የደስታው መጠን፣ በአግዚአብሄር የታመንንበትንና የተደገፍንበትን ያህል ነው።
ብዙ ደስ የሚያሰኙ ነገሮች በዚህ ምድር ሊኖሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን ጊዝያዊ አና ተለዋዋጭ ናቸው። የማይለዋወጥ ዘመን የማይሽረው የዘለኣለም ደስታ ግን የሚገኘው በጌታ በአየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።
ሰው በሕይወት ዘመኑ ነገሮችን የሚለይበት መንፈሳዊ ብቃት ከሌለው ለብዙ አደጋ የተጋለጠ ነው። በዚህ ትምህርት ውስጥ መንፈሳዊ ሰው ሁሉን ይመረምራል እሱ ግን በማም አይመረመርም የሚለውን የቃሉን እውነት እንማራለን።በዘመናችን ነገሮችን ሳናመዛዝን እና በመንፈስ መለያትን ሳናደግ ለገባንባቸው ስህተቶች ሁሉ አስተማሪ የሆነ መልዕክት ነው። መረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ የተመረኮዘ መለየት እና መንፈሳዉ መለየት የተለያዩ ነገሮች እንደሆኑ በዚህ ትምህርት ላይ ተብራርቶ ተሰጥቷል።
ይህ ትምህርት በውስጡ እግዚአብሄር የተሃድሶ አምላክ እንደሆነ እና ሰይጣን ደግሞ ነገሮችን ለማፍረስ የሚተጋ ፉ መሆኑን የምንማርበት ነው። በዚህ በመጨረሻው ዘመን መንፈስ ቅዱስ እውነተኛ አዳሽ ሆኖ በየዕለቱ ያድሰናል። የኛ ድርሻ ወደዚህ የተሃድሶ አምላክ መቅረብ ብቻ ነው። ስለዚህ እግዚአብሄር ግለሰቦችን ቤተስብን እንደዚሁ ቤተክርስቲያንንም ያድሳል። ይህን መልዕክት ለመስማት የታደማችሁ መንፈስ ቅዱስ በዚህ መልዕክት ተሃድሶን እንደሚሰጣችሁ እናምናለን
ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የእግዚአብሔር ልጆች የሆኑ ሁሉ ህይወታቸው የሚመራው በውስጣቸው በሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ ነው:: ሰለዚህ አማኝ በውስጡ ያለውን የሚያስተምረውን ከክፉ የሚጠብቀውንና በቀና ጎዳናው የሚመራውን የእርሱን የመንፈስ ቅዱስን ማንነት ደግሞም አሠራሩን እንደሚገባ ማወቅና መረዳት ይገባዋል:: በዚህና በሚቀጥሉት ተከታታይ ትምህርቶች የመንፈስ ቅዱስን ማንነት አሰራርና አመራሩንም እንማራለን::
በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሁሉ በፊቱ ሞገስ አግኝቷል:: ይህ በጌታ ፊት ያለው ሞገስ የሚጠበቀው ግን አግዚአብሔርን በመፍራት ህይወት ውስጥ እስከኖረ ድረስ ብቻ ነው:: ከዚህ በወጣ ግን በደልና መተላለፍ አመፅና ድፍረት ባለበት ከቃሉ ከፈቃዱም የወጣ አካሔድ ባለበት በዛ ሞገስ አይኖርም:: ፀሎታችንም አይሰማም:: ደግሞም ዋጋ ያስከፍለናል:: የምናልፍባቸው ሁኔታዎች የሚያስጨንቁን ቢሆኑም እንኳ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ በሆነልን ጊዜ እምነትና ተስፋ ብርታትም ይሆንልናል:: ሰለዚህ እግዚአብሔርን በመፍራት ህይወት መኖር ዋና ነገር ነው::
እግዚአብሔር የበረከት አምላክ ነው። አብርሃምን እግዚአብሔር በባረከበት በረከት ውስጥ አብርሃም በዚያ በተባረከበት ሕይወት ውስጥ ሕይወቱን ጠብቆ እንዳይኖር ብዙ ትግሎችን አሳልፏል። እግዚአብሔር በባረከን በረከት ውስጥ በታማኝነት ጸንተን በመመላለስ በረከታችንን ጠብቀን ልንኖር እንደሚገባን ይህ መልዕክት ያስተምራል።እግዚአብሄር የባረከንን በረከት ማንም ሊወስድብን አይችልም። እግዚአብሄር የባረከንን በረከት ማንም ሊሽር አይችልም ሰይጣን ግን በዚያ በረከት ውስጥ እንዳንመላለስ እኛ እና በረከታችን እንዳንገናኝ ከመስመር ሊያስወጣን ብዙ ይጥራል። በዚህ ትምህርት ውስጥ እንዴት በበረከታችን ውስጥ ጸንተን ሥፍራ ሳንለቅ መጠበቅ እንዳለብን ያስተምረናል።
እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ ያለው ፍቅር በሙላት የተገለጠው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ አለም በስጋ በመገለጡ በሞቱና በትንሣኤውም ምህረትንና ደህንነትን በማወጅ ነው:: ይህ የተገለጠው የእግዚአብሔር ፍቅር እኛን ከነካን በኃላ እኛም ለዚህ ፍቅር የምንሰጠው ምላሽ በተለያየ መንገድ ይገለጣል:: በጌታ ፊት የምናሰቀድመው ምን ሊሆን እንደሚገባ እንድናስተውልና በቅን ልብ ልንሆን የተገባ ነው:: - በፍቅሩ ውስጥ ከሆንን በሰላሙና በእረፍት ውስጥ እንሆናለን:: በመባከን ህይወት እንዳንጠመድ ይልቁንም በእግሩ ስር ልንሆን ከቃሉም ማዕድ ልንመገብ የእርሱ ፈቃድ ነው::
ከእግዚአብሄር ጋር ሳይስማማ የምድር ሕይወት ዘመኑን የሚኖር ሰው ሰላም እና ደስታ እፎይታ የሌለበት ህይወትን ይኖራል፡ከእግዚአብሄር ጋር በተስማማንበት ነገር ላይ ሁሉ ነገር ዕረፍት እና ደስታ አለበት። ለሌሎች ያልተመቸ ነገር ከእግዚ ጋር ብቻ ሰለተስማማን ያ የማይመች ነገር ለኛ የተመቸ ይሆናል። በቃሉ ውስጥ ከእግዚአብሄር ጋር በመስማማታቸው ብቻ በረሃብ ዘመን የጠገቡ ሰዎችን ታሪክ በዚህ ትምህርት ላይ በስፋት ተጠቅሰዋል። በዚህ መልዕክት ከእግዚአብሄር ጋር ያልተስማማንባቸውን ጉዳዮች እንድናስተውልባቸው ይናገረናል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ቤተ ክርስትያንን ሊከፍል ሊለያይ የሚመ'ጣ የወንጌል ትምህርት ወደ ቤተ ክርስትያን ሲመጣ የአንድነት እና የህብረት መሰረት ሆነን መቆም የምንችለው እንዴት ነው? 2. ሰው እግዚአብሔርን እያወቀ መከተል የሚችለው እንዴት ነው? ሳያውቅ ከመከተል ኪሳራስ ለመውጣት ምን ማድረግ አለበት? 3. በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውንና ያልሆነውን ስለት አውቀን መመለስ የለብንም ወይ? 4. እጊዚአብሔር አብረውን እንዲቆሙ የሰጠንን ሰዎች ማንነታቸውን አካሄዳቸውን ማወቅ አለብን ወይ? 5. በልማድ በምናደርገውና በእምነት በምናደርገው መካከል ያለውን ግንኙነት ብታብራራልን? 6. የምናደርገው ነገር ከእግዚአብሔር ነው እያልን ወደ ብርሃን መምጣት የሚያቅተን ለምንድን ነው? 7. ሁለት ዐይነት ሰዎች አሉ የራሳቸው መንፈሳዊ ትክክል የሚመስላቸውና ሌሎቹ ደግሞ የእግዚአብሔር መንፈሳዊ ትክክል ነው የሚሉ የሚለውን ብታብራራልን? 8. ካልጠበቅነው ነገር እግዚአብሔር መልስ አለው የሚለው ይብራራልን። 9. የእኛ ነገር የእግዚአብሔርን ግቡኝት እንዲፈጥን ያደርገዋል ወይ?
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ከጨለማው አለም ወደ ብርሃኑ መንግስት ካመጣን በኃላ ብቻችንን የተወንና በራሳችን እንድንቆም የለቀቀን አይደለም:: ነገር ግን ዘወትር በእጁ የተያዝንና የተጠበቅን ነን እንጂ:: የምናልፍበትና ያለንበት ሁኔታ የሚያስፈራ ደግሞም ብቻችንን የሆንን የተተውንም መስሎ ቢታየንም እንኳ በዚህም ውስጥ አጁ ይዛናለች:: ትመራናለችም:: የጠራን ጌታ እርሱ የታመነ ነው:: - ጌታ ይረዳኛልና አለፈራም ተብሎ እእደተፃፈ በእምነት ፀንተን እንቁም::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በአይምሮ ህመም ያሉ ሰዎች እንዴት ነው ወደ ንስሀ መምጣት የሚችሉት? 2. “አንድ መንፈስ፣ አንድ ልብ ነበራቸው” የሚለውን ብታብራራልን? 3. ዛሬ እንደ እስጢፋኖስ በህይወታቸው ምስክር የሚሆኑን ሰዎች ስለሌሉ ነው እኛ በህይወታችን ምስክር መሆን ያልቻልነው? 4. ልጆች መጠመቅ ያለባቸው በስንት እድሜአቸው ላይ ነው? 5. ህይወታችን ጌታ ከሆነ ለምንድን ነው በህይወታችን ተቅበዝባዥ የምንሆነው? ከዚህስ እንዴት ነው መውጣት የምንችለው? 6. ኑሮአችንን ከጌታ ጋር ካነካካን የመለየት ስጦታ አለን ማለት ነው ይህ ከሌለን ግን መንፈሳዊ ህይወታችንን መጠበቅ እንችልም የሚለው ሀሳብ ቢብራራልን? 7. ጌታ በመጀመሪያ የሚያየው የእኛን ማንነታችንን ነው ከዛ በኋላ ነው ፀሎታችንን የሚሰማው ሀሳብ ቢብራራልን?
በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከክፉው ወጥመድ ከጨለማው ያመለጠ አማኝ መግባትና መውጣቱ ደግሞም ሁለንተናው በጌታ ጥበቃ ውስጥ ይሆናል:: ይሁን እንጂ ጠላት ዝም ብሎ አይቀመጥምና ውጊያ አለበት:: ውጊያውም መንፈሳዊ ውጊያ ነው:: የአማኝ ህይወት ከሁሉ አስቀድሞ ትህትናን የተሞላ ደግሞም ራሱን ዝቅ ያደረገና ራሱነ የሚገዛ ሊሆን አንደሚገባና አንዲሁም ለመንፈሳዊ ውጊያ ሊኖረን የሚገባውን ዝግጅትና በዚህ በተሸነፈው አለም እለት እለት በአሸናፊነት እንዴት ልንመላለስ አንደምንችል በዚህ መልዕክት በስፋት ተዘርሯል::
ፀሎት አንዱ የአማኝ የህይወት ክፍል ነው:: ሰለዚህ ዘወትር የምንከውነውና የምንኖረው ነው:: ፀሎት በአግዚአብሔር ፊት ቀርበን ከእርሱ ጋር የምንነጋገርበት ለእርሱ የለንንም ወዳጅነት የምንገልጥበትና ከእርሱ ዘንድ ምክርና መመሪያ የምንቀበልበት ነው:: መቼና ለምን እንፀልይ? እንዴትና ሰለምን እእፀልይ? ለሚሉትና ለሌሎችም ጥያቄዎች የተብራራ መልስ በዚህ ትምህርት እናገኛለን::
ብዙ ደስ የሚያሰኙ ነገሮች በዚህ ምድር ሊኖሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን ጊዝያዊ አና ተለዋዋጭ ናቸው። የማይለዋወጥ ዘመን የማይሽረው የዘለኣለም ደስታ ግን የሚገኘው በጌታ በአየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።
የኣንድ መንፈሳዊ ሰው ከፍታ፣ሙሉ ህይወት አና ክፍተት የሌለበት የሚሆነው፣ አየሱስ ይበቃል ወደሚል መረዳት ሲደርስ ነው። አየሱስ ይበቃኛል ስንል አርሱ ሁሉ በሁሉ ነው ማለታችን ነው። ማርያም ቃሉን ልትሰማ በኢየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጣ ነበረች፣ማርታ ግን አገልግሎት ስለ በዛባት ባከነች። ኢየሱስም መልሶ ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት። ይህ ጥቂት ወይም አንድ ነገር ለሁሉም መልስ አና ሁሉንም የሚሞላ ነው፣ አርሱም አየሱስ ነው። ሉቃስ 10:41-42
ማርያምና ሌሎችም የእግዚአብሔርን ቃል በመተማመን የጠበቁ ሰዎች፣ በትልቅ ድል ውስጥ እንዳለፉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተፅፎልናል። የምንሰማውን ቃል ሁለንተና ካደረግነው እንጠብቀዋለን፣ በመጠበቃችን ደግሞ እንከብራለን ያልጠበቅነው ቃል ደግሞ ሕይወት አይሆንልንም። አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ያለን ቃልና እኛ የምናልፍበት ሁኔታ በጣም የተራራቀና ያለንን የሚያስጥል ሊሆን ይችላል ሆኖም ግን እግዚአብሔር አንዱ መንፈሳዊነትን የሚያለማምደን መንገዱ በመጠበቅ ውስጥ ነው።
እየሱስ ማን ነው ዮሃንስ ወንጌል 4:10 እና 4:39-45
እየሱስ ማን ነው? ዮሐ. 4:10 እና 4:39-45 ክፍል 2
እየሱስ ማን ነው?ዮሐ.4:10 እና 4:39-45 ክፍል 4
እየሱስ ማን ነው ዮሐ. 4:10 እና 4:39-45 ክፍል 3
እየሱስ ማን ነው?ዮሐ.4:10 እና 4:39-45 ክፍል 5
ኢየሱስ ማን ነው? ሉቃ.19:1-9 ክፍል 6
ኢየሱስ ማን ነው? ሉቃ.5:27-39 ክፍል 8
ኢየሱስ ማን ነው? መኃልይ.5:2-9 ክፍል 7
ኢየሱስ ማን ነው? ሉቃ.5:27-39 ክፍል 9
እየሱስ ማን ነው? ሉቃ.15:11-24 ክፍል 6
እየሱስ ማን ነው? 1 ጢሞ.1:5 ክፍል 11
እየሱስ ማን ነው? 2ቆሮ.10:1-6 ክፍል 14
እየሱስ ማን ነው? ሉቃ.4:1-13 ክፍል 15
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 16 ሮሜ ምዕራፍ 7:4-6
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 18 1ኛ ጢሞቴዎስ - ምዕራፍ 1:8-11
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 17 ሮሜ ምዕራፍ 8:9-11
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 19 ቆላስይስ ምዕራፍ 2:3
ኢየሱስ ማን ነው? ቆላ.ምዕራፍ 1:13-14 ክፍል 20
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 21 ቲቶ ምዕራፍ 3:5 እና ማቴ ምዕራፍ 1:21
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 22 ሮሜ ምዕራፍ 7:4-12
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 23 1ኛ ዮሐ2:15,16 ገላ 1:4 ሐዋ 2:40
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 24 ቆላ.ምዕራፍ 1:1-8
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 25 ቆላ.ምዕራፍ 1:7-12
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 26 ቆላ.ምዕራፍ1:8-12
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 27 ቆላ.ምዕራፍ1:13-23
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 28 ቆላ.ምዕራፍ1:21-29
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 29 ቆላ.ምዕራፍ1:24-29
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 30 ቆላ.ምዕራፍ 2:1-5
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 31 ቆላ.ምዕራፍ 2:1-9
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 32 ቆላ.ምዕራፍ 2:6-15
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 33 ቆላ.ምዕራፍ 2:7-19
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 34 ቆላ.ምዕራፍ 2:12-15
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 35 ቆላ.ምዕራፍ 2:16-23
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 36 ቆላ.ምዕራፍ 3:1-4
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 37 ቆላ.ምዕራፍ 3:6-13
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 38 ቆላ.ምዕራፍ 3:12-17
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 39 ቆላ.ምዕራፍ 3:18-25
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 40 ቆላ.ምዕራፍ 4:1-5
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 41 ቆላ.ምዕራፍ 4:7-9
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 42 ቆላ.ምዕራፍ 4:10-12
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 43 ቆላ.ምዕራፍ 4:12-18
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 44 ቆላ. ከምዕራፍ1-4
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 45 ቆላ. ከምዕራፍ 1:24-25
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 46 ቆላ. ከምዕራፍ 4:7-8
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 47 ቆላ. ከምዕራፍ 1:28-29
የእህቶች ፕሮግራም (በአውሮፓ ሕብረት የተዘጋጀ)- ክፍል 1
የእህቶች ፕሮግራም (በአውሮፓ ሕብረት የተዘጋጀ)- ክፍል 2
የእህቶች ፕሮግራም (በአውሮፓ ሕብረት የተዘጋጀ)- ክፍል 3
መንፈሳዊ ተሀድሶን ወደ አማኝ ህይወት የሚያመጣው እግዚአብሔር ራሱ ነው:: አላማውም የሰውን ሁለንተና ወደ ራሱ ፈቃድ መመለስ ደግሞም በቤተክርሰቲያን በአማኞች መካከል ክብሩን በመግለጥና ሰዎችን ወደ ህይወት ወደ ብርሃን ማምጣት ነው:: መንፈሳዊ ተሀድሶ ሲመጣ ምስጢር ይገለጣል:: የንስሃ ጥሪ ለሰው ሁሉ ይሆናል:: የእግዚአብሔርም የማዳኑ ጉልበት ይገለጣል:: ድንቅና ተአምራት ይሆናልም:: በዚህ መልእክት እግዚአብሔር መንፈሳዊ ተሀድሶን ወደ ህይወታችን የሚያመጣባቸውን መንገዶች እንማራለን::
በዚህ ምድር ስንኖር በአንድም ወይም በሌላ ትንሽም ይሁን ትልቅ ሰው ሁሉ የራሱ የሆነ አንድ ተስፋ የሚያደርገው የሚኖርለት ነገር አለው:: ነገር ግን ከእግዚአብሔር የሆነ ደግሞም የተበረከ አማኞች ሁሉ እለት እለት የሚኖሩለት ተስፋ አለ:: እርሱም የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ በክብር መምጣት ነው:: በዚህ መልዕክት ይህን የተባረከ ተስፋ እለት እለት እነዴት ባለ ህይወት እየተጠባበቅን ልንኖር እንደሚገባን እንማራለን::
አማኝ በውስጡ ያለውን የሚመክረውን የሚወቅስና የሚገስፀውን በመንገዱም በቀና ጎዳና የሚመራውን መንፈስ ቅዱስን በቃሉ እንደተገለጠው ማወቅ እምነታችንን ያሳድጋል:: በፈተና ውስጥም ፀንተን መቆም እንችላለን:: በዚህ መልዕክት መንፈሰ ቅዱስ ሁሉን የሚያይ ሁሉ በፊቱ የተገለጠ ደግሞም በሁሉ ላይ ስልጣን ያለው ሁሉን ቻይ መሆኑ እንማራለን::
ፀሎት ለአማኝ የህይወቱ ክፍል እለት እለት የሚተጋበት ደግሞም በእግዚአብሔር ፊት በእምነት የሚቀርብበት ሥልጣን ነው:: በእግዚአብሔር ፊት የሚቀርብ ፀሎት የእግዚአብሔርን ታላቅነትና ሁሉን ቻይነት የሚያውጅ ነው:: በዙሪያችን ከምናያቸው አስፈሪና አስጨናቂ ነገሮችና ሁኔታዎች ይልቅ እግዚአብሔርን አግዝፎ አተልቆ የሚያሳይ ነው:: በእርግጥም እግዚአብሔር እርሱ ትልቅ ነውና:: ይህ መልዕክት አማኝ በማን ፊት ምን እያየ መጸለይ እንዳለበት የምንማርበት ነው:
ጌታ ኢየሱስን የተቀበልነው ደግሞም የምንከተለው ለህይወት ነው:: በዚህ አለም ስንኖርም እርሱ ጌታችን ብቻ ሳይሆን ነገር ግን የቅርባችን ችግራችንንም የምናካፍለው ወዳጃችን ነው:: የጠየቅነው ሁሉ አንዳይመለስ የፈለግነውንም ሁሉ እንዳናገኝ ግልፅ ነው:: ይሁን እንጃ ሁሉ ለመልካም ነው::ለበጎ ነው:: በጊዜውም አለጊዜውም በጌታ ላይ ባለን እምነት ፀንተን እንቁም:: ሰለዚህ በህይወታችነ ቀዳሚው በነገሮችና በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ ደግሞም የማይናወጥ በጌታ ላይ ያለን እምነት ነው::
እግዚአብሔር በህይወታችን የሚሰራውን ሁሉ በራሱ ጊዜና በራሱ መንገድ ለራሱ ክብር ይሰራል:: በእኛ ሚዛን ትልቅና ትንሽ ወይም ከባድና ቀላል የምንለው ጉዳይ ሊኖር ይችላል:: ይሁን እንጂ በእግዚአብሔር ፊት ሁሉም ነገር የእርሱን ክብር የሚገልጥበት ነውና በራሱ ጊዜና ሁኔታ ወደ ጉዳያችን ይመጣል:: የአማኝ ድርሻው በእምነት መቆም ደግሞም በተስፋ መፅናት ነው:: የጉዳያችን ክብደት ደግሞም የጊዜው ርዝመት እምነታችንን ሊፈትን ተስፋችንንም ሊያጨልም ይችላል:: ጌታ ግን ከእምነታችንም ሆነ ተስፋ ካደረግነው በላይ ነው:: ደግሞም እርሱ ተስፋን የሰጠ የታመነ አምላክ ነው::
መታዘዝ በአማኝ የየእለት የህይወት ጉዞ ውስጥ ዋና የሆነና ደግሞም ከጌታ የተማረው ህይወት ነው:: ሰለዚህ በመንፈሳዊ ህይወት ጉዟችን ቆም እያልን ራሳችንን መጠየቅና ምናልባት ከመታዘዝ የጎደልንበት እንዳለ በጌታ ፊት ራሳችንን ልናዋርድና ልንመረምር የተገባ ነው:: አማኝ እለት አለት ራሱን ሊጠይቅ ደግሞም ሊኖርባቸው ከሚገቡት ትእዛዞች ጥቂቶቹን ከዚህ መልእክት እንማራለን::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ለምንድን ነው አይሁዶች ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ያልተቀበሉት? 2. ቤተ ክርስትያን ስለ አይሁድ ምን ትላለች? 3. አይሁድ ስለ እምነት ምን አመለካከት አላት ከ3ተኛው ክፍለ ዘመን እስከ 21ድኛው ክፍለ ዘመን? 4. ላባችን እየተቃጠለ ዐይናችን ሊከፈት የማይችልበት መንገድ ምንድን ነው? 5. ድሆችን ማሰብ ትተን እኛ የሚመቹንን አብሮ ለመሆን ስንፈልግ ይህ ለቤተ ክርስትያን መውደቅ ምክናያት ሆናል የሚለው ይብራራልን። 6. ሰው ደህንነትን ከተቀበለ በሗሏ ወደ መንፈስ ቅዱስ ሙላት መምጣት የለበትም ወይ? መሞላቱስ ከግለኝነት ህይወት ወደ ህብረት ህይወት እንዲመጣ ይረዳዋል ወይ? 7. እነ ጳውሎስ እስር ቤት እያሉ ይዘምሩ የነበሩት ዝማሬ ህይወታቸው ስለሆነ ነው ወይ? 8. ከእግዚአብሔር መንፈስ ሳይሆን ሰዎች ትክክለኛ ትንቢት ሊናገሩ ይችላሉ ወይ? ከቻሉስ እንዴት ነው መጠንቀቅ የምንችለው?
በዚህ ትምህርት ውስጥ ረዓብ የተባለች፣ ከአብርሐም ዘር ያልሆነች፣የተቀበሉት እንኳን ለማመን የተቸገሩበትን የእግዚአብሔርን የበላይነት፣ በሰማይም በምድርም እርሱ ብቻ አምላክ መሆኑን የሰማች፣ የሰማችውን ደግሞ አምና የተቀበለች ሴት እንዴት አድርጋ አገሩን ሊሰልሉ የተላኩትን ሁለቱን ሰዎች ሸሺጋ አንዳዳነች፣ እንዲሁም ራሷንና ቤተሰቦቿን ከጥፋት እንዳተረፈች እናያለን።
ተስፋውን የሰጠው እግዚአብሔር ከሆነ፣ እርሱ የታመነ እና የተናገረውን የሚያደርግ አምላክ መሆኑን በማመን፣ ምንም እንኳን የሕይወት ውጣ ውረድ ቢበዛም ጌታን በትዕግስትና በዕርጋታ መጠባበቅ ያስፈልገናል። እግዚአብሔር የሰጣቸውን ተስፋ ደግሞ እየተጠባበቁ ለአሉት ሰዎች እንቅፋት ላለመሆን ዘወትር እራሳችንን ልንመረምር ይገባናል።
የቅዱሳን ጠላት፣ ሰይጣን ሁል ጊዜ በውጊያ ላይ እንዳለ በማወቅ፣ ክርስቲያን በጌታና በሃይሉ ችሎት የበረታ ሆኖ እንደ ወታደር ነቅቶ መጠበቅ አለበት። የአለም ጨውና ብርሃን መሆኑን በመረዳት፣ ከማንኛውም ሐጢያትና ዐመፃ በመራቅ፣ የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ፣ ደግሞም የድሉ ባለቤት መሆኑን አውቆ በእምነት መኖር አለበት።
የሰው ልጅ አግዚአብሄርን የሚፈልግ ባህሪይ የለውም፣ ጌታ ግን የሰውን ህይወት ለማዳን የሚጠቀምበት አንዱ መንገድ በችግር ውስጥ አርሱን አንድንፈልግ ማድረግ ሲሆን፣ የሰው ድርሻ ደግሞ በሚያልፍበት ማንኛውም ችግር አግዚአብሄርን ማመን ነው። እምነት ነገራችንን ሁሉ ጌታ ወደ አለበት ያደርሳል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሰው ጌታን ሲቀበል ወዲያው መንፈስ ቅዱስ ይሞላል (ያድርበታል) ወይ? 2. ሰው ጌታን ሲቀበል በመንፈስ ቅዱስ ከታተመ ለምን ለመንፈስ ቅዱስ ሙላት መፀለይ እለበት? 3. በመንፈስ ቅዱስ ባንሞላ የሚጎድልብን ምንድን ነው? 4. የመንፈስ ቅዱስ በሙላት መፈለግ አለብን ወይ? 5. መንፈስ ቅዱስን እንዴት ነው የምንሞላው? 6. በህይወታችን ጌታ የተናገረን ሲለዝምብን ለምንድን ነው የሚጨልምብን?
በዘመኑ ሁሉ በተሰጠው የአገልግሎት ስፍራ በታማኝነት አገልግሎ በእድሜው መጨረሻ ላይ የህዝቡን መሪዎች ሰብስቦ ሊከተሉ የሚገባውን ስርዓት ያሳሰበበትንና በእግዚአብሔር ፊት በጥንቃቄ ደግሞም በትጋት ሊሆኑ እንደሚገባ ያስጠነቀቀበትን ደግሞም ለእኛ ለዛሬው ህይወታችን የሚሆነውን የምክር ቃል በዚህ መልዕክት እናገኛለን:: በእግዚአብሔር አብሮነት ውስጥ ያለ ህዝብ ለእግዚአብሔር ለፈቃዱ የሚታዘዝ ራሱንም ከርኩሰትና ከነውር የሚቀደስ በዘመኑ ሁሉ ከአምላኩ ጋር የተጣበቀ ሊሆን ይገባል::
የእግዚአብሔር ቃል እውነትና የታመነ ነው፣ ጌታም እንደቃሉ ነው። እኛም እግዚአብሔርን እንደ ቃሉ ካየነው፣ የምናልፍበት ማንኛውም ከባድ የህይወት ውጣ ውረድ ይቀልልናል። በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ለሰው አይምሮ የማይቻል የሚመስሉ ሁኔታዎች ተፅፈዋል ሆኖም ግን አግዚአብሔርን በቃሉ ያዩትና እንደ ቃሉ የተቀበሉት፣ መከራቸውን ሁሉ በድል አልፈው፣ በረከታቸውን ተቀብለዋል።
ጌታ በህይወታችን ያደረገውን የማዳኑን እውነት ምህረትና ቸርነቱንም በመመሰከር ልንመላለስ የእለት ተእለት ኑሮአችንም የህንኑ የብርሃን ህይወት ሊያንፀባርቅ የተገባ ነው:: ጌታም እንደ ተስፋ ቃሉ ለዚህ የሚረዳንን ብቃትም የሚሆነንን ፀጋ ይሰጠናል:: ይህ መልዕክት የማርያምን የማርታንና የዓልአዛርን ህይወት በመዳሰስ አኛነታችንን እና ከእነርሱም ህይወት ልንማር የሚገባውን ያሳያል::
የአማኞች በምድር ላይ መኖር የእግዚአብሔርን መንግስት ለማወጅ ነው:: ለማስፋትም ነው:: በዚህ የጨለማው አለም የእግዚአቤሔር መንግስት የምትሰፋው በመውረሰ ነው:: በመማረክ ነው:: ይህም የሚሆነው አማኞች የእግዚአብሔር ልጆች በፀሎት ሆነው መንግስትህ ትምጣ እያሉ የኢየሱስ ክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ በማወጅ ደግሞም በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ዝቅ በማለት በትህትና በቅድስናና በፅድቅ በመመላለስ በኑሮ በመስከር ነው:: በዚህ መልዕክት ስለ እግዚአብሔር መንግስት ስርአት ደግሞም በውስጧ እንዴት ባለ ሁኔታ ልንኖር እንደሚገባ በስፋት እንማራለን::
የፀሎታችን ግብ የመጀመሪያው ለእግዚአብሔር ክብርን ያመጣ ዘንድ ያለመ መሆን አለበት:: ጌታ ኢየሱስ በምድር በስጋ በነበረበት ጊዜ ይናገር ከነበረውና ከፀሎቱም የምናየው ይህንኑ ነው:: የትምህርቱም ሆነ የፀሎቱ አላማ አባቱን ማክበር ነው:: እግዚአብሔርን የሚያከብር ፀሎት መልሱ የፈጠነ ነው:: ከፀሎቱ መልስ በላይ የበለጠ እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ ያመጣናል:: እምነት ተስፋና መፅናናት ሀይልም ይሆንልናል:
በቤተክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ አንዱና ዋናው አገልግሎቱ ኢየሱስ ክርስቶስን መግለጥ ነው:: ማክበርም ነው:: የእውነት መንፈስ አርሱ መንፈስ ቅዱስ በአማኞች ውስጥ የሚኖር ወደ እውነት የሚመራ የሚያፅናና እና በተስፋ እንድንፀና በተዕግስት እንድንሆን ደግሞም በፍቅር እንድንኖር ያደርጋል:: ፈቃዳችንን ለእርሱ ባስገዛን መጠን መንፈስ ቅዱስ እንደወደደ ለአካሉ ጥቅም ይሆን ዘንድ ፀጋን ይሰጣል:: ፈቃዱንም ያደርጋል::
ለሚታዘዝ ለእርሱ ከእግዚአብሔር ዘንድ በረከት ደግሞም ክፉውን የሚቃወሞበት ሀይልና ጉልበት ይሆንለታል:: መታዘዝ ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆንም እንኳ ፍሬው ግን በብርሃን የተሞላ የእግዚአብሔርን ክብር ክንዱንም የምናይበትና ለምስጋናም በፊቱ የሚያቆመን ነው::
የሰው ፈቃድ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ሲተያይ ሰማይ ከምድር እንደሚርቅ እንዲሁ የራቀ ነው:: ነገር ግን እግዚአብሔር ፀጋን እየሰጠ ደግሞም በራሱ መንገድ በመምራት ሰውን አሰቀድሞ ወደ ተፈጠረለት ወደ ፈቃዱ ያመጣዋል:: ሰው ግን ራሱን ባዶ ሊያደርግ ደግሞም በእርሱ ያለውን የጌተን ፈቃድ ለማድረግና ለእርሱም ለመኖር መምረጥ ይኖርበታል:: ይኸውም በስጋ ሳይሆን ነገር ግን አይናችን ተከፍቶ አይተን የምንመርጠው ነው:: - ሰው ራሱን በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ያገኘበት ሰአት ያ እጅግ የተወደደ ሰአት ነው::
እግዚአብሔርን እንደትናገረው ካላመንን አይመችንም ስንታመነው እንደቃሉ ስናየው ንብረታችን አቅማችን ነው ችግር የለም ማለት አይደለም ከችግር በላይ ነው ማለትና ማመን ግን ሃይል ማግኘት ነው ነገር ግን ሰይጣን ይህ እውነት እንዳይገባን ይታገልናል ስለዚህ ጨለማውን እያየን ተስፋ መቁረጥ የለብንም
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ፍርድ ካለበት ፀሎት እንዴት ነው መውጣት የምንችለው? 2. የወንጌል ትኩረት ወደ ራስ ጥቅም የለወጠው ምንድን ነው? 3. ወንጌልን ስንመሰክር ስለ ወንጌል መናገር ያለብን ምን መሆን አለበት? 4. በቤተ ክርስትያን እናት ሳይሆኑ እናት የሆኑ አሉ የሚለው ሀሳብ ቢብራራልን።
እግዚአብሔር እርሱ በሰማይና በምድር አምላክ ነው::ብላ ያመነች ደግሞም የመሰከረች ረዓብ ከሚጠፉት ጋር አብራ አልጠፋችም:: ምንም ታናሽና ደካማ ብንሆን በእምነት በፊቱ እንሁን እንጂ እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን ሊሰራ ፈቃዱ ነው:: በዚህ መልዕክት ትናንት በረዓብ ህይወት ድንቅን ያደረገ ጌታ ዛሬም በእኛ እንዴት እንደሚሰራ እንማራለን::
ኢያሱ በፊቱ ተሰብስቦ ላለው ለእስራኤል እግዚአብሔርን ፍሩ ብሎ አወጀ::በጉዞው ሁሉ ደግሞም ወደፈት ሊኖርበት ባለውም ምድር የእስራኤል ጉልበት እግዚአብሔርን መፍራቱ ነውና:: በክርስቶስ ኢየሱስ ከሞት ወደ ህይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የተጠራን አኛ ሁልጊዜም በልባችን ሊኖር የሚገባው አንድ ነገር እርሱም ከራሳችን የሆነ አንዳች የሌለ ደካሞች እንደሆንን ነው:: በመንግስቱ ውስጥ ግን በእግዚአብሔር ሀይል እንወጣለን እንገባለን ደግሞም በእርሱ ሀይል እናገለግላለን እርሱንም ለማክበር እንኖርማለን::
የአማኝ መንፈሳዊ ጉዞ ከሀይል ወደ ሀይል ከክብርም ወደ ክብር ነው:: ደግሞም የማያቋርጥ ለውጥ በህይወቱ ይኖራል:: በህይወታችን የሚኖረው ለውጥ እንዲያድግ እግዚአብሔር የወደደው የልጁን መልክ ወደ መምሰል ነው:: ይህ ደግሞ ራስን ከመካድና ዝቅ ከማለት ደግሞም ከመታዘዝ ይጀምራል:: በዚህ መልዕክት በቀደሙት የተለያዩ ሰዎች በህይወታቸው የተገለጠውን የለውጥ አይነት በማየት ዛሬ ደግሞ ለእኛ የህይወት ለውጥ ይጠቅመን ዘንድ በስፋትና በዝርዝር ቀርቧል::
ቃሉን ሰምቶ መታዘዝ የሉቃስ ወንጌል 10: 1-11 መታዘዝ ቃሉን ከማድመጥ ይጀምራል። ጌታ እየሱስ በመጀመሪያ ደቀ መዛሙርቶቹ እንዲለማመዱ የፈለገውና ዛሬም አማኞች የሆንን ሁላችን ልናደርገው የሚገባን፣ ለሰማነው ለእግዚአብሔር ቃል መታዘዝን ነው። ለክርስቶስ ያለንን ፍቅር የምንገልፀው፣ ቃሉን በመስማትና በመታዘዝ ሲሆን፣ ይህ ለቃሉ በመታዘዝ መኖር ደግሞ ክርስቶስን ወደ መምሰል ያደርሰናል።
እግዚአብሔር በባሕሪው ማንንም አይረሳም። በሰው አይምሮ ነገራቸው ሁሉ ያለቀና የተረሱ የሚመስሉ ብዙ ሰዎች በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደ ምሳሌነት ተጠቅሰውልናል፣ በመጨረሻ ግን በእግዚአብሔር ታስበው፣ ዛሬም ያለፉበትን የሕይወት ውጣ ውረድ ስንማር ያስደንቀናል። እግዚአብሔር ፍርድ የሚያደላድለው፣ ሰውን የሚያስብ አምላክ በመሆኑ ነው።
ለተቀበልነውና በስሙ ለምናምን፣ የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን ስልጣን ተሰጥቶናል። ይህንን የዘለአለም ሕይወት ተስፋ ለመጨበጥ፣ ልጅ ከመሆን ይጀምራል። እንደ ልጅ፣ ያዳነንን እርሱን ጌታችንን ደስ ለማሰኘት ስንተጋና፣ የተስፋችን ፍፃሜ የሆነውን አምላካችንን ለመገናኘት ስንናፍቅ፣ ይህንን ተስፋ ለመጨበጥ የሚያስችል ፀጋ ይለቀቅልናል።
ሁሉም ፀጋ የሚለቀቀው ሰው ለጌታ ፈቃድ ሲመች ነው። ለፈቃዱ ለመመቸት ከራሳችን ፈቃድ ወጥተን ለእግዚአብሔር መሆንና አርሱ የሚወደውን መውደድ ይጠይቃል ደግሞም የእግዚአብሔር ፈቃድ ደስታችን ሊሆን ይገባል። ለሰው ትልቁ የመንፈስ ኪሳራ፣ ለእግዚአብሔር ፈቃድ ሳይመች ሲቀር ነው።
የዲያብሎስን ሽንገላ ለመቃወም፣ ክርስቲያን በክርስቶስ ፅድቅ ውስጥ መሸፈን አለበት። ትግሉ ከሰው ጋር ሳይሆን ከሰዎች ጀርባ ካለ ከክፋት መንፈሳዊ ጋር መሆኑን በመረዳትና የሰይጣንን ሐሳብ ላለመሳት፣ በእግዚአብሔር ቃል እውነት ማደግ እንዲሁም በፅድቅና በቅድስና ሊኖር የተገባ ነው።
ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የእግዚአብሔር ልጆች የሆንን እና በመነንፈስ ቅዱስም የታተምን ሁላችን መሪያችን እርሱ መንፈስ ቅዱስ ነው:: እርሱ የአሁኑን ደግሞም ወደፊት የሚሆነውንም የሚያውቅ ጌታ በቀናው ጎዳና በጽድቅና በቅድስና በእውነትም እንደ ፈቃዱ ይመራናል:: በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ እንሁን የእኛ መሰጠት ደግሞም ለምንሰማው ድምፅና ምሪት መታዘዝ እሺ ማለት ከእኛ የሚጠበቅ ነው::
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጌዴዎን የተባለ ስው ምድያማውያንን ፈርቶ በተሸሸገበት ስፍራ፣ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት አንተ ጽኑዕ ኃያል ሰው፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው አለው። ጌዴዎን የነበረበት ሁኔታና መልአኩ ተገልጦ የነገረው ቃል በፍጹም አብሮ የሚሄድ አልነበረም። ነገር ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ ከህዝቡ ጋር ነው። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የመሆኑ መለኪያው የምናልፍበት ጊዚያዊ ሁኔታ ሳይሆን፣ የነገረን ቃሉ ነው። እስከ አለም ፍጻሜ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ ስላለን፣ በምናልፍበት በማናቸውም ሁኔታ፣ በክርስቶስ እየሱስ ያገኘነውን አብሮነት እያጣጣምን ልንኖር ይገባናል።
እግዚአብሔር የጠራን ለብርታት ሳይሆን፣ የእርሱ ኃይል መገለጫ እንድንሆን ነው። ጌታ ጳውሎስን ጸጋዬ ይበቃሃል ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና እንዳለው፣ ዛሬም የእግዚአብሔአ ፀጋ በእኛ የሚገለፀው በበቃንበት ሳይሆን ባልበቃንበትና ኃይል ባጣንበት ነው። የሰው ውድቀትና ኪሳራው፣ ከድካሙ ይልቅ በራሱ ሀይል መመካት ሲጀምር ነው።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በብሉይ ኪዳን “ በሀጢያት ምክንያት ሴቶቻችሁ ያምጣሉ ፅንሱ በቀጥታ አይወጣም ልጆቹም አህምሮ የጎደላቸው ይሆናሉ።” የሚለው ቃል ይብራራልን። 2. ምህረት ማድረግ ምርጫ ነው ወይ? 3. ይቅርታ ማለት ነገርን መርሳት ነው ወይስ ነገሩ እያለ መተው ነው? 4. የእግዚአብሔር ፍቃድ እንዲከናወንልን ራስን አሳልፎ መስጠት አለብን የሚለው ይብራራልን? 5. በእግዚአብሔር ፍቃድ ለመደሰት ሂደት ነው ወይ? የእግዚአብሔር ፍቃድ እኛን ለማስደሰት ሗይል አለው ወይ? ይህ መረዳት እኛን ይጠቅመናል ወይ? 6. የእግዚአብሔር ፍቃድ ከእምነት ጋር ይያያዛል ወይ? 7. እንደተነገረን ቃል መኖርና በውጭ ላሉት ተጠንቅቆ መኖርን እንዴት ነው በህይወታችን የምናስታርቀው? 8. ራሳችንን ትልቅ ባደረግንበት ሆነ ሰዎች ትልቅ ባደረጉን ነገር ጌታን ማየት ትተናል ማለት ነው? 9. ልጆችን ካደጉ በሗላ እንዴት ነው ማስተካከል የምንችለው?
እግዚአብሔር ለሰው ፊት አያደላም:: ነገር ግን እርሱ ለሚጠሩት ሁሉ ሙሉ ደግሞም ባለጠጋ ነው:: በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ባመንን ጊዜ ህይወታችን በሰማያዊ ስፍራ ተሰውሯል:: በምድር ላይ በሚኖረን ዘመን ሁሉ ደግሞ ስለ እግዚአብሔር ፈቃድ ሁለንተናችን በመለኮት ጥበቃ ውስጥ ነው::የሚሆነውና የምናልፍበት ሁሉ በእርሱ ፊት የታወቀ ነው:: በዚህም ውስጥ ታላቅነቱን ደግሞም ሁሉንቻይነቱን እናያለን
ፀሎት ማለት ሐይማኖታዊ ልምምድ ሳይሆን ከምንጠይቀውና ከምንቀበለው ያለፈ፣ በመንፈስ ቅዱስ መገኘት፣ ወደ ውስጠኛው የጌታ ህልውና ውስጥ ገብተን ከጌታ ጋር የአባትና የልጅ ሕብረት ማድረግ ማለት ነው። ለዚህም ነው መፅሐፍ ቅዱሳችን የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች ብሎ የሚመክረን።
እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው:: እርሱ የእኔ ነው :: ለሚል ደግሞም በስፍራው ፀንቶ ለቆመ ለእርሱ የታመነበት ደግሞም አለኝ ያለው ጌታ ባለበት በሁኔታው ላይ ይመጣል:: ክብሩንም ይገልጣል:: ታምኗልና:: በእኛ ዘንድ ያበቃለት ተስፋም የተቆረጠበት ጉዳያችን ሁሉን ቻይ በሆነው ጌታ የእኛ በሆነው በእርሱ ዘንድ ቀላል ነው:: ሞቷል ለምንለውም እንኳ ህይወት ይሰጠዋል:: እንዴት ይሆናል ተብሎ አይጠረጠርም
መንፈሳዊ አይኖቻችን ሲከፈቱ የምናየውና የምንሰማው ደግሞም ሁለንተናችንን የሚወርሰው የሚገዛው የሚመራውም የእግዚአብሔር ድምፅ ይሆናል:: ለተጠራንለትም አላማ እንኖራለን:: በህይወታችን የሚሆኑትን ነገሮች ሁሉ በስሜት ሳይሆን በማስተዋልና በጥንቃቄ ማየት እንጀምራለን:: አሻግረን ወደፊት ማየት እንችላለን:: በእምነት እንበረታለን ሀይልና ጉልበት ተስፋም ይሆንልናል::
የክፉ መናፍስት ሥራ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር የለውን ህብረት ማበላሸት ደግሞም በእግዚአብሔር ላይ ያለንን እምነትና መታመን መሸርሽር ያለንንም ተስፋ ማጨለም ነው:: ስለዚህ ሁልጊዜ ለክፋት በተለያየ መንገድ የሚተጋ ጠላት እንዳለብን አማኞች ልናስተውል ፀንተንም በእግዚአብሔር ቃልና በፀጋው ልንዋጋውና በአሸናፊነት መንፈስ ልንቆም ያስፈልጋል:: በዚህ መልዕክት የክፉውን አሰራርና በሌላ በኩል ደግሞ በክርስቶስ ያገኘነውን የአሸናፊነት ህይወትና የፀጋውን ጉልበት እንማራለን::
እግዚአብሔር ለእስራኤል የተናገረው የተስፋ ቃል ሁሉ ተፈፅሟል :: መንገዳቸው በበረሀ ውስጥና በብዙ ፈተናም የተሞላ ቢሆንም በእግዚአብሔር ላይ የታመኑ እንደተባለላቸውም በተስፋው ቃል የፀኑ የጉዟቸውን ፍፃሜ መዳረሻ አይተዋል:: ወደ ተስፋውም ምድር በድል በሞገስ ገብተዋል:: በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከኃጢአት ባርነት ተላቀን ከአለም ወጥተን ወደ መንግስቱ የፈለስን አኛም እንደ እስራኤል ሁሉ ለህይወት ጉዟችን የተሰጠ መመሪያ አለ:: ይህንን በዚህ መልዕክት በጥልቀት እንማራለን::
እግዚአብሔር ባሰበን ጊዜ የእርሱ ባርኮት ወደ ህይወታችን ይፈሳል:: የፀሎት መልስ ይሆናል:: ተስፋ ያደረግነውም እውን ይሆናል:: የሚሆነው ሁሉ የሚሆነው ግን በእኛ ጊዜ አይሆንምና አንዳንድ ጊዜ ተስፋ እንቆርጣለን:: ከምናልፍበት ሁኔታ የተነሳ እግዚአብሔር እኔን ረስቶኛል ለማለትም ደፍረን ይሆናል:: ጌታ ግን ሁሉን በራሱ ጊዜና ሰአት በወደደውም መንገ ውብ አድርጎ ይገልጠዋል:: እግዚአብሔር እርሱ አይለወጥም:: ዛሬም ያስባል::ይጎበኛልም:: እኛ ግን በጊዜውም አለጊዜውም በምስጋና ሆነን በፊቱ ልንቆይ ያስፈልጋል::
የአማኝ እድል ፈንታ እርሱ አንዳሰበው፣ አንደሰማው ወይም እንዳየው ሳይሆን እግዚአብሔር እንዳዘዘው ነው። አንድ አማኝ ወደ እግዚአብሔር በቀረበበት መጠን የእግዚአብሔር የሆነው ነገር በህይወቱ ስፍራን እየያዘ፣ የእግዚአብሔር ያልሆነው ነገር ደግሞ እየቀለለበት ይመጣል፣ የእግዚአብሔርን አዋቂነት በበለጠ በመረዳት በሚያልፍበት የህይወት ውጣ ውረድ ሁሉ፣ ጥያቄው ለምን? ሳይሆን እግዚአብሔር ብሏል ወይ? ይሆናል።
በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሁሉ በምድር ሲኖር ተልዕኮ አለው:: ተልዕኮውም ጌታ ኢየሱስን ለሌሎች ማሳየት ነው:: በቃልና በሰራ በኑሮ:: ይህንንም ተልዕኮ እለት እለት ለመፈፀም መታዘዝ ስርአትና እምነት ከእኛ የሚጠበቁ ናቸው:: - ለጌታ ፈቃድ ለቃሉ በመታዘዝ እንዲሁም የራሳችንን ክብር ጥለን ለሌሎች እንቅፋት ባለመሆን ደግሞም በእምነት መራመድ::
ትልቁ የአማኝ በረከት የዘላለም ህይወት የኃጢአት ሰርየት መፅናናተ ሰላምና ደሰታ የሆነው ጌታ እግዚአብሔር የእኛ መሆኑና እኛም ለእግዚአብሔር መሆናችን ነው:: ይህም በረከት ከእግዚአብሔር ነውና ከእኛ ማንም ሊወስደው አይችልም:: ሰለዚህም የአግዚአብሔር በሆኑት ላይ የበረከት ተቃራኒ እርግማን እንዳይሰራ እናያለን:: ነገር ግን ከእግዚአብሔር ፈቃድ በወጣንና ባልታዘዝን ጊዜ በህይወት ጉዟችን ሊያገኙን ያሉት በረከቶች ይያዛሉ:: ሰለዚህ ለእግዚአብሔር በመገዛት በመታዘዝም በመንገዱ በእውነትና በፅድቅ ልንሆን ያስፈልጋል::
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር አንዲሆን እየሔድንበት ካለው ከራሳችን ሀሳብ ደግሞም ከክፉ ስራችን መመለስ ያስልጋል:: እዲሁም ደግሞ በምናልፍበት በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ከተናገረን ከቃል ኪዳኑ የተነሳ እርሱ ከእኛ ጋር ይሆናል:: የተቀበልነው ተልዕኮም የወንጌል ስራ የእርሱን አብሮነት ይጠይቃልና ሰለወንጌል በምናልፍበት ፈተና ውስጥ ጌታ ከእኛ ጋር ይሆናል:: እግዚአብሔር እርሱ በቃሉ የታመነ አምላክ ነው::
በአንድ አማኝ ህይወት ውስጥ ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን ከሞት ወደ ህይወት የመጣበት ዳግመኛ የተወለደበትና የእግዚአብሔር መንግስት ዜጋ የሆነበት የጉብኝት ቀን እጅግ አስደናቂ ሁልጊዜም የሚታሰብና ደስም የምንሰኝበት ነው:: እንደዚሁም ደግሞ በተለየ ሁኔታ የእግዚአበሔር ጉብኝት ወደ ህይወታችን ይመጣል:: ሰለዚህ ከጉብኝቱ ጋር እንዳንተላለፍ ዘወትር በጥንቃቄና በተቀደሰ ህይወት እንደ እግዚአብሔርም ፈቃድ ልንመላለስ ያስፈልጋል::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በህይወታችን ወደ እግዚአብሔር ሀሳብ እንዴት ነው የምንመጣው? 2. ይሁዳ ከጌታ ጋር ሦስት ዓመት ተኩል ከቆየ በሗላ ጌታ አሳልፎ ወደ መስጠት የመጣበት ምክንያት ምንድን ነው? 3. በምናልፍበት ህይወት ላይ በእምነት ጌታ ብርሃኔ ነው ማለት የምንችለው እንዴት ነው? 4. ጌታን በህይወታችን ብቁ እንዳይሆን የሚያደርጉ ነገሮች ምንድን ናቸው? 5. በፀሎት ጌታን እንጠይቃለን ወደ ጌታ ግን አናመጣውም የሚለውን ብታብራራልን። 6. ጣርያ ነድለው ወደ ጌታ ያመጡትን ሰው ጌታ የፈወሰው ያመጡትን ሰዎች እምነት አይቶ ነው ወይስ የሰውየው እምነት?
አማኝ የተጠራው በራሱ ትግል ትክክለኛ ሰው እንዲሆን አይደለም:: ነገር ግን እግዚአብሔርን በመምሰል በፀጋው ጉልበት በሚሄድበት ሁሉ ብርሃን ለመሆን ኢየሱስን ለማሳየት ነው:: ይኸውም በቃል ብቻ ሳደሆን ደግሞም በመኖር ጭምር ነው:: በዚህ ምድር በተሰፈረው ዘመናችን በእኛ ህይወት የበራውን ብርሃን ክርስቶስን ለማብራት መጠራታችን ትልቅ እድል ነው::
የሰማነው ወይም ያየነው ነገር ሳይሆን የሞተ ነገራችን ነው ታማኝ የሚያደርገን። ከምድር ወጥተን ከስጋችን ተለይተን የላይኛውን ማየት ስንጀምርና የደህንነታችን መሰረት የሆነውን ክርስቶስን ተደግፈን በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር ስንሆን መፅናት እንችላለን። ሰው በሐይሉ አይበረታም እንደሚል የእግዚአብሔር ቃል፣ የሚያበረታን ፀጋው ነው። ሰይጣን ግን ሁልጊዜ በትጋታችን ሊያስመካን ይጥራል።
ጌታ እየሱስ የድል አምላክና ለሁሉ መልስ ነው። ለጥያቂያችን ሁሉ መልስ የሚሆነው ግን የህይወታችንን ዋና ክፍል በሰንጥነው መጠን ነው። ዛሬ ጌታ ስጡኝ ሲለን ያልለቀቅንለት፣ በብዙ ነገር እያለፍን ጌታን ወደዳር ያስቀመጥንበት፣ ወደላይና ወደታች የምንልበት፣ ተሸክመን የምንደክምበት ነገር ምን ይሆን? ለከበደን ነገር ሁሉ መፍትሄ ለማግኘት፣ ጌታ እየሱስ የህይወታችን ሁለንተና እንዲሆን እንፍቀድለት።
የክርስትና ህይወት የተጀመረው ካሸናፊነት ነው። ጌታ እየሱስ ክርስቶስ ሞታችንን ሞቶ፣ የዕዳችንን ጽሕፈት ደመስሶ፣ በእርሱ የኃጢአትን ስርየት አግኝተን የድል ሕይወትን ስጥቶናል። የድል ሕይወትን ስለሰጠን ደግሞ የድል ኑሮን እንድንኖር ይጠብቅብናል። የድል ኑሮን ለመኖር፣ እርሱን ድል የሰጠንን አምላካችንን በማክበር፣ ሁልጊዜ እራሳችንን በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ማየት ይኖርብናል። የተለያዩ ችግሮች በመነንገዳችን ሲገጥሙን፣ ከእግዚአብሔር ጋር በመስማማት፣ የገባልንን የተስፋ ቃል አያሰላሰልን፣ አልፈን ማየት መቻል ይኖርብናል።
በዮሐንስ ራእይ ውስጥ በተደጋጋሚ "መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ" እያለ ሲናገር የቤተክርስቲያንን ሕንፃ ሳይሆን እኛን ክርስቲያኖችን ነው የሚያመለክተው። በዚህ ትምህርት ውስጥ የዚህን መንፈስ ከብዙ ስራዎቹ ጥቂቶቹን ስንማር፣ ክዚህ ህያው ከሆነው የመንፈስ ቅዱስ ድምፅ ጋር ላለመተላለፍ፣ ከጌታና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የጠበቀ ህብረት በማድረግ ቃሉን ለማወቅ መትጋት እንዳለብን እናያለን።
ጊዝያትና ዘመናት ይለዋወጣሉ፣ ነገስታቶች ወደ ስልጣን የወጣሉ ደግሞም ከስልጣን ይወርዳሉ። ጥበብና ሀይልን የተሞላው አምላካችን እግዚእብሔር ግን ዙፋኑ የማይናወጥ የሁሉ ገዢና ጌታ ነው። እኛም የማይናወጥ መንግስት የሚጠብቀን ሰዎች መሆናችንን ተረድተን፣ አንድ ቀን በፊቱ እንደምንቆም በማመን፣ በመፅናት እርሱን አምላካችንን መጠባበቅ ይኖርብናል።
በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ በተለያየ ጊዜ፣ በተለያዩ ቦታዎች ለብዙዎች ደርሳ ያደረችውን ድንቅ ነገሮች በዚህ ትምህርት ውስጥ እናያለን። እጁ ለሚፈሩት ትታወቃለችና፣ የአግዚአብሔር እጅ ወደ እኛ እንድትመጣ፣ አግዚአብሔርን መጠየቅና አሱን በመፍራት በፅድቅና ከበደል ነፃ የሆነ ኑሮን ልንኖር የተገባ ነው። በተጨማሪም፣ እግዚአብሔር አምላካችንን ከፍ ከፍ አያደረግን፣ ከምስጋና ጋር ለእግዚአብሔር ስራ መነሳሳት አለብን።
የክብርን ወንጌል ሰዎች ሰምተው ወደ ጌታ እንዳይመጡ ከሚዋጋበት መንገድ አንዱ የሰዎችን መንፈሳዊ አይን በማሳወር ጆሮንም በማደንቆር ነው:: በአማኞችም አዕምሮ ክፉ ሀሳብን በመላክ ደግሞም አይኖቻችን በአለም ውበት እንዲሳቡ በማድረግ ይዋጋል:: ይሁን እንጂ በክርስቶስ በስሙ ስልጣንና በፀጋው ጉልበት አሸናፊዎች ነን:: ለጨለማው ገዢ እምቢ እያልን ለጌታ ግን በመገዛትና በመታዘዝ ፈቃዳችንንም ሁሉ ለእርሱ ፈቃድ በማስገዛት ልንመላለስ ያስፈልጋል
እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ እንደተፃፈ ቅዱሳን ልንሆን ተጠርተናል:: ለዚህ ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደመምሰል ህይወት እንድንመጣ እለት እለት መንፈስ ቅዱስ ያዘጋጀናል:: መንፈስ ቅዱስ ካዘጋጀው በላይ በእግዚአብሔር ፊት የበቃ ወይም ቅዱስ ሆኖ መታየት አይቻልም:: መንፈስ ቀዱስ ከፊት ሊሆን ያለውን የሚያውቅ ስለሆነ ከወዲሁ ያዘጋጀናል::ሰለዚህ የምናልፍበት ምንም አስቸጋሪ እና አስፈሪ ቢሆን እንኳ በእርሱ ችሎት እናልፈዋለን::አስቀድሞ ለችግሩ ለፈተናው አዘጋጅቶናልና:: ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ የሚለው ቃል እንዲሀ አይደለም:: ነገር ግን የሚያዘጋጀን መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቶን ነው እንጂ::
አማኝ ህይወቱ ጌታን የሚከተል ተልዕኮ ያለው በዚህ ምድር በአላማ የሚኖር ነው:: ተልዕኮውም የኢየሱስን ሞትና ትነሣኤ በቃልና በስራ በኑሮ የመስከር ሰውንም ሁሉ ወደ እግዚአብሔር መንስት ማፍለስ ነው:: ስለዚህ አማኝ ሁሉ በደቀመዝሙርነት ህይወት ሊመላለስ ደግሞም ለአማኝ ሁሉ በተሰጠው ስልጣን ስሙን ሊጠራና በእምነትም ስልጣኑን ሊጠቀምና ሊመላለስ የጌታ ፈቃድ ነው:: በዚህ መልዕክት የደቀመዝሙርን ህይወት ከስልጣንና ከእምነት ጋር በተገናኘ በስፋት እንማራለን::
ለእግዚአብሔር አደራ መስጠት እና ማመስገን ዕዝራ 8:21-23
ለእግዚአብሔር አደራ መስጠት እና ጸሎት 1ሳሙ 12:23
ጸም እና ጸሎት ዘጸ 24, ዘጸ 33:3 , ት.ኤር 52, ዘኍ14:27, 2ነገ 25
በባለፈው እያመሰገኑ መጸለይ መዝ 16:13, 78:14 ማቴ 16:5 ማር 8:14
ጸሎት እና ምስጋና መዝ 50:3፣ 65:1 ኤፌ5:20 1ኛ ተሰ 5:17-18 ፊል 4:6
ልብን ማፍሰስ ሉቃ 18፡35-43 ሮሜ 8:26-27 ኤር 33:3
አምኖ መጸለይ 11:24 ማቴ 21:22 ዕብ4:16
ወደ ትክክለኛ ምሪት የሚያደርስ ጸሎት ሉቃ 4:3-8 መዝ 90
እራስን መመርመር 1ኛ ቆሮ 11:31 2ኛ ቆሮ 13:5
እንዴት እንጸልይ ያዕ 2:14-26 ዕብ 10:38 ሮሜ 1:17 ገላ 3:11 ክፍል 18
የእምንት መሰርት ሮሜ 10:17 ዮሐ4:4-29
እንዴት እንጸልይ ክፍል 20 እምንት እና ፈተና ነህ 9:8 1ኛ ጴጥ 5:6-11
Play Episode Listen Later Sep 20, 2021 9:10
ያመጣነውን ለጌታ መተው
Play Episode Listen Later Sep 21, 2021 11:25
በጸሎት መቆየት
Play Episode Listen Later Sep 22, 2021 11:12
እግዚአብሔር ጸሎትን ይሰማል
Play Episode Listen Later Sep 24, 2021 12:09
ጸሎት ከተሰጠን ጸጋ ጋር መገናኘት ነው
በክርስቶስ ውስጥ መሰወር ቆላ 3:2-3 2ኛ ተሰ 3:3 ሮሜ 12፡12 ሮሜ 8:28
ጸሎትን መከተል አስ 4:13-17 አስ 5 ማቴ 11:28
የጸሎት ፈተናዎች ዮሐ17:11 ዮሐ 18 ማቴ 17 ማቴ 26 ሉቃ 8
Play Episode Listen Later Oct 3, 2021 15:20
በእምነት በጸለይነው ጽሎት ውስጥ መቆየት ሉቃ 1 1ኛ ሳሙ 14 ዘፍ- 26 መዝ 90:89 ዮሐ 16:30
እግዚያብሔር እይታ ውስጥ መሆንን ማየት. ዘፍ 16:13 ዘፍ 39:2-3 ዘፍ32
Play Episode Listen Later Oct 10, 2021 16:22
እራስን እና የራስን ህይወት መጠበቅ ምሳ 1:33 1ኛ ጢሞ 4:13-16 2ኛ ነገ 9 ማቴ 25:1-25
በህይወት ለማደግ እንድንችል ልናስተውላቸው የሚገቡ ነገሮች መክ 7:25 መክ 10:1
በህይወት ለማደግ እንድንችል የሚርዱን ነገሮች ዕብ 5:11-14 1ኛ ጴጥ 2:2-3
Play Episode Listen Later Oct 13, 2021 12:04
እያደግን እንደሆን በምን እናውቃለን? 1ኛ ጢሞ 6 ቆላ 3-17 1ቆሮ 10-31 1ኛቆሮ 12-13
Play Episode Listen Later Oct 14, 2021 18:06
ሰው ለመንፈሳዊ እድገት ምን ያስፈልገዋል? ዕብ 11:6-7 ዕብ11:1 ሉቃ 24 ኤፌ 1:13 ሮሜ 5:1-6 ኤፌ2:8 ሮሜ 12
በጌታ ሆኖ ለሌሎች መታወቅ ሮሜ 16፡10 ዕብ 4፡15 ፊሊ 2:19-22 ማቲ 10:25
Play Episode Listen Later Oct 16, 2021 12:26
ለእድገት የሚያስፈልጉን ነገሮችና ለማደግ የሚጠቅመን ነገሮች ምንድን ናቸው? 2ኛ ጢሞ 4 2ኛ ጢሞ 2:1-2 ቆላ 1:28 ሮሜ 1
Play Episode Listen Later Oct 17, 2021 14:23
ለማደግ በስፍራ መገኝት 1ኛ ጵጥ 3 1ኛጢሞ 5:22 1ኛጢሞ 6:20 2ኛጢሞ 1:14 1ጢሞ 6:30 ገላ 6:1
Play Episode Listen Later Oct 18, 2021 12:11
የማደግ ምልክቶች ውስጥ አንዱ ለእግዚያብሔር እራስን እየሰጠን መምጣት ሲሆን ሌላው ደግሞ የራሳችንን ሸክም ለመሸከም የበቃን ሆኖ መግኝት እና የመንፍስ ፍሬን ማፍራት ናቸው 1ሳሙ 1:24-28
Play Episode Listen Later Oct 19, 2021 28:40
ለማደግ የእግዚያብሔርን ነገር ማስተዋልና የእግዚያብሔርን ውለታ መስብስብ ወይም መያዝ ያስፈልጋል መዝ 103 ኢያ 1 መዝ 50:23
Play Episode Listen Later Oct 20, 2021 11:07
ያደገ እውነት የበራለት ስው ለይቅርታ የማይቸገር እና በመንፍሳዊ ህይወቱ የሚተጋ ይሆናል ሉቃ 19:1-10
Play Episode Listen Later Oct 21, 2021 14:26
እራሳችንን በጌታ ብርሃን ማወቃችን እና ይህ ብርሃን እየጨመር ሲመጣ እየለወጠን እየጠራን እያስጠጋን ሲመጣ ማደጋችን ይታውቃል ኢሳ 6:1 ዮሃ 13:37 1ኛ ቆሮ 15 ቲቶ 3:4-6
Play Episode Listen Later Oct 22, 2021 12:45
እንዳደግን አንዱ ትልቁ ምልክቱ መጽናኛችን መንፈስ ቅዱስ ሲሆን ነው ዘፍ 16 ሮሜ 14:17 ሐዋ 9:31 2ኛ ቆሮ 12
መንፈስ ቅዱስ ህያውና የሚሰራ፣ ወደ እውነት ሁሉ የሚመራንና እረፍትን የሚሰጠን መንፈስ ነው። ይሕ መንፈስ በአማኝ ሕይወት በጣም ብዙ ስራዎችን ይሰራል፣ የእግዚአብሔርም ክብር በመካከላችን እንዲታይ ያደርጋል ሆኖም ግን ይህ ህያው የሆነው መንፈስ በሙላት በህይወታችን አንዳይሰራ የሚያደርጉ ነገሮች አሉ። አስራ አራት የሚሆኑ የመንፈስ ቅዱስ ስራ እንቅፋቶችን በዚህ ትምህርት ውስጥ ተጠቅሰው እናያለን።
በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ዳግመኛ በተወለድን ጊዜ የእርሱን መንፈስ ተካፍለናልና መንፈሳውያን ተብለናል:: መንፈሳዊ ስንባል መነፈስ ሆነናል ማለት ሳይሆን ነገር ግን ከተካፈልነው የክርስቶስ ቅዱሱ መንፈስ የተነሳ በእኛ ላይ ሰልጥኖ የነበረውን የሥጋን ሥራ በመግደል ለእግዚአብሔር ፈቃድና ሀሳብ ሁለንተናችንን በማስገዛት መመላለስ ነው:: * መንፈሳዊነታችን በልባችን ውስጥ ከሚመላለሰው ሀሳብ ጀምሮ በውጭ እስከሚሰማና እስከሚታይ እንቅስቃሴያችን ድረስ እለት እለት በኑሮአችን የሚገለጥ ነው::
በምድር ሥህተት የሌለበት የከበረ ሕይወት፣ ሰው እግዚአብሔርን አስቀድሞ የሚኖረው ሕይወት ነው። የነገር ሁሉ መነሻና መድረሻ የሆነውን ትልቁን እግዚአብሔርን መውደዳችንን የምንገልጥበት መንገድ እርሱን በማስቀደም ሲሆን፣ ማስቀደማችንን ደግሞ የምናሳየው፣ የራሳችንን ፈቃድ በመተው፣ ከሐጢያት በመራቅ፣ ያለ ሁከት፣ በሰላምና በእርጋታ፣ ነገራችንን ሁሉ በርሱ ላይ ጥለን በእረፍት በመኖር ነው።
በመከራና በስደት ወይም በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ማለፍ ደስ የሚያሰኙ ሁኔታዎች አየደሉም ሆኖም ግን እንዚህ ሁኔታዎች የእግዚአብሔርን አብሮነት ማሳያ መንገዶች ናቸው። እግዚአብሔር አብሮን ሲሆን፣ በጊዜው ከመጣብን የሕይወት ነውጥ ይታደገናል፣ የሚታየውን ብቻ ሳይሆን የውስጣችንን ነውጥ ሁሉ ወደ መረጋጋት ይለውጠዋል። እግዚአብሔር አብሮን ሲሆን፣ ሰልፍ የለም ማለት አይደለም፣ ነገር ግን በሰልፍ ውስጥ ድል አለ።
ጌታን መከተል ማለት ለእግዚአብሔር ፈቃድ መኖር ለሀሳቡም መገዛትና በመንገዱ መሔድ ማለት ነው:: በእርሱ ፈቃድና ሀሳቡ ለመኖር የሚያስፈልገው የሰው እውቀትና ችሎታ ሳይሆን የሰማያዊው ጥሪ ተካፋይ መሆን ደግሞም በፀጋው መቆም ነው:: እግዚአብሔርን መከተል የእኛን ፈቃድ ይጠይቃል:: ደግሞም ዋጋ ለመክፈል የተዘጋጀን ልንሆን ያሰፈልጋል:: በመረጥንበትና በወሰንበትም ልክ የሚያበቃንን ፀጋ እንቀበላለን:: Activity
የዛሬ ጥያቄዎች 1. መንፈሳዊ ህይወታችንን ጠብቀን አጉል ቦታ ላሉት ወንጌልን እንዴት ነው ማድረስ የምንችለው? 2. የማይሆን ነገር መስማት ሀጢያት ነው የሚለው ይብራራልን። 3. በታማኝነት ያደረግነው ነገር የተረሳ የሚመስለን ግዜ አለ የሚለው ይብራራልን። 4. በእግዚአብሔር ፊት ባዶ ለመሆን ማደረግ ያለብን ነገር ምንድን ነው? 5. የጴጥሮስ ዋና ጠላቱ አውቃለው ማለቱ ነው የሚለው ይብራራልን? 6. ጌታን እናገለግላለን የምንል ሰዎች እንዴት ነው ወደ ባዶነት መምጣት የምንችለው?
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ከጌታ የሆነውንና ከሌላ የሆነውን መከራ እንዴት ነው የምንለየው? 2. እኛ የጌታ ባርያ ነን የሚለው ይብራራልን። 3. “በዋጋ ተገስታችኋልና የሰው ባርያ አትሁኑ” የሚለው ምን ማለት ነው? 4. ከአንድ ደረጃ ወደ ሌላ ከፍታ የሚያወጣንን መከራ እንዴት ነው መለየት የምንችለው? 5. ጌታ ከተናገረን ተቃራኒ ነገር ሲገጥመን ምን ማድረግ ነው ያለብን? 6. የዳነ ሰው ችግር ሲገጥመው እርግማን ነው ይባላል እና የዳነ ሰው እርግማን ያጋጥመዋል ወይ?
Play Episode Listen Later Jul 5, 2021 44:27
በበደላችን ሙታን ሆነን ሳለን፣ እግዚአብሔር በክርስቶስ እየሱስ ሕይወትን ሰጠን፣ በጸጋም አዳነን፣ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ሆኖም ግን ይህንን ደህንነታችንን የማይወድ ሰይጣን፣ ሊያዘናጋን ሁልጊዜ ይተጋልና፣ ሃሳቡን ላለመሳት፣ ክፉ ስራዎቹን ልናውቅ ይገባናል። በዚህ ትምሕርት ውስጥ በሰፊው የነዚህን ክፉ መናፍስቶች ስራ ተዘርዝረው እናያለን።
ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብና ከእግዚአብሔር ጋር ስንሆን ሁልጊዜ አሜንና ሐሌሉያ የምንልበትን መልስ ብቻ ላንቀበል እንችላለን። ሊሆን የሚገባው ባይሆን፣ በጥያቄያችን ላይ ጥያቄ ቢደራረብብን፣ ጌታ ከባሕሪው ተካፋዮች ሊያደርገንና ዕይታችንን ከእግዚአብሔር ዕይታ ጋር ሊያስማማ ነውና፣ እኛ ግን እግዚአብሔር በተቀደሰ መቅደሱ እንዳለና እውነተኛ ፈራጅ መሆኑን ተረድተን፣ እግዚአብሔር በኛ የጀመረውን ስራ እንዲጨርስ፣ በፊቱ ዝም ብለን እርሱን ብቻ ከምስጋና ጋር መጠበቅ ይኖርብናል።
በየዘመናቱ እግዚአብሔር ሀያላን የሚላቸውን ሰዎች በህዝቡ መካከል ያስነሳል:: የእርሱን ፈቃድ የሚፈፅሙ ሀሳቡም የሚከናወንባቸው:: ስለዚህ ሀያላን በመካከላችን እንዲበዙ ደግሞም ሀይላቸው እንዳይደክም የእግዚአብሔርንም ፈቃድ ከመፈፀም እንዳይዝሉ ልንፀልይ ያስፈልጋል:: በዚህም መልዕክት ሰለሀያላን መነሳት በፀሎት እንተጋ ዘንድ ሰለምን እንደሚዝሉ ደግሞም ስለምን እንደሚወደቁ በስፋት እንማራለን::
የእግዚአብሔር ቃል ሰው ከታናሽነቱ ጀምሮ ሀጢአተኛና ከእግዚአብሔር ክብር የጎደለ ደግሞም ከሀጢአት የተነሳ በእግዚአብሔር ፊት ሊቆም የማይችል እንደሆነ ይናገራል:: ይሁን እንጂ ግዚአብሔር ሰውን ከመውደዱ የተነሳ በራሱ ምረጫ እንደገና በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ወደ ክብር ሊያመጣው ወደደ:: በዚህ መልዕክት ድንቅ የሆነውን የእግዚአብሔርን ምህረት ደግሞም የእኛን የአማኞችን ማንነት በምድር ላይ ባለ አጭር ዘመናችንም ሊኖረን የሚገባውን ኑሮና እንዲሁም ደግሞ የህይወት መዳረሻችንንም በስፋት እንማራለን::
መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ በወረደ ጊዜና የመጀመሪያውን የወንጌል ምስክርነት አሰምተው ሰዎች በኢየሱስ ባመኑ ጊዜ የቤተክርስቲያን ውበት መገለጥ ጀመረ:: በአመታት መካከል በቁጥር እየበዛችና እያደገች ደግሞም እየተገለጠች መጣች:: መከራ እየጨመረ በመጣ መጠንም በቤተክርስቲያን አብዝቶ ድንቅና ተአምራት ይሆን ነበር:: ፀጋም ይገለጥ ነበር:: በጉዞ ውስጥ ድካም ሲኖር ዝለት ሲመጣ ጌታ ደግሞ ተሃድሶን ያደርጋል:: ጉብኝት ይሆናል:: ሀይል ይታደሳል:: እንደ ቀድሞ የእግዚአብሔር ሀይል ይገለጣል:: በዚህን ጊዜ ግን እግዚአብሔር አስቀድሞ ከእርሱ ጋር ያለው የሰው ግንኙነት እንዲታደስ ይፈልጋል::
ትልቁ አምላካችንና ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር ሲመላለስ የሁሉ ነገር ምንጩ አባቱ ነው። ሁሉን የተቀበለውና ለሁሉ ነገር መልስ የሰጠን ወደላይ እያየ ነው። እኛም ዛሬ ከአመጻ የተነሳ ፍቅር በቀዘቀዘበት፣ ርህራሄና መተማመን በጠፋበት በዚህ አለም ስንኖር፣ አይናችንን ልናነሳ የሚገባን ወደላይ ወደ ጌታ ነው። አንዱ የታማኝነት መገለጫ አይናችንን በርሱ ላይ ማድረግ ሲሆን፣ አይናችንን ከርሱ ላይ ማንሳት ደግሞ ዋጋ ያስከፍላል።
ያለ መንፈስ ቅዱስ ህይወትም ሆነ አገልግሎት ድካም ነው። በመንፈስ ቅዱስ የተነገረለትና፣ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ የተወለደው ትልቁ አምላካችንና ጌታችን ወንጌልን መስበክ የጀመረው፣ በሽተኞችን ይፈውስና አጋንንትን ያስወጣ የነበረው በእግዚአብሔር መንፈስ ነው: በሚያደርገው ነገር ሁሉ ይህ መንፈስ አብሮት ነበር ። ትልቁ ጌታችን በመንፈስ ይህን ካደረገ፣ ለኛ ለደካሞቹ ምን ያህል ይህ መንፈስ ቅዱስ እንደሚያስፈልገን ማሰብ አያዳግተንም። ይህ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ የሚሠጠው ፈቃደኛ ለሆኑና ለሚፈልጉት ስለሆነ፣ ዕለት ዕለት ከምንም ነገር በላይ አጥብቀን ልንፈልገውና ልንሞላው የተገባ ነው።
ተለክቶ በተሰጠን በዚህ ዘመናችን በእኛ ህይወት እግዚአብሔር ሊያደርግ ካቀደው ከወሰነው ማንኛውም ነገር ከማድረግ ከመፈፀም የሚያግደው አንዳችም ነገር የለም:: የሚያገኘን ክፋት ደግሞም የምናልፍበት ሁኔታ በእኛ ላይ ያለውን የጌታን ጥበቃ ሊያልፍ ማዴኑንም ሊከለክል አይችልም:: ለትምህርታችን ተፅፏልና በቀደሙት የእምነት አባቶች ህይወት የተገለጠውን የጌታን ማዳን ጥበቃውንም በዚህ መልዕክት በስፋት እንማራለን:: ዛሬም ጌታ የሚታደግ የሚያስመልጥ እንደሆነ እናይበታለን::
የነቃ መንፈሳዊ ነገራችን ያያል፣ ያስባል፣ ይለያል። ንቁዎችን እግዚአብሔር አያልፋቸውም፣ እንቁዎቻቸውን ይጠብቃሉ ከአጉል መንገድም ይጠበቃሉ። በኛ ላይ ያለውን ፀጋ የመጠበቅ ሃይላችን የነቃነውን ያህል ነው። ሰይጣን በርኩሰት፣ የብርሃን መልአክ መስሎ በመገለጥ እንዲሁም በጥበብ ተመስሎ ሁልጊዜ የሚያደባው ባልነቃንበት የህይወት ክፍል ነው። ወደ ህይወታችን ገብተው ዛሬ መውጫ ያጡ ነገሮቻችን ሁሉ፣ ባልነቃንበት ቀን የገባንበት ወይም የገባብን ነገር ነው። ስለዚህ፣ ክዚህ በኋላ ሁልጊዜ በነቃ መንፈስና በትጋት እንድንኖር መንፈስ ቅዱስ ይርዳን።
በዚህ በክፉው በተያዘ ደግሞም ወደ ጥፋቱ እየፈጠነ ባለው አለም ያለን የእግዚአብሔር ልጆች በሁሉ ነገር ንቁ ልንሆን ያስፈልጋል:: ንቁ ያልሆነ ከሚታየው አልፎ ከመንፈስ ቅዱስ የሆነውን ዘልቆ የማያይ እርሱ ለዘመኑ ባዳ ነው:: ይህ መልዕክት በህይወታችን ንቁ እንድንሆን ደግሞም በፊታችን ከቆመው ከሚያስፈራራንና ከሚያስጨንቀን ችግራችን ይልቅ የምናመልከው አምላክ እርሱ ትልቅ እንደሆነ እናይ ዘንድ ያነቃቃናል::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. የእግዚአብሔር ሀሳብ አውቀን መውጣት ማለት ከራሳችን ያለፈ ለሌሎች በረከት ያደርገናል ማለት ነው ወይ? 2. በህይወታችን እድገት የማናየውና ወደ ደስታ የማንመጣ ከሆነ ችግሩ አለመለወጣችን ነው ወይስ አለመዳናችን ነው? 3. ለእግዚአብሔር ቀንተን ሰውን ልናስዝን እንችላለን ወይ? 4. አልኮል መጠጥ መጠጣት ተፈቅዳል ወይ? ከተፈቀደስ መጠን አለ ወይ? 5. መጠጥ የሚለው አልኮል ያለው ሳይሆን ሌሎች የሚያሰክሩ ነገሮች አሉ የሚለውን ብታብራራልን። 6. ዳዊት “አንተን ብች በደልኩ” ሊል የቻለው በምን መረዳት ውስጥ ሆኖ ነው? 7. ሀጢያትን እግዚአብሔር እንደምንበድል ሲገባን ለሀጢአት የሚኖረን ክብደት ይጨምራል ማለት ነው?
ዳዊት እግዚአብሔርን የለመነውና ሁልጊዜ የሚሻው አንድ ነገር ነበር ይኸውም፤ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት መኖርና እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ነገር ማየት ነበር፣ ይህ ደግሞ ዳግመኛ ከማይጠፋ ዘር የተወለድን ሁላችን ልንመኘው የሚገባ ነገር ነው። ብዙ የጌታን ፍቅርና ምህረት ከመለማመዳችን የተነሳ፣ የእግዚአብሔርን ክብር እንዳንዳፈር፣ ነቅተን፣ ለእግዚአብሔር የሚሰጠውን ክብር ባለማጛደል ለመኖር ስንወስን፣ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ይረዳናል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በህይወታችን ላይ ያለውን መንትያ ሀሳብ ለመጣል ስንሞክር ወድቀን እንቀራለን የሚለውን ግልፅ ብታደርግልን? 2. ፍሬ እንድናፈራ የሚያደርገንና ፍሬ እንዳናፈራ የሚያደርገን ወንጌል አለ የሚለውን ግልፅ ብታደርግልን። 3. በወጀብ ውስጥ ስናልፍ ጌታ አጠገባችን እያለ የለሌለ ይመስለናል የሚለውን ቢብራራልን። 4. ሰዎችን ማፅናናት የምንችለው ጌታ ሲናገረን ብቻ ነው ወይስ እኛም ማፅናናት እንችላለን ወይ? 5. ጌታ ጳውሎስን “አብረሁ ያሉትን ሰጥቼአለሁ” ያለው በሥጋ ነው ወይስ መንፈሳቸውንም ጭምር ነው? 6. የአህምሮ እና የልብ ጠቢብነት የሚለው ቢብራራልንና የልብ ጠቢብነት ቀድሞ የአህምሮ ጠቢብነት ሊከተል ይችላል ወይ?
እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ የስው ልጆችን ለልባቸው ፈቃድ ይሰጣል። ሰው ደግሞ ለልቡ ፈቃድ ሲሰጥ፣ ክንዱን አምላክ ያደርጋል፣ ስለሚፈልገው ነገር የሚያደርገው ሁሉ ትክክል ይመስለዋል፣ የመጨረሻ ጥበቡንና ብርታቱን ይገልጣል ነገር ግን ሰው የእግዚአብሔርን ፅድቅና ዕውነት ማዛባት ሲጀምር፣ ፃድቁና ፍርድ አደላዳዩ አምላክ እግዚአብሔር ይነሳል፣ ጣልቃ ይገባል። እግዚአብሔር ሲነሳ ደግሞ የሰው ኩራትና ትእቢት ሁሉ ከንቱ ይሆናል፣ ትልቅ ነኝ ያለው ትንሽ ይሆናል።
እግዚአብሔር ሂዱ ባለን መንገድ ላይ ከሆንን፣ በተለያየ እቅጣጫ ብዙ የሚያናውጥ ሁኔታ በዙሪያችን ቢከስት እንኳን፣ ፍጥረት ሁሉ የሚታዘዝለት ይሄ ታላቅ ጌታ ብቻችንን እይተወንም። ሂዱ ያለን አምላክ እንደማይተወን በማመን፣ በስልጣኑ ሁሉን ማድረግ የሚችለው አምላካችን፣ የሚናገረንን ቃል ብቻ እየሰማን፣ በዙሪያችን ያለውን ወጀብ ሳይሆን፣ አይኖቻችንን ብርቱ በሆነው አምላክ ላይ ልናደርግ ይገባናል።
የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ስንፈልግ የሚይስፈልገን ነገር ሁሉ ይጨመርልናል። እግዚአብሔር ልጆቹን የሚባርክበት የተለያዩ ቁልፎች አሉ፣ ከብዙ የበረከት ቁልፎች አንዱ፣ የእግዚአብሔር የአምላካችንን ስራ በመተባበር እርሱ በሚፈልገው ሁኔታ መስራት ሲሆን፣ ለዚህ ስራ ስንነሳሳ፣ ልባችንን ከመንገዳችን እንድናነሳና የእግዚአብሔርን ስራ ለማደናቀፍ፣ ሰይጣን መካሪ ይገዛብናል፣ በሌለንበት ነገር ክስ ያዘጋጅብናል፣ ሌሎችም ብዙ የተለያዩ ፈተናዎችን በመንገዳችን ያቆማል። በዚህ ሁሉ ግን እኛ ለእግዚአብሔር ስራ ጨክነን ስንቆም፣ እግዚአብሔር፣ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ የሚል ድምጹን ያሰማናል።
መታዘዝ ማለት ራስን በጌታ ፈቃድ ውስጥ በገባን በተረዳንና በተገለጠልን ማግኘት ማለት ነው:: ለአማኝ በህይወት ለመኖር ለመጠበቅና ለማደግ አስተማማኝ ስፍራ እርሱ ለመታዘዝ ህይወቱን የሰጠበት ስፍራ ነው:: መታዘዝ እነደ ደረስንበት መረዳት መጠን ዋጋ ያስከፍላል:: ይሁን እንጂ የመታዘዛችን ፍሬው የህይወት መብዛት ነው:: ከእኛ አልፈን ለሌሎችም በረከት ሰላምና መፅናናት እንሆናለን:: በአሸናፊነትም ህይወት ይቀጥላል::
የቤተክርስቲያን መልክ በውስጥና በውጭ የሚገለጥ ነው:: በውስጥ በሰላም የተሞላች ነበረች:: በውጭ ደግሞ መፈራትና ሞገስ ነበራት:: የቤተክርስቲያን ሰላም ከጌታ የተቀወለችው በውጭ ባለው ሁኔታ የማይወሰን በበመከራና በፈተና ውስጥ እንኳ የማይደፈርስ የፀና ሰላም ነው:: ጌተ የሰጠን ሰላም አለም እንደሚሰጥ ሳይሆን በሁኔታዎች የማይደፈርስ የውስጥ ሰላም ነው:: እያንዳዳችን በዚህ ሰላም ከተሞላን ደግሞም ከጠበቅነው ቤተክርስቲያንም በዚሁ ሰላም የተሞላች ትሆናለች:: ስለዚህ በቤታችን በስራ ቦታ በስፍራው ሁሉ ራስን በመግዛት ጌታንም በመታመን የሰላም ሰው ሆነን ልንመላለስ ያስፈልጋል::
መንፈስ ቅዱስ ስለ ኃጢአት፣ ስለ ጽድቅና ስለ ፍርድም የሚነግረን አውነተኛ የሕይወት መሪ ነው። ይህ ከክርስቶስ ጋር አብሮ ይስራ የነበረው መንፈስ፣ የእየሱስ የሆነውን ሁሉ የሚነግረንና፣ ይህንን ታላቅ ጌታ በሕይወታችን እንድናከብር የሚረዳን መንፈስ ነው። ካለዚህ መንፈስ ቅዱስ እርዳታ ወደ እውነት መድረስ ስለማንችል አጥብቀን ይህንንን መንፈስ መፈለግና ለመቀበል ደግሞ ልባችንን ማዘጋጀት ይኖርብናል።
የክርስቶስ ወገን የሆንበት አንዱ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ስላለብን ነው። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ስላለ፣ መንፈሳዊ ሰዎች ለመባል አያበቃንም ነገር ግን መንፈሳዊ ሰዎች የሚያሰኘን፣ ለዚህ መንፈስ ቅዱስ ዕውቅናን በመስጠት፣ ስናከብረውና ሀሳባችንንም ፈቃዳችንንም እንዲገዛ ስንፈቅድለት፣ በሕይወታችን ደግሞ ተገልጦ ፍሬው ሲታይ ነው።
የአማኝ አንዱ የደህንነት ትሩፋት ቅዱሱን ጌታ እግዚአብሔርን ማገልገል ነው:: ነገር ግን የምናገለግለውን ጌታ እንደሚገባ ልናውቀው የተገባ መሆኑ ዋና ነገር:: የነገሮቻችን ሁሉ መፍቻ ቁልፍ እርሱን ማወቅ ነውና:: እግዚአብሔር ራሱን የሰወረ አምላክ አይደለም:: ነገር ግን እኛ እርሱን ለማወቅ ያለን ፈቃድ ደግሞም አካሄዳችን ወሳኝ ነገር ነው:: በዚህ መልዕክት እንደ ቃሉ እግዚአብሔርን እንደሚገባ የምናውቅባቸውን መንገዶች በስፋት እንማራለን::
Play Episode Listen Later Jul 16, 2021 47:41
በራሳችን እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ብዙ ነገሮችን ለማድረግ እየጣርን፣ እየወጣንና እየወረድን ብዙ እየደከምን፣ ይሄ ሁሉ ድካማችን ግን ከእርሱ ደስታ ጋር አላገናኘን ይሆን። ኢዮሣፍጥ የተባለ የይሁዳ ንጉሥ አንድ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነገር እንደተገኘበት መፅሐፍ ቅዱሳችን የነግረናል። ይህም ነገር እግዚአብሔርን ለመፈለግ ልቡን ማዘግጀቱ ነው። እግዚአብሔርን የሚያስደስተው፣ የኛ ልጅ መሆን ነው። እኛም ልጅ መሆናችን ከገባን፣ ልጅነታችንን፣ ከአባታችን ጋር ህብረት በማድረግ፣ እርሱን በመውደድና በመታዘዝ፣ በልጅነት ስፍራችን ልንገኝ ይገባናል።
አንዳንድ ጊዜ ተስፋ አድርገን በድፍረት የተናገርንበት፣ ነገራችንን ሁሉ የጣልንለትና የምናልፍበት ሁኔታ በጣም የተራራቀና ልብን ዝቅ የሚያደርግ፣ መነጋገሪያም አድርጎን ሊሆን ይችላል። ነገር ግን፣ እግዚአብሔር ተስፋ የሚይደርጉትን፣ ልባቸውንና አይናቸውን እርሱ ላይ ያደረጉትን አሳፍሮ አያውቅም። በምናልፍበት ሁሉ፣ እርሱን በመተማመን አንጠብቀው። በታገስንበትና እርሱን በጠበቅንበት መጥቶ ሀይላችንን ያድሳል፣ ቀና ያደርገናል፣ ለቅሶአችንን ወደ ደስታ ይለውጣል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሊሰራን ወደ እኛ የሚመጣውን የእግዚአብሔርን ቃል እንዴት ነው በምን መንገድ እንደሚሰራን የምናውቀው? 2. ሰማያዊ ጥበብ ለቤታችን የሚጠቅመን ምንድን ነው? 3. ለጌታ ፍቅራችንን የምንገልጥበት ቃል ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 4. የተገለጠልን፣ የተሰጠን እና የሆነልን ነገሮች ምንድን ናቸው? 5. በእኛ ስለሚበዛው ህይወት ብታብራራልን። 6. ዐይናችን ወደ ጌታ እንዳናነሳ ችግራችን ምንድን ነው?
እግዚአብሔር በሰው አይምሮ የማይቻል፣ በስርአትና በሕግ የማይንካ ነገርን አልፎ ይነካል ። በመፅሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ብዙ ምሳሌ የሚሆኑን በእግዚአብሔር የተነኩና ከቀድሞ ማንንነታቸው የተለወጡ ሰዎች ተጠቅሰውልናል። ሰው ከመለኮት ጋር ከተነካካ የቀድሞውን ማንነቱን መሆን አይችለም። ምህረትን፣ ፍቅርንና ፅድቅን የተለማመደ፣ በብርሀን የሚመላለስና፣ የአሸናፊነት ህይወት ያለው ይሆናል። ዛሬ የእግዚአብሔርን ቃል እየሰማን፣ እያመለክንና እያገለገልን፣ የደከምንበት ወይም ያልተነካንበት ነገር ካለ፣ ይህንን ታላቅ ጌታ እንጠይቀው፦ በመራራት፣ እጁን በድን ወደሆነው ነገራችን ላይ ይዘረጋል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ለጽድቅ ሊሞቱ የተጠሩ ሰዎች አሉ የሚለውን ብታብራራልን። 2. ችግር ሲገጥመን ዝም ብለን ጌታን እያየን መጠበቅ አለብን የሚለው ይብራራልን። 3. ወደ ቅድስና ህይወት ለመምጣት መንገዱ ምንድን ነው? 4. በሰውነታችን ለሀጢአት ህግ መገዛት እና በአህምሮአችን ለእግዚአብሔር ህግ መገዛት ምን ማለት ነው? 5. ለሀጢአት የሞታችሁ ለጽድቅ ህያዋን ናችሁ የሚለው ይብራራልን። 6. ለሰራነው ሀጢአት የህሊና እና የብርሃን ወቀሳ ልዩነት ምንድን ነው? 7. የምንወቀሰውን በክርስቶስ ካላየነው ሀጢአት ይሆንብናል የሚለውን ብታብራራልን።
እግዚአብሔር በልጁ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ወደ መንግሥቱ ሲያስገባን ሁለንተናችንን ለራሱ ሊያደርግ ነው:: ለእርሱ ልንሆን ነው:: የአማኝ ደስታና እረፍት ለጌታ መሆኑ ነው:: ነገር ግን ለእርሱ ባልሆንበት በግል ደረጃም ሆነ እንደ ቤተክርስቲያን ከክብሩና ከሰላሙ የጎደልን እንሆናለን:: ስለዚህ በጊዜውም አለጊዜውም በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ ለጌታ ልንሆን ፈቃዱም በእኛ ሊፈፀም ቤተክርስቲያንም የበረከት የሰላምና የመፅናኛ ስፍራ ልትሆን ይገባታል::
በዚህ ትምህርት ውስጥ፣ ከሰይጣን መጠበቅ የምንችልባቸውን አስፈላጊ ዝርዝሮችን ስንማር፣ ከዝርዝሮቹ አንዱ እግዚአብሔርን መፍራት ነው። እግዚአብሔርን በመፍራት ስንኖር፣ የእግዚአብሔር መላእክቶች በዙሪያችን ይሆናሉ የሚያስፈራንና የሚያስደነግጠን ከእርሱ በቀር ምንም አይኖርም ክፉ ነገርም አያገኘንም። በተጨማሪም፣ እግዚአብሔርን ስንፈራ ከሐጢያት ለመራቅ ጉልበት እናገኛለን የአሸናፊነትንም ሕይወት እንለማመዳለን።
መጠበቅ ቀላል ነገር አይደለም፣ ሕይወትን ወደ ብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ የሚከት፣ ብዙዎች አባቶቻችን ተፈትነው የወደቁበትና ጥቂቶች ያለፉበት ደግሞ በረከታቸውን የተቀበሉበት ነገር ነው። በዚህ ትምህርት ውስጥ፣ በተለየ አገላለፅ፣ የእግዚአብሔርን ታላቅ ፈዋሽነት፣ ፈውስን የተቀበለው የሠላሳ ስምንት አመት ታማሚ በመጠበቅ ውስጥ ያለፈባቸው ሁኔታዎችንና አንዲሁም በአካባቢው ያሉትን ሰዎች ባህሪ እናያለን።
ሰው ለሚያውቀው ምህረትን ሊያደርግ ይችላል ያም ቢሆን እንኳን ምህረቱ ውስን ነው። የእግዚአብሔር የአምላካችን ምህረት ግን ለዘለአለም ነው። ደግሞም ምህረቱ በሁኔታዎች ወይም በስሜት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን፣ ቸርነትና ምህረት ባህሪው ነው። በእግዚአብሔር ቤት ለመኖራችን ዋስትና ምህረቱ ነው፣ በዚህ ብዙ ውጣ ውረድና መከራ በበዛበት አለም፣ ወደ ፊት ለመራመድ አቅም የሚሆነን የእርሱን ፍቅር፣ ምህረቱንና በጎነቱን ሁልጊዜ ስናስብ ነው።
በመለኮት እቅድ የተጠራ ስው፣ ገና በማህጸን ሳለ፣ በጌታ የታወቀና የተጠበቀ ነው። በእምነት እራሳችንን በእርሱ ጥበቃ ውስጥ ማስቀመጥን እንድንለምድ እግዚአብሔር ይፈልጋል። ጌታ ትልቁ የሚፈልገው፣ የታመነ መሆኑን እንድናውቅና በቃሉ የሚገኝ ታላቅ አምላክ መሆኑን እንድንረዳ ነው። እግዚአብሔር እራሱን ለኛ የገለጸው፣ በታማኝነቱ ነው፣ ይህንን ስንረዳ፣ በእርሱ ላይ ተደግፈንና አርፈን መኖር እንችላለን።
የቀደመችው ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ቃል እውነት የምትመላለስ በፀና መሠረት ላይ የታነፀች ነች:: ይህ ደግሞ ከቃሉ የተነሳ በጌታ ላይ የፀና ህይወት መኖርን ያመለክታል:: በእግዚአብሔር ቃል ሥር የሰደደና የፀና ህይወት ከየአቅጣጫው በሚነፍሰው የአመፅና የክፋት ንፋስ አይናወጥም:: ስለዚህም ነው ወንጌል በብዙ ፈተናና መከራ አልፎ ወደእኛ የደረሰው:: በዚህ መልዕክት ቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል እለት እለት በህይወታችን ደግሞም በቤተክርስቲያን ያለውን ስፍራና ፋይዳ እንዲሁም ከእኛ የሚጠበቀው ምን እንደሆነ እንማርበታለን::
የመንፈስ ቅዱስ መውረድ ተስፋ፣ በክርስቶስ ደም ታጥበን የእግዚአብሔር ልጆች ለሆንን ሁሉ የተሰጠ ተስፋ ነው። መንፈስ ቅዱስ ወደ እውነት ሁሉ ይመራናል፣ አዲስ ስውና ትሁት ያደርገናል፣ ሀይላችንና ሰላማችን፣ አፅናኛችን፣ አስተማሪያችን፣ የእግዚአብሔርን ቃል የሚያሳስበን ነው። በዚህ ነውጥ በበዛበት አለም ውስጥ፣ ከመቼውም በበለጠ ይህ መንፈስ በሚይስፈልገን ጊዜ፣ ከዚህ ተስፋ ውጪ ብንሆን እጅግ በጣም እንጎዳለን።
በዘመናችን እጅግ ብዙ የዕውቀት መገብያ ድርጅቶች ተከፍተዋል ነገር ግን እነዚህ ሁሉ የዕውቀት ስፍራዎች እግዚአብሔርን ወደማወቅ አያደርሱንም። ለኛ ግን በክርስቶስ እውነተኛ የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቦና ተስጥቶናል። እርሱም እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው። እግዚአብሔርን ከማወቅ አንዱ ይህን አለም ለኛ እንዳልተገባ አድርጎ መቁጠር ነው።
እግዚአብሔር እንደፈቀደ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ በማመን ልጆቹ የሆንን ሁላችን በእኛ ካደረው ከመንፈስ ቅዱስ የተነሳ መንፈሳውያን እንባላለን:: መንፈሳዊነታችንም እንደ ጌታ ፈቃድና ሀሳብ በመመላለስ በተግባር ይገለጣል:: ክርስቶስንም እንመስል ዘንድ እለት እለት በቃሉና በመንፈሱ እንሰራለን:: እኛም ለመሰራት እራሳችንን እናቀርባለን በምድር ላይ በተሰጠን አጭር የእድሜ ዘመን በቅድስና በፅድቅ አና በእውነት ልንመላለስ በጨለማውም አለም የወንጌልን ብርሃን በቃልና በህይወት ልናበራ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው::
እግዚአብሔር የሰውን ዋና ነገር ይፈልጋል:: ልባችንን:: የሰው ሁለንተና በልቡ ካለው ሀሳብና ፈቃድ ጋር የተያያዘ ነው:: ስለዚህ በፊቱመልካም እንዲሆንልን እንታዘዘውና እንገዛለት ዘንድ ጌታ ልባችንን እንድንከፍት ፈቃዱንም ከቃሉ ምክር እንድንቀበል ይጠይቀናል:: ሰምቶ ለሚከፍት ከጥፋት መዳን ይሆንለታል:: የተራቆትንበት ጉድለታችንም ይሞላል:: በረከትም ወደ ህይወታችነ ይመጣል:: * ለወዳጃችን ለጌታ ኢየሱስ ልባችንን ላለመክፈት ምክንያት አይኑረን::
ማርያም መልአኩ የነገራት መልእክት ምንም እንኳን ለሰው አይምሮ ከባድ ቢሆን፣ እርሷ ግን የእግዚአብሔርን ነገር በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር። መንፈሳዊ ህይወታችን ትክክል አለመሆኑ አንዱ መገለጫው መጠበቅ ሲያቅተን ነው። የምንጠብቀው የእግዚአብሔር እውነት ግን በውስጣችን ካለ፣ ለጠበቅነው ነገር ለመለየትና ዋጋ ለመክፈል አቅም ይሆነናል፣ የሰይጣን ፈተናም ሲመጣብን፣ የጠበቅነው እውነት ራሱ ጋሻ ይሆንልናል። ይህ በውስጣችን ያለው እውነት ደግሞ ተዳፍኖ መቅረት ሳይሆን በጸጋው በእኛ ውስጥ አልፎ ለትውልድ እንዲደርስ ያስፈልጋል።
ከአብርሃም እስከ ዳዊት አስራ አራት ትውልድ አለ፣ ከዚያም እስከ እየሱስ ድርስ ሄዷል፣ አሁንም ሰዎችን ሁሉ በክርስቶስ የማዳን ስራ፣ የመንግስቱ ስራ እየሄደ ነው። ይህ የእግዚአብሔር ሃሳብ ከትውልድ ወደትውልድ እየተላለፈ የመጣው፣ የእለቱን ሳይሆን የዘላለሙን በተመለከቱ ስዎች ነው። ነገሮችን በራሳችን እይታ ማየት ከጀመርን፣ የመለኮትን ሃሳብ አናሳልፍም፣ እየተራመደ ያለውን የእግዚአብሔርን ስራ ያስቆማል። ማለትም፣ ጌታ በራሱ መንገድ ስራውን ይቀጥላል ግን በኛ አልፎ አይሄድም፣ የጌታንም ስራ በትውልዳችን አናይም ይህ ደግሞ ትልቅ ጉዳት ነው።
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 12 ሮሜ ምዕራፍ 12:3
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ጌታ ባደረገልን ነገር ጌታን ማወቅ አንችልም የሚለው ይብራራልን። 2. ሰዎች ፅድቅን ለማድረግ ከኢየሱስ ጋር የሆኑ እመመሰላቸው ከቴታ ጋር ላይሆኑ ይችላሉ የሚለው ይብራራልን። 3. ለሀጢያት መሞት ማለት ምን ማለት ነው? 4. የማላ የተትረፈረፈ በለከት ምንድን ነው? 5. የተቀበልነው ወንጌል ኢየሱስ ማን እንደሆነ ለእኛ ይወስነዋል የሚለው ይብራራልን።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በዮሐንስ ምዕራፍ 9 ላይ ዐይኑ የተፈወሰው ሰው ጌታን ከተፈወሰ በሗሏ ከማግኘቱ በፊት ምስክርነቱ ትክክል አልነበረም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 2. ጌታን አግኝተውም ሆነ ሳያገኙ ጌታን የተከተሉ ሰዎች አሉ የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 3. ቤተክርስትያም በመከራ ካላለፈች ለጌታ መሆን አትችልም ወይ? 4. “ፊተኛው አዳም ህያው ነፍስ ሆነ ሗለኛው አዳም ህይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ” የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 5. አማሊቅ የማን ዘር ነው? 6. ሰይጣን ሀጢአት ሲሰራ ይህ አለም ቀውስ ውስጥ አልወደቀም ሰው ግን ሀጢያት ሲሰራ ፍጥረት ሁሉ ወድቃል ለምንድን ነው? 7. ብዙ ተምረን ወደ ተማርነው የማንደርሰው ለምንድን ነው
ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል 13 ዮሐ.ምዕራፍ 14:8-11
አጋር በአግዚአብሔር አይን ለመታየት፣ ለሰው አይምሮ እጅግ በሚከብድ ሁኔታ ውስጥ አለፈች። እንዳንድ ጊዜ የተመቻቸና ትክክለኛ ቦታ ያለን እየመሰለን፣ ግን በእግዚአብሔር አይን ውስጥ ላንሆን እንችላለን። ያንጊዜ፣ አግዚአብሔር በእርሱ አይን መታየታችንን ስለሚፈልገው ፣ በመራራ ነገር ውስጥ እንድናልፍ ይፈቅዳል ግን ይሄ የጊዜው መራራ ጉዞ፣ ከዘለአለም ደስታችን ጋር አንደሚያገናኘን አውቀን የመራራውን ጉዞ፣ ከሰው ጋር ሳናያይዝ፣ እግዚአብሔር በአይኑ ለመታየት ሊያበቃን፣ የዘለአለም ባለታሪክ ሊያደርገንና ከተራ ማንነት ሊያወጣን መሆኑን በመረዳት፣ ደስተኞች ልንሆን ይገባናል።
የዲያብሎስን ሽንገላ ለመቃወም ፣ የጌታ እየሱስን ስልጣንና ሃይል፣ እንዲሁም የተሰጠንን መሳሪያ አጠቃቀም ማወቅ አለብን። ይኸውም፣ ወገባችንን በእውነት መታጠቅ፥ የጽድቅን ጥሩር መልበስ፥ የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልናጠፉ የምንችልበትን የእምነትን ጋሻ ማንሳት፤ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ መያዝ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው። በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ እየጸለይን፤ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመነን በመጽናት ሁሉ መትጋት የገባናል።
ጸጋንና ምህረትን ከጌታ የተቀበልን፣ በምህረቱ ውስጥ ያለን አማኞች ሁሉ፣ ልንኖር የሚጠበቅብን፣ ምህረትን እንዳገኘ ሰው ነው። ምህረትን ያገኘ ሰው ደግሞ፣ አይዝም፣ አይቆጥርም ደግሞም አይፈርድም። ነገርን ከእግዚአብሔር ጋር ብናያያዝ በምህረት እየኖርን ነው፣ ነገርን ከስው ጋር ብናያያዝ ግን በምህረት እየኖረን አይደለም፣ ሰይጣን ከህይወት መንገድ እያወጣን ነው። በክርስቶስ ምህረትን ያገኘን ሁላችን ዛሬ ህይወታችንና አኗኗራችን ማንን ይመስላል? የሚጠሉንን እየወደድን፣ የሚረግሙንን እየመረቅን፣ ? ለሚያሳድዱን እየጸለይን፣ በክፉውስ ፋንታ፣ መልካምን እያደረግን ነው?
ደቀመዛሙርቶቹ እርሱን ሲያዩት፣ ሁሉን ትተው ተከተሉት። መንፈሳዊ አይኖቻችን ተከፍተው፣ ጌታን ካላየን፣ የምንፈልጋቸው ጊዚያዊ ነገሮች፣ ክጌታ እኩል ይሆኑብናል፣ አንዳንዴም ከጌታ በልጠውብን እናገኛቸዋለን። ለአንድ መንፈሳዊ ስው ትልቁ ስጦታው የአይን መከፈት ነው። አይናችን ሲከፈት፣ ሁሉን ለመተውና፣ ጌታችን የሆነውን ክርስቶስን እስከመጨረሻ ለመከተል፣ የሚከፈለውንም ዋጋ ሁሉ ለመክፈል የተዘጋጀን እንሆናለን።
የቀደመችው ቤተክርስቲያን አንዱ መታወቂያዋ እግዚአብሔርን መፍራት ነበር። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ስዎች እግዚአብሔርን በመፍራት እንደከበሩና ብዙዎች ደግሞ እርሱን ባለመፍራት ፍርድን እንደተቀበሉ ያስተምረናል። እግዚአብሔርን በመፍራት የምንኖረውን ኑሮ እውን ለማድረግ፣ ለአባትነቱ የሚገባውን አክብሮት ፣ ልጌትነቱ የሚገባውን ክብር፣ በመስጠትና እንዱሁም ለእርሱ ሀሳብና ትዕዛዝ ምላሽ በመስጠት እንገልጻለን። እግዚአብሔርን በመፍራት ስንኖር ጌታ ይከብራል፣ እኛም ከተለያየ የሀጢያት ክፋት እንጠበቃለን፣ እግዚአብሔርን በመፍራት የሚኖሩትን ወገኖች ልብ ደግሞ እናሳርፋለን።
እግዚአብሔር ሰውን የወደደበት ፍቅር ከመታወቅ የሚያልፍ መንፈስ ቅዱስ ብቻ የሚያበራልንና የሚገልፅልን እውነት ነው:: ይህ ፍቅር የበራለት አማኝ ታላቅ ለውጥ በህይወቱ ይሆናል:: በአስተሳሰብና በእይታው ሁሉ ይለወጣል:: መንፈሳዊ ድፍረትም ይኖረዋል:: በእግዚአብሔር የተወደድንበት ፍቅር ሲበራልን በእግዚአብሔር ላይ ያለን ትምክህት ደግሞም ለፍቅሩ የሚኖረን ምላሽ እለት እለት በምንኖረው ኑሮ ይገለጣል:: የምንምር የምንራራ ደግሞም እኛም የምንወድ እንሆናለን::
ጌታ እየሱስ በምድር በነበረበት ጊዜ፣ የአባቱን ፊት በመፈለግ፣ ለሁሉ መልስን ይሰጥ ነበር፣ የጸሎት ስው ነበር። እኛማ ዛሬ በዚህ እጅግ አስቸጋሪ በሆን አለም የምንኖር፣ ምን ያህል ፊቱን መፈለግ ይገባናል? ጸሎት በእምነት ጌታን እንድናውቅ ከማድረጉ በላይ፣ ትሁቱን ጌታ በመምሰል ወደ እግዚአብሔር መቅረብን ያስተምረናል፣ ደግሞም አንዱ የእግዚአብሔርን ቅርብነት የምንመለከትበት መንገድ ነው። እግዚአብሔር ጸሎትን ይሰማል ግን በኛ ጊዜ ሳይሆን፣ በራሱ ጊዜ ይመልሳል። በዚህ ትምህርት ውስጥ፣ ስለ ጥቂት የተለያዩ የጸሎት ሰዎች መልስ እንማራለን።
የሰው ልብ እጅግ አስቸጋሪ ነው፣ ልባችን ለራሳችን እንኳን አይታዘዝልንም ምክኒያቱም የሰው ልብ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነው። የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት ፈቃደኞች ስንሆን ግን፣ እግዚአብሔር ልባችንን ይከፍትልናል፣ ንፁህ ልብን ይሰጠናል፣ እራሳችንን እንድናይና ነገራችንን እንድናስተካክል ይረዳናል ያንጊዜ ከእግዚአብሔር ስዎች ጋር ህብረት ማድረግ አንቸገርም፣ ለመንፈስ ቅዱስ ደግሞ የተመቸን እንሆናለን።
የሰው ልብ እጅግ አስቸጋሪ ነው፣ ልባችን ለራሳችን እንኳን አይታዘዝልንም ምክኒያቱም የሰው ልብ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነው። የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት ፈቃደኞች ስንሆን ግን፣ እግዚአብሔር ልባችንን ይከፍትልናል፣ ንፁህ ልብን ይሰጠናል፣ እራሳችንን እንድናይና ነገራችንን እንድናስተካክል ይረዳናል ያንጊዜ ከእግዚአብሔር ስዎች ጋር ህብረት ማድረግ አንቸገርም፣ ለመንፈስ ቅዱስ ደግሞ የተመቸን እንሆናለን።
ከውድቀት በኃላ በሰው ልጅ ላይ መጀመሪያ የተገለጠው የሰው ጠላት ፍርሀት በሰው ላይ ሰልጥኖ ይኖራል:: በውስጥ ፍርሀት በውጭ ፍርሀት በማግኘት ፍርሀት በማጣትም ፍርሀት:: ከዚህ የፍርሀት ባርነት ነፃ መውጫ መንገዱ አንድ ነው:: እርሱም እግዚአብሔርን መፍራት ነው:: እግዚአብሔርን የሚፈራ እርሱ እንደ ቃሉ ይኖራልና በእግዚአብሔር ላይ ያለው መታመን የበረታ ነው::ሰለዚህ የክፉው ስራና ማስፈራራቱ በእርሱ ላይ ሀቅም አይኖረውም::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ጠላት የሚፈትነን ሰዓት አለው ወይ? በምን ዐይነት ሁኔታ ስንሆን ነው ጠላት የሚፈትነኝ? 2. በመንፈስ የሚመሩ በውስጣዊ ማንነት ብቻ ነው ወይስ በውጫዊ ማንነት መገለጥ አለባቸው ወይ? 3. ማንነታችንን (የጌታ ልጅ መሆናችንን) መንገር ያለበት ማን ነው? 4. በውስጣችን የተቀመጠውን የጥበብ እውቀት ወደ ህይወታችን እንዲመጣ ምን ማድረግ አለብን?
Play Episode Listen Later Oct 23, 2021 11:29
እድገት ጥበብ እና እውቀት በአንድ ላይ መጨመር ማለት ነው ማቴ 10 ያቆ 3:13 2ኛዜና 9:22 መክ 2:3 መክ 1:18 ቆላ 4:5
Play Episode Listen Later Oct 24, 2021 10:21
ያደገ ሰው እግዚያብሔርን ያስቀድማል ማቴ19:4 ዘፀ 12:15 ዘሌ 23:5 ዘፀ 4:23 1ኛ ሳሙ 14
Play Episode Listen Later Oct 25, 2021 12:05
የእግዚያብሔር እውቀት የእድገታችን መሰርት ነው ዘፍ 12 ዮሐ 10 1ዮሐ 5:20 ዮሐ 4 ዮሐ 9 ማቴ 16
Play Episode Listen Later Oct 26, 2021 10:04
መንፈሳዊ ሰልፍ የሌለበት መንፈሳዊ ጉዞ ውርስ የሌለው ነው ሐዋ 14 ሉቃ 9፡62 2ኛ ዜና 25:7-10
Play Episode Listen Later Oct 27, 2021 15:25
ህይወት የሆነው ክርስቶስ እና በህይወት ውስጥ መኖር ኤፊ 1:13 ማቴ 18:8-9 1ኛ ዮሐ 5:12 ዮሐ 15:7 ሉቃ 2:49 ዮሐ 6:26
ያረፈ የተረጋጋ እና የተቀመጠ ማንነት ዘጸ 14:13 ቆላ 3:3 ኤፊ 2 ሮሜ 14
የማይርካ ማንነት እና መንፈሳዊ እድገት ጢሞ 6:6 ፊሊ 4:11 መዝ 73:25
Play Episode Listen Later Oct 30, 2021 12:02
የሰው ትክክለኛ ማንነት ሁሉ በሞላና በተደላደለ ጊዜ እና በጨነቀው ጊዜ ይገለጣል ዘፍ 22 መዝ 118:5-6 ያቆ 1:1 1ኛ ጵጥ 5:10 ዘዳ 32:15
ነገሮችን ሁሉ በእግዝያብሔር ቃል የሚመርምር ማንነት 1ኛ ተሰ 5:20-21 ፊሊ4:8
ያደገ ሰው በተቀርፀበት ማንነት የሚገለጥ ነው ሮሜ 15:3 ዕብ 13:16
Play Episode Listen Later Nov 2, 2021 8:47
በሰላም ወቅት የተደረገውን መልካምነት በክፉ ቀን የማየርሳ ማንነት መዝ 103 ሮሜ 16 ዕብ 6
ስልቹነት ያለማደግ ምልክት ነው 1ኛ ጴጥ 2:3 1ኛ ነገ 19 2ኛ ነገ 2:10-12
ተሸንፎ ማሸነፍ የመንፈሳዊ ሰው እድገት ውጤት ነው ማቴ 5:3-12 ዮሐ 10
Play Episode Listen Later Nov 5, 2021 13:17
ራስን መግዛት እና እግዚያብሔርን ለመምሰል ራስን ማለማመድ ገላ 5:22 ምሳ 25:28 1ኛጵጥ1:5 1ኛ ጢሞ4:8 መኃ2:4 ኤር 4:6
ያወቅነውን የጌታን ቃል ምን ያህል እንኖረዎለን? ሉቃ 5:9
እድገት እራስን መለወጥ እና ለሀላፊነት መብቃት ነው 1ኛ ቆሮ 13:11 አሞ 6
የጌታን ድምጽ በግል መስማት ዮሐ 5:25 ዮሐ 10:4
በጽሎት ማደግ ማቴ 16:21 ኢሳ 43 መዝ 22 1ኛ ነገ 17 ሰቆ.ኤር 3
Play Episode Listen Later Nov 10, 2021 10:16
ነገሮቻችንን ወደ ጌታ ማምጣት ጌታን ወደ ነገሩ ያመጣዋል ማቴ 11:27 ማቴ 17:17 ማቴ 8:7
ያደገ ማንነት በጌታ ስለሚታመን ስለ ነገ አይጨነቅም ማቴ 6:34 ማቴ 7:24 ሉቃ 12
እኛ በጌታ ውስጥ ጌታም በእኛ ውስጥ መሆኑን ማወቅ 1ኛ ዮሐ 3:21-24
ያደገ ሰው ፀሎት እና ያላደገ ሰው ፀሎት መዝ 32:6 ኤር 2:27 ሉቃ 22:46 መዝ 11
በጌታ ያደገ ማንነት እና ያላደገ ማንነት ገላ 4 ሉቃ 11:5-13 ዕብ 4:16
ያደገ ሰው የውስጡን ንጽህና ግድ ይለዋል ያላደገ ሰው ደግሞ ስው የሚያየው የውጭው ማንነቱ ግድ ይለዋል መዝ 51:10 ዘፍ 6:5 ዘፍ 8:21 ማቴ 5:8
ያደገ ሰው ለሚወስነው ውሳኔ ሁሉ የእግዚያብሔርን ሃሳብ የሚጠይቅ ሰው ነው ያላደገ ስው ግን ስዎች የሚሉትን ብቻ ይሰማል 1ኛ ሳሙ 14:36 ሮሜ 8:14 መሳ18:5-
Play Episode Listen Later Dec 17, 2021 9:17
ያደገ ማንነታችን ክርስቶስን በመምሰል ሲገለጥ ባላደገው ማንነታችን ደግሞ ስጋችን ይገለጣል ምሳ 20:22 1ኛ ጵጥ 3
Play Episode Listen Later Dec 18, 2021 13:16
ወዳጅነታችን እንደ ክርስቶስ ባህሪ የሆነ የማይለዋወጥ መሆኑ ማደጋችንን ያሳያል ምሳ 11:17
Play Episode Listen Later Dec 19, 2021 11:28
ክርስትያን የሚያድገው የፈርሰውን ያህል ነው ያደገ ሰው ይሰማል ምሳ 1:32-33 ሮሜ 10:10
Play Episode Listen Later Dec 20, 2021 12:09
ባደገ ሰው ውስጥ ከሚታዮት ባህሪዎች ውስጥ ለሌሎችህ መስጠት ለራስ ከማድርግ በላይ ያስደስተዋል ዕብ 13:16 ሉቃ 6:38
ያደገ ሰው ጦር እቃው ምንድን ነው? ያላደገስ? 2ኛ ቆሮ 10 1ኛ ጵጥ 3
Play Episode Listen Later Dec 22, 2021 11:07
ለሰዎች መሆን ክርስቶስን መምሰል ሲሆን ዋጋ ያስከፍላል ዘኍ 16:45 ኢያ 3፡13 ዘኍ 16፡41
ያደገ ሰው በጽጋ ይኖራል ሮሜ 7 ሮሜ 6:14 ሮሜ 6:11 ራዕ 12:10
Play Episode Listen Later Dec 24, 2021 10:49
ሰው እግዚያብሔርን ተስፍ ካደረገበት በላይ የህይወት አቅም የለውም ሮሜ 8፡24 ሮሜ 8:12 ዘፍ 13:10
Play Episode Listen Later Dec 25, 2021 10:53
ሰው እግዚያብሔርን ተስፍ ካደረገበት በላይ የህይወት አቅም የለውም ሮሜ 8፡24 ሮሜ 8:12 ዘፍ 13:10
Play Episode Listen Later Dec 26, 2021 12:54
በህይወቱ ያደገ ሰው የሰማውን ቃል የመጠበቅ ብቃት አለው በአንጻሩ ያላደገው ሰምቶ የመጠበቅ ብቃት የለወም ሕዝ 3:10 ሉቃ 8:13-15 2ኛ ጢሞ1:14 ራዕ 3:3 ኢዮ 20
Play Episode Listen Later Dec 27, 2021 10:30
በመንፍሳዊ ህይወታችን ሰናድግ ፈረሃት አይገዛንም ዕብ 2:14-15 1ዮሐ 4:18 ኢሳ 8:13 መሳ 6:10 ራዕ 21:8
Play Episode Listen Later Dec 28, 2021 13:38
ያደገ ሰው ወደ ውስጥ የሚያስገባውን እና ከውስጡ የሚያውጣውን በቃሉ እና በመንፍስ ቅዱስ ይመዝናል 1ኛ ቆሮ 2:13 2ኛ ነገ 13 ሐዋ 17:11-28
- የዋህና ዝግተኛ መንፍስ መልበስና አቅምን ከእግዚአብሔር ለመቀበል ተስፋ ማድርግ የትግስት ጉልበት አለው - ጌታን መስለው የሚኖሩ ሰዎች የማያውቁዋቸው ደቀመዛሙርት አልዋቸዉ - የማያምን ባል ያላት ለባሏየመማመን ምክንያት እንድትሆን በኑሮዋ ጌታን እያከበርች ሳትፍታ ምስክር ልትሆን ይገባል
በዙርያችን ባለው ወጀብ እና አውሎንፋስ ሳንናወጥ እግዚአብሔርን ለመስማት በእግዚአብሔር ፀጥታ ውስጥ መገኘት ያስፈልገናል:: ትልቁ የህይወታችንየእምነት ደረጃ ልኩ በእግዚአብሔር ፀጥታ ውስጥ መገኝታችን ሲሆን በመለኮት ፀጥታ ውስጥ በመሆን የእግዚአብሔርን ፈቃድና ምሪት ትክክለኛውን የእግዚአብሔር ድምፅ እንሰማለን:: በመለኮት በፀጥታ ውስጥ ያለች ነፋስ እግዚአብሔርን ትጠብቃለች :: በፀጥታ ውስጥ ለመሆን እግዚአብሔርን በቃሉ ማወቅና መጠጋት አለብን::
እግዚአብሔር ቃሉን አክባሪ አምላክ ስለሆነ እርሱ ቃሉን ጠብቆ ሲመጣ እኛም ቃሉን አምነን እንድንጠብቅ እና በቦታችን እንድንገኝ ይፈልጋል:: መነሻ የሆነውን የእግዚአብሔርን ሀሳብ ሰው ሲጠራጠርም እሱ እንደቃሉ ይገኛል:: ቃሉ አዲስ ያደርጋል ቃሉ ይፈጥራል እሱ ከሀጥያት በቀር በሁሉ የተፍተነ ለሳቱ ለተጠራጠሩ ለደካሞች ለማያውቁ የሚራራ ሊቀካህን ስለሆነ በእግዚአብሔር ቃል ስንፈተን እምነት እንዴሆንልን አለቀ ባልንበት ሰዓት ቃሉን ማከናወን ባህሪው ነው::
ወደ እግዚአብሔር ክብር የምንደርሰው በእምነት ነው:: ሆኖም እምነታችን በመከራ መፈተኑ የማይቀር ነው:: ያለ መስቀል የትንሳኤ ኑሮ መኖር አይቻልምና እውነተኛውን እምነት መመዘኛው በፈተናው አልፎ ጠርቶ መውጣቱ ነው::
ሰው ግራ ሲገባውና ሲጨነቅ መጨረሻው እንደርሰ ሲሰማው እግዚአብሔር የመውጫ በርን ያደርጋል እግዚአብሔር በጠባብ ሁኔታዎች ውስጥ ህይወታችንን የሚያስገባው ማምለጫ ይሆናሉ ብለን የያዝናቸውን ጨርሰን ወይንም ጥለን እርሱን እና የከፈተውን በር እንድናይ ሲሆን የዘላለም ሀሳቡን በከፈተልን ጠባብ በር በመግባት እንውርሳለን:: ከእግዚአብሔር በተሰጠ ሰዓት እና በር ካልተጠቀመ ማምለጥ አይችልም::በዚህ በተከፈተልንየመገኝት እና የመዳን በር ለመግባትደግሞ በመንበርከክ ዝቅ በማለት በመመለስ ወደ መሰረቱ መጠጋት ይኖርብናል::
ቤተክርስትያንን ለማናወጥ በመምጣት ላይ ያለውን ፈተና ለመቋቋም በቃሉም ላይ በመመስረት ከብዙ ስህተት ከሆኑ አስተምሮቶች ለመዳን ጴጥሮስ የሰጠው ምክር።
ከተገለጠው ምልክት ውስጥ የተደበቀውን የእግዚአብሔርን አላማ ማወቅ ከእግዚአብሔር እቅድ ጋር እንድንስማማ ያደርገናል:: የተገለጠውን ጉድለት በሽታ ወይንም ስው የሚያልፍበትን ከባድ የሕይወት ውጣውረድ እግዚአብሔር ለመለ ኮታዊው አጀንዳ መጠቀሚያ ምክንያት ያርገዋል::
ቤተክርስትያን የመንግስቱ መገለጫና የባህሪው ተካፋይ እንዲሁም መቅደሱና የእርሱ ማደረያ ስለሆነች እግዚአብሔር ለቤተክርስትያን የሰጣት ስልጣን በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም አቅም ያለው ነው።
የሰው መንፈሳዊ ህይወቱ በእይታው ልክ ነው። ሙሴ አርቆ ስላየ የፈርዖንን ቤት ለመናቅና ከእግዚአብሔር ህዝብ ጋር መከራ ለመቀበል ወሰነ። አርቆ ማየት ሰውን ትሁት ያደርገዋል።
እግዚአብሔር ፃድቅ አምላክ ስለሆነ የክፋትንና የፅድቅን ብድራት በምድር ላይ ያደርጋል:: ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገር የክፋት ክፍያ በትውልዶች መካከል ይመጣል:: ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ ሰለሆነ ደግሞ በምህረቱ ይገለጣል:: ስለዚህ በአሰጨናቂ ነገሮች ውስጥ ሲታለፍ የምህረቱንና የይቅርታውን ደጅ ማንኳኳት ተገቢ ነው::
እግዚአብሔርን በሚጠብቁ ሰዎች ህይወት ውስጥ የሚከናወኑ ሦስት ዋና ዋና ትላልቅ እውነቶች አሉ:: * ሀይላቸውን ያድሳሉ ( ሣራ በዘጠና አመቷ ወልዳ ለማሳደግ ሀይል ሆኖላታል::) ** እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ አያፍሩም:: *** እግዚአብሔር እርሱን በተስፋ ለምትጠብቀው ነፍሰ የታመነ ነው::
የጴጥሮስ መልዕከት የተፃፈበት ዋና ምከንያት: አማኞችን ለማስጠንቀቅ ነው:: * ከጥቂት ጊዜ በኃላ ክርስትና ከፍተኛ ሥደት የሚነሳበት እምነት እየሆነ የመጣ ሰለሆነ አማኞችንና የቤተክርስቲያን መሪዎችን ለማስጠንቀቅና አውቀትን ለመሰጠት ነው::
2 ጴጥሮስ 1 :3-5 ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት እና የመንግስቱ ወራሽ ለመሆን የተጠራንበትን ህይወት ለማፅናት መትጋት ይኖርብናል መዳናችንን በቅድስና እየጠበቅን መልካም ፍሬ እንድናፍራ የስጋ ምኞት እያስወገድን የእግዚአብሔር መንግሥት ስራ በትጋት እንድንሰራ እና ለመንግሥቱ እንድንበቃ ስራ ፈቶች እንዳንሆን የእግዚአብሔር ቃል ያስተምረናል::
እግዚአብሔርን መስማት እርሱን ከማመን የሚመጣ ነው። በሀይወታችን ያሉንትን የማይመቹትንና ለምቀበል የሚያስቸግሩንን ሁኔታዎች አልፈን ለመኖር የምንችለው፤ እርሱን በመስማትና በእርሱ ውስጥ በመሆን ብቻ ነ።
ጴጥሮስ በ2ኛው የመልዕክቱ ምዕራፎች ዋና ትኩረት የሚሰጠው የምናመልከውን ጌታ ምን ያህል እናውቀዋለን የሚለው ነው:: * በክርስቶስ የተሰጠውን ታላቅ ፀጋ በእርሱ ለመኖር ደግሞም ለመጠበቅ በመጀመሪያ ሰው እራሱ ምን ያህል አቅመ ቢስ እና ዋጋ የሌለው እንደሆነ ማሰብና መረዳት ሲችል ያን ጊዜ ክርሰቶሰ የእርሱ የህይወት አቅም ይሆናል::
2ነገሥት 13 ንጉሥ ኢዮርብዐም ንግሥናውን ሲጀምር እግዚአብሔርን በመስማት ቢጀምርም ነገር ግን በዛው ከፍታ አልዘለቀም:: እግዚአብሔር ሲሰራንና ሲያበጀን እርሱን የሚሰማ ማንነት ይሰጠናል:: -- እግዚአብሔርን እያወቅነው ስንመጣ ፍፁም አምላክነቱንና የማይለወጠውን ቃሉን እንረዳለን:: -- የእግዚአብሔር መልሰ ፍፁም እግዚአብሔርን ከማንጠብቀው ስፍራ አለ::
ማር. 4:35 ጌታ ቀኑን ሙሉ ሲያስተምር ውሎ ወደ ማዶ እንሻገር አላቸው:: *ጌታ እንሻገር ሲል የሚሰራው ሥራ አለ:: ** ጌታ ኑሩ ብሎ ቀን ሲሰጠን እስከመጨረሻው አስትንፋሳችን ድረስ የሚሰራው ሥራ አለ::
መንገድ ማለት በእግዚአብሔር ዘላለማዊ አጀንዳ ውሰጥ ስንሆን በመንገድ ላይ ነን: ከዚህ ውጪ የሆነ ህይወት ግን ከመንገድ ውጭ ነው::
አባቶቻችን ነገን ተስፋ በማድረግ የዛሬን መከራና ችግር ታገሱ:: በምድር ሥንኖር አንዳንድ ነገሮች አይለወጡም ነገር ግን ድል መንሳት የሚቻለው በነገው ክብር ዛሬንስንኖር ነው::
ሐዋርያው በ2ኛ ጴጥሮስ ምዕራፍ ሁለት ላይ የሚያነሳው ዋና ነጥብ ቤተከርስቲያንን ለማስጠንቀቅ ነው:: ጴጥሮስ ሊመጣ ያለው ከባድ አደጋ በቤተክርሰቲያን ላይ እየተጋረጠ መሆኑን ሥለተረዳ ያንን አስቸጋረ ሁኔታ ቤተክርስቲያን ማለፍና መጠንቀቅ እንድትችል ለማሳሰብና ለማዘጋጀት ነው::
የልጆች አስተዳደግ በ 21ኛው ክፍለ ዘመን! ልኞቻችንን በጌታ ተስፋ ቅል ውስጥ አግኝተናቸዋል?
2ኛ የጴጥሮስ መልዕክት ምዕራፍ ሁለት የሚይስተምረን ቤተክርስትያን ከሚያስመስሉ እውነተኛ ካልሆኑ ነብያት እንድንጠበቅ ነው። በዚህ ውስጥ ሊያስጠንቅቀን የፈለገው እውነትን እንድንመርጥ ነው።
ሰው ከእግዚአብሔር መቀበል የሚችለው በውጣበት መጠን ነው። የእግዚአብሔር ነገር በህይወታችን የሚያገኘን ከውጣን ነው። መውጣት ማለት ዋጋ ለመክፈል ፍቃደኛ መሆን ማለት ነው።
በዘመን መጨረሻ ያሉ ሰዎች ክርስቶስ አይመጣም የሚሉት ምኞታቸውን ለመኖር ነው:
በዚህ ክፍል ከቁጥር 10 ጀምሮ ከሀሰተኛ ነብያቶች እና ከዘባቾች በተጨማሪ የእግዚአብሔርን ቃል ለጥቅማቸው የሚያጣምሙትን ያሳያል::
የእግዚአብሔር ፈቃድ እግዚአብሔርን በሚያምኑም በማያምኑ ስዎች ውስጥ ይኖራል በቃሉ እንደሚል "መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሰራ እግዚአብሔር ነው " ይላል :: እግዚአብሔር የሚቀባውን ስው ለቅባቱ ብቁ እንዲሆን ሳይቀባ ያዘጋጀዋል:: ንጉስ ዳዊት ለንግስና ሳይቀባ በመዝሙረ ዳዊት26 የዘመረው ያን ያስተምረናል ::
ትንቢተ ዳንኤል እና የአስቴር መፅሐፍ የታሪክ ተወራራሽነት አለው:: ጌታ ህዝቡ ምንም አይነት ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ቢሆንም እንኳ እርሱ ግን ህዝቡን አይተውም አይጥልም ያድናል ይታደጋልም::
እግዚአብሔር ወደ አየልን ለምድረስ በብርሃኑ መገኘት አለብን። በብርሃኑ ለመገኘት መልካም መሻታችን ወደ እግዚአብሔር መሻት ስር አምጥተን አስገዝተን፤ የእርሱን የልብ ፍቃድ ማገልገል ይኖርብናል ። መሻቱ በሰው እጅ ቢሆንም መፈፀሙ በእግዚአብሔር እጅ ነውና።
ነገ የማያሳስበውና የማያስፈራው ሰው ማንም የለም: ነገር ግን ነገ የማያስፈራው እርሱ ዛሬን በክርስቶስ ያየ ሰው ነው::
እግዚአብሔር የቆረጠው ቀን እስኪመጣ በእርሱ የታመኑት የእርሱ ልጆች በተለያየ መንገድና ፈተና ቢያልፉም ፤ እግዚአብሔር አባት ስለሆነ የቁርጥ ቀን መምጣቱ አይቀርም እግዚአብሔር ያስባል ፣ ያወጣል ፣ በቆረጠው ቀን ይመጣልና በምስጋና እንቁም።
በሰው ህይወት ውስጥ ብዙ ውጣ ውረድ ህይወት አለ። ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ወደ እግዚአብሔር ስንመለከት በነገሮች ሁሉ መጽናናት ይሆንልናል።
ሰው ትክክለኛ ፀሎት የሚፀልየው ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ትክክል ሲሆን ብቻ ነው:: እንደ ቃሉ እና እንደ ፈቃዱ የሆነ ፀሎት ሰማይን ሲከፍት በአንፃሩ ትክክል ያልሆነው ቃሉን የሚፃረን ፀሎት ስማይን ይዘጋል::
በእግዚአብሔር በአርሱ ምርጫ ተወደናል:: በስራችን ግን ጠላቶች ነበርን:: ሰለ ፅድቃችን ሳይሆን ሰለ ፅድቁ ተወደናል:: ስለዚህ ከመዳናችን በፊት ለመዳናችን ከዳንን በኃላ ደግሞ ለተጠበቀልን የዘላለም ተስፋ እንድንበቃ በእርሱ የተጠበቅን ነን::
ነገራችንን ለጌታ ባልተውንበት ሁኔታ ውስጥ የጌታን ባለጠግነት ማየት አንችልም:: እስራኤላውያን ከግብፅ ሲወጡ የተቦካ ሊጥ ይዘው ነበር የወጡት ያግን የሚያኖራቸው አልነበረም:: በምድረበዳ ያኖራቸው የእግዚአብሔር ባለጠግነት ነው::
እግዚአብሔር ሊሰራብን ክብሩንም ሊገልፅብን ወደ ሚፈልግበት ማንነት መሻገር የምንችለው ፤ ከእኛ ማንነት ከወጣንበት፣እንዲሁም ራሳችንን ለፈቃዱ ለማስገዛት በወሰንበት ነው:: የተሻገረ ሰው እርሱ ለእግዚአብሔር መሆን አይከብደውም::
እግዚአብሔር ሁሉን ስለፈጠረ ክፉንም ደጉንም ያያል። ክርስትያን የተደላደለ ህይወት የሚኖረው እግዚአብሔር እንደ ሚያየው ሲረዳ ነው። እግዚአብሔር እንደሚያየው ሲረዳ ለህይወቱ ይጠነቀቃል።
አግዚአብሔር ከህዝቡ ጋር ለመኖሩ ምልክቱ የተቀበሉትና የሚኖሩበት የሚተዳደሩበት ህግ ነው:: እንደፈለጋቸው እንዳይወጡና አንዳይገቡ የእግዚአብሔር ህልውና እየተሰማቸው በፈቃዱ ውስጥ እንዲሆኑ የተሰጣቸው ህግ ዋና ጉዳይ ነው:: *** በአዲስ ኪዳን ለምንኖር ለእኛ ደግሞ እግዚአብሔር ከፊተኞቹ ይልቅ በራሳችን ጥረት ሳይሆን በሚረዳን ፀጋ ይበልጥ በፈቃዱና በሀሳቡ ውሰጥ ልነሆን ይፈልጋል::
ውጤታማ ፀሎት 2ኛ ዜና:20 በፓስተር ሰመረ እዮሳፍጥ እግዚአብሔርን ተስፋ ያደረገ ንጉሥ ነበረ:: በተጨነቀ ጊዜ እራሱን አዋርዶ የጌታን ፊት ፈለገ: በመሰጋናም ወደ ፊቱ መጣ:: በተጨነቅን ጊዜ ከማጉረምረም ወጥተን በምስጋና የአግዚአብሔርን ፊት ልንፈልግ እንደሚገባ ከእዮሳፍጥ ህይወት እንማራለን::
መንፈሳዊ ነገራችን የተቀመጠው በእምነትና በመታዘዝ ላይ ነው። የእምነት መነሻና መደምደሚያው መታዘዛችን ነው።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ዮሐንስ ምዕራፍ 12፡20-29 ላይ ጌታ እየሱስን የጠየቁት ሊያዩት ሆኖ የመለሰላቸው ግን ሌላ ነው። ይህ ክፍል ቢብራራልን። 2. እድሜአችን ከገፋ በሗሏ ጌታን አወቅን ታድያ ጌታን በምንድን ነው የምናገለግለው? 3. መታዘዛችን የሚፈጸመው መቼ ነው? አለመታዘዝን የምንበቀለው መቼ ነው? 4. የበቀል ቅባት ተቀባው ይባላል ቢብራራልን። 5. እግዚአብሔር የእጁን ይስጠው የምንለው ይህ የበቀል መንፈስ ነው ወይ ሌላ? 6. በተፈጥሮ ማንነታችን ስርአት ከሌለን መንፈሳዊ ህይወታችን ስርአት የለውም የሚለው ይብራራልን። 7. አስቀድመን የሠራነው ከሌለን ለጌታ አንጠቅመውም የሚለውን ግልፅ ቢሆንንል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በምናልፈው ነገር እንዴት ነው እግዚአብሔርን ማፅደቅ የምንችለው? እንዴትስ ነው ከእግዚአብሔር ጋር የምንወግነው? 2. እንዴት ነው የከበበንን ጠላታችንን ድል የምንነሳው? 3. በምናየውና በምንሰማው ነገር የምንሰናከለው ከራሳችን ፅድቅ ጋር ስለምናያይዘው ነው ወይ?
ጌታ ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ ስለአለና ስጋ ደግሞ ደካማ በመሆኑ መትጋት የምንችለው በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር ስንሆን ብቻ መሆኑን ሊነግረን ነው፣ ሰይጣን በብርቱ የሚዋጋን መንፈስ ከሆነው አባታችን ጋር የጠበቀ ግኑኝነት እንዳይኖረን በማድረግ ነው ይህን መንፈሳዊ የሆነውን የጠላት አሰራር መዋጋትና ማሸነፍ የምንችለው በመንፈስ ስንሆን ነው፣ በመንፈስ መሆን የሚያስገኘውን ውጤት በዚህ ትምህርት በዝርዝር እናያለን፣
የእግዚአብሔር ቃል ምን ያህል አቅምና ጉልበት እንዳለው የተረዳው ፣የእምነት ምሳሌ አባታችን አብርሃም ልጁን ለመሰዋት አልራራም። አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር የተናገረን ቃልና እኛ የምናልፍበት መንገድ ፈጽሞ ላይገጣጠም ይችላል ሆኖም ግን የተናገረን እግዚአብሔር ይሁን እንጂ፣ የሌለን ነገር ወደ መኖር የሚያመጣ፣ ቃሉን የማያጥፍ ጌታ፣ በቃሉ ይገኛል፣ ከኛ ጋርም ሆኖ የሚያናውጠንን ወጀብ ጸጥ ያደግልናል። ቃል ካለን፣ ባዶ አንሆንም፣ አንወድቅም፣ አንጠፋም፣የማንሻገረውም ማዕበል አይኖርም።
ዛሬ የፍላጎታችንን ትልቁን ስፍራ የያዘው ምን ይሆን? መጽሐፍ ቅዱሳችን ግን፣ በማንንኛውም ችግርና መከራ ወይም በተመቻቸ ሁኔት ውስጥ ብንሆን፣ ሁልጊዜ ይህንን ትልቁን ጌታ እንድንፈልግ ያስተምረናል፣ ስንፈልገው ደግሞ እርሱ ፈጥኖ የሚገኝና፣ ከማንኛውም የመከራ አይነት የሚታደገን አምላክ ነው። እግዚአብሔርን በመፈለግ ብዙ ከምናተርፍባቸው ዝርዝሮች ጥቂቶቹ፣ እንጸናለን፣ ሁሉን ወደ ማስተዋል እንደርሳለን፣ ሌሎችን የሚይስጨንቅ ምድራዊው ነገር አያስጨንቀንም፣ ደግሞም እግዚአብሔርን ስንፈልግም በህይወት እንኖራለን።
በህይወት ዘመናችን ሁሉ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው:: ነገር ግን ደግሞ በህይወታችን ሊያደርግ ሊፈፅም የሚፈልገውን የሚያደረገው በራሱ ጊዜ ነው:: ስለዚህ በምናየው በምንሰማውና ደግሞም በምንሰራው ውስጥ የጌታን አብሮነት መፈተሽ ፈቃዱንም መመርመር ያስፈልጋል:: አግዚአብሔረ እንዳያልፈን ከቸርነቱና ከበጎነቱ እንዳንጎድል ያጀርጋልና:: በዚህ መልዕክት ለትምህርታችን ደግሞም ለህይወታችን መቃናት ይሆን ዘንድ በህይወታችን ሰለምን ምክንያት ጌታ እንደሚያልፈን በዝርዝር እንማራለን::
የተቀበልነው የጸጋ ስጦታ የተለያየ ሆኖ በሁላችን ውስጥ ያለው የጌታ መንፈስ ግን አንድ ነው፣ ይህ የጸጋ ስጦታ እራሳችንን የምናስተዋውቅበት ሳይሆን ክርስቶስን ከፍ የምናደርግበትና ለአካሉ ጥቅም የተሰጠ መሆኑን ልንረዳ ይገባል፣ በዚህ ትምህርት ውስጥ እነዚህን የተለያዩ የጸጋ ስጦታዎችንና ለአካሉ የሚሰጡትን ጥቅሞች በዝርዝር እንማራለን
Play Episode Listen Later Aug 6, 2021 51:26
የእግዚአብሔር ከብዙዎቹ የአምላክነቱ መገለጫው አንዱ፣ ሰውን በስፍራው መመልከት፣ ማወቅና መድረስ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ፈውሶች በእየሱስ ተከናውነዋል ብዙ በረከቶችም ከጌታ ለስዎች ተሰጥተዋል። ይህንን ፈውስና በረከት የተቀበሉ ሰዎች ሁሉ፣ ያልተቅበዘበዙና በስፍራቸው የተገኙ ሰዎች ናቸው። ከበረከታችን ጋር እንድንተላለፍ ሰይጣን የሚጠቀምበት አንዱ ትልቁ መሳሪያው፣ እኛን በማቅበዝበዝ፣ ስፍራችንን አንድንለቅና መገኘት በማይገባን ስፍራ እንድንገኝ በማድረግ ነው። እኛ ግን ያለንበት ስፍራ ምንም የማይመች ቢሆንም፣ ስፍራችንን ላለመልቀቅ በመጨከን፣ የሚለቀቅልንን ጸጋ በመደገፍ በእምነት መጽናት ይገባናል።
እግዚአብሔር ባዶ ወደሆነው ህይወታችን ሲመጣ ለክብሩ ምስጋና ሊያደርገን ታሪካችንንም ሊለውጥ ነው:: በጉድለታችንና በባዶነታችን ጊዜ አጠገባችን ሊቆም የሚወድ ችግራችንንም የሚካፈል ማግኘት ጭንቅ ነው:: ቢገኝም አብሮን የመቆም ችግራችንንም የመካፈል ሀቅሙ ጥቂት ነው:: ክፉውም ይህን ሁኔታችንን ምክንያት አድርጎ ተስፋ ሊያስቆርጠን የሚጠቀምበት ይሆናል:: ጌታ ግን ጉድለታችንን ሊሞላ ሊያቆመንም ተችሎታል:: ስለዚህ ሰው ሁልጊዜም የሚመስለው የተሞላውን ነው:: በዚህ መልዕክት ባዶነታችን በምን ሊምላ እንደሚገባው እንዴት እንደሚሞላም እንማራለን::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ለጣኦት የተሰዋውን አትብሉ የሚለው ቢብራራልን። 2. ወንድም ለመከራ ቢዜ ይወለዳል ሲል ማን ማለት ነው? 3. ምሳሌ 17፡17 “ወዳጅ በዘመን ሁሉ ይወዳል” ምን ማለት ነው? 4. ምሳሌ 24፡26 የምንናገረው ቃል ሀይል አለው ሲል ክፉ ነገር ብንናገር ይሠራል ማለት ነው? 5. ምሳሌ 25፡6 እና 17 ሁሉን ነገር በመጠን መኖር አለብን የሚለው ሀሳብ መንፈሳዊ ነገራችንንም እንዲህ መሆን አለበት ማለት ነው? 6. ሰው ከህይወታችን አጣ ማለት እግዚአብሔር ወደ ህይወታችን የሚመጣበት መንገድ አጣን ማለት ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 7. በአህምሮአችን ያለው ትክክል ነው ብሎ ሰው ካሰበ ወደ መንፈሳዊ ነገር መምጣት አይችልም የሚለው ይብራራልን። 8. በመንፈሳዊ ህይወታችን የአህምሮ መታደስፍ የሚመጣው እንዴት ነው? 9. ጌታ በትክክል በህይወታችን ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው?
እግዚአብሔር በሐይሉ ችሎት የበረታና ለታላቅነቱ ወሰን የሌለው አምላክ ነው፣ አንዳንድ ጊዜ ግን በተለያየ መከራ ውስጥ ስናልፍ፣ ከዚህ እውነት ጎድለን፣ አይናችንን ከእግዚአብሔር ላይ አንስተን፣ እምነታችን ላልቶ እናገኘዋለን፣ አይናችንን ከእግዚአብሔር ላይ ማንሳትና በምናልፍበት ሁሉ እርሱን አላማመናችን፣ የእግዚአብሔርን ችሉት ያጠፋብናል፣ እርሱን ውስን ያደርገዋል፣ እግዚአብሔርን መወስን ደግሞ ሐጢያት ነው፣ እግዚአብሔር አይናችንን እንዲከፍትልንና የእግዚአብሔርን ትልቅነት ዘወትር እንድናስብ እንዲረዳን መጸለይ አለብን
እግዚአብሔር እርሱ የቃል ኪዳን አምላክ ነው:: ስለዚህ የቃል ኪዳኑን ህዝብ ያስባል:: የምናልፍበት ማንኛውም ሁኔታ በፊቱ ነው:: በጊዜው ጉብኝት ይሆናል:: በእግዚአብሔር መታሰባችንም በተለየ ሁኔታ ይገለጣል:: የአስበኝ የፀሎት መልስ እውን ይሆናል:: ጨለማው በብርሃን ይለወጣል:: ከውድቀት መነሳት ይሆንል:: ከድካም መበርታት ይሆናል:: ተስፋም ይሞላል:: በህይወታችን ያለው አንዱ ተስፋ እርሱም በእግዚአብሔር የምንታሰብ ሰው መሆናችን ነው::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሰው ቢበድለን ለራሱ እንንገር እንጂ ለሌላ ሰው መንገር የለብንም የሚለው ይብራራልን። 2. ታዘን እሺ ካልን በሗሏ ባናደርገው ይህ ወደ መንፈሳዊ ህይወት አያመጣንም የሚለው ይብራራልን። 3. ለሰዎች ታማኝ ባልሆንበት ነገር ሰውን እናሳዝናለን ይህ ደግሞ ለመንፈሳዊ ህይወታችህ ጥሩ አይደለም የሚለውን ብታብራራልን። 4. ትዕግስት ማለት ምን ማለት ነው? 5. ትዕግስት ማለት ሽንፈት ማለት ነው? 6. ሰው ተስፋ አላደረገም ማለት የጌታ ፍቅር የለውም ማለት ነው? 7. ታማኝነት ማገልገል ብቻ ሳይሆን መሆን ነው የሚለው ቢብራራልን። 8. ለሎሎች የንስሀ እድል ሲሰጥ ለምንድን ነው ለአዳምና ለሄዋን ያልተሰጠው?
በህይወት ጉዞ ውስጥ መልካምና በጎ የሀሴትና የደስታ ጊዜዎች እንዳሉ እንዲሁ ደግሞ የምናልፋቸው ብዙ አስጨናቂና አስፈሪ ሁኔታዎች ይኖራሉ:: አናልፍም ያልናቸውን አልፈንና ተሻግረን ዛሬን መድረሳችን ከሚመራንና ካሳለፈን ከእግዚአብሔር የተነሳ ብቻ ነው:: የእግዚአብሔር እኛን የመምራቱ ችሎት ከሚያስጨንቀን ከወጀቡ በማሳለፍ ይገለጣል:: በልጆቹ ላይ ክፉው የክፉውም ማስጨነቅ ስልጣን የለውምና:: ይሁ ደግሞ ለስሙ ክብር ይሆናል::
አማኝ የተጠራበት ጥሪ የከበረ እንደሆነና ያገኘውንም የክብር ታላቅነት አጥርቶ ማየትና ማወቅ ዋነኛና አስፈላጊ ነገር ነው:: የጠራንን አምላክ ልጁንም ኢየሱስ ክርስቶስን በማወቅ በተጠራንበትም መጠራት እንደሚገባ ልንመላለስ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድና ደሰ የሚያሰኘውም ነው:: የዚህም መልዕክት ትኩረት በዚሁ ሀሳብ ላይ ነው:: እንዴት እንደሚገባ መመላለስ እንዳለብን በስፋት ይዘረዝራል::
እግዚአብሔር ወደእኛ የሚመጣው በሕብረት በአንድነትና በፍቅር ስንቆም ለእርሱ ስንታዘዝና የሚለንን ስናደርግ ነው፣ ጌታ ደግሞ አንድ ነገርን አድርጉ ብሎ ካዘዘን ክብሩን ለመግለጽ ክብሩን ለማየት ተካፋዮች ሊያደርገንና ጎዶሎ የሆነው ነገራችንን ሊሞላ ነው፣ የሚያደርገውን የሚያውቅ ይህ ትልቅ ጌታ አድርጉ የሚለንን ሰምተን ከታዘዝን የበረከቱ ተካፋዮች እንሆናለን የሚለንን ደግሞ ካላደረግን ክብሩን ከማየት እንጎድላለን፣
አሸናፊ ሕይወት እንድንኖር የሚረዳንና መንፈሳዊ ሰው የሚያስብለን እግዚአብሔር ያየውን ስናይና ያወቀልንን ስናውቅ ነው፣እግዚአብሔር ያየውን ካየን በዙሪያችን ያለ ማንኛውም ሁኔታ አያናውጠንም፣ እርሱ ያየውን ካላየን ግን ከእምነታችን እንጎድላለን ተስፋችን የሆነው እየሱስ ይደበዝዝና በምናየውና በምንሰማው እውነት ባልሆነው ሁሉ የምንናወጥ፣ ጭንቀትንና ፍርሃትን ብቻ የምናስተናግድ እንሆናለን፣ እግዚአብሔር ግን ለአምላክነቱ እውቅናን እየሰጠን ቃሉን ተደግፈን በአረፍት እንድንኖር ይፈልጋል፣
የቤተ ክርስቲያን መብዛት ማለት የአዳዲስ ሰዎች መጨመር ማለት ነው፣ መጽሐፍ ቅዱሳችን እንደሚያስተምረን በስደት የተበተኑት የክርስቶስ ተከታዮች ወንጌልን ለማብሰር ስደታቸው አላቆማቸውም፣ እንዲያውም በደረሱበት ሁሉ የምስራቹን ቃል ያበስሩ ስለነበረ ስደታቸው ለመብዛታቸው ምክኒያት ሆኖላቸዋል፣ ዛሬም እኛ ይህን ደህንነት ያገኘን ሁሉ የእግዚአብሔርን መንግስት ለማስፋት ሀላፊነት እንዳለብን በመረዳት በግልም ሆነ በሕብረት እግዚአብሔር ባዘጋጀልን ስፍራና በከፈተልን በር ሁሉ የክርስቶስን አዳኝነት ለሰዎች ሁሉ ልንመሰክር ይገባናል፣
መንፈሳዊ ህይወታችን ጤናማ መሆኑ የሚታወቅበት አንዱ መንገድ መንፈሳዊ ነገርን የሚራብና የሚጠማ ማንነት ሲኖረን ነው፣ ተፈጥሯዊ ማንነታችን መንፈሳዊውን ነገር አይፈልግም ጌታ ግን ፍቅር ስለሆነ በወደደው መንገድ አሳልፎ እርሱን ፈላጊዎች ያደርገናል፣
አማኝ መንፈሳዊ ህይወቱ ጤነኛ ለመሆኑ መገለጫው ጌታን መጠማቱና መራቡ ነው:: ጌታን መራብና መጠማት ባለበት በዛ ተስፋ አለ:: መፅናናትም አለ:: አስቀድሞ በእርሱ የሚሆንልንን ሳይሆን እርሱን ራሱን ጌታን መጠማትና መራብ ለህይወት መታነፅና እድገት የሆንልናል:: ከእርሱም የሆነው በጎነትና በረከት ይጨመርልናል:: በዚህ መልዕክት ጌታን መፈለግና ከጌታ የሆነውን የመፈለግ ልዩነት እንማራለን::
የምናመልከው አምላክ እርሱ ሁሉን ቻይ አምላክ ነው:: ሰለሆነም በእኛ አይን ምን ከባድና የማይቻል ሆኖ ቢታየን እግዚአብሔር ግን እንዴት ይሆናል አይባልም:: ያልነበረውን ወደ መኖር ባመጣ በእርሱ ዘንድ ቀላል ነው:: ድንቅና ተአምራት የምታደርግ የእግዚአብሔር እጅ ዛሬም ለመርዳት ለማገዝ ለማዳንም የተዘረጋች ነች:: አላጠረቸ::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ክርክራችን ከታላላቆቻችን ጋር ቢሆን ምን ማድረግ ነው ያለብን? 2. ከሰዎች ጋር ያለንን ክርክር ለሰዎቹ ሳንናገር ወደ ፀሎት ማምጣት እንችላለን ወይ? 3. ለበደለን ሰው መልካም ስናደርግ እግዚአብሔር ብድራቱን ይመልስበታል በሚል መንፈስ መሆን አለበት ወይ? 4. ሰው በጌታ ከሆን በሗሏ በህሊናው ባይወቀስ ርሱን መጠየቅ የለበትም ወይ? 5. ሰው ጌታ ካወቀ በሗሏ ቀድመው አብረው ከነበሩ ሰዎች ጋር ያደርግ የነበረውን ላለማድረግ መለየት አለበት ወይ? 6. ከእግዚአብሔር ሀሳብ ውጪ የሚያስተምሩትን እንዴት ነው መለየት የምንችለው? 7. ወንጌልን ለመናገር ድፍረት እስከማጣት የምንደርሰው ለምንድን ነው
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በአሁኑ ግዜ ቤተ ክርስትያን የማይስማሙትን የክርስቶስ አካል ስላልሆኑ ነው የሚለው ይብራራልን። 2. የክርስቶስ መከራ በህይወታችን ካላላፈ ለስዎች መፅናናት መሆን አንችልም ማለት ነው? 3. በወንጌል አላፍርም የሚለውን ብታብራራልን። 4. በሀጢያት ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነታችንን እናጣላን ወይ? 5. ሰዎች ጌታን ከማወቅ ይልቅ ትክክል መሆን አለመሆኑን ለማወቅ ይፈልጋሉ ይህን ማወቅ ጥቅም አለው ወይ? 6. ልጆች ወ ተሳሳተ ትምህርት እንዳይሄዱ ወላጆች ምን ማድረግ ነው ያለባቸው? 7. ወገኖችን ለማፅናናት ሀዘን ቤት ስንሄድ ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? 8. መጨቃጨቅ ማለት ማድረግ ያለባቸውን ስላላደረጉ ያንን ደጋግሞ መናገር ማለት ነው?
በእግዚአብሔር መታሰብ ውስጥ ያሉ ሶስት ነገሮች ቦታ ሁኔታና ሰዓት ናቸው፣ አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ሊያገናኘንና በበለጠ ወደ እርሱ ሊያስጠጋን፣ በወሰነው ስፍራ በተለያዩ ሁኔታዎች እንድናልፍ ይፈቅዳል፣ እነኚህ ሁኔታዎች የመታሰቢያችን ምክኒያቶች ናቸው፣ ሁኔታዎችን ለመቀየር መታገል ለውድቀት እራስን ማጋለጥና መከራችንን ማብዛት ነው፣ የሚሻለን ሁኔታዎችን በእግዚአብሔር እይታ እያየናችው በራሱ ጊዜ በማዳን የሚገለጠውን ጌታን ብቻ ተስፋ በማድረግ እርሱን መጠበቅ ነው፣
ከታማኝነት አንዱ እገዚአብሔርን መጠበቅ ነው፣ የሚታየውና የምናልፍበት ሁኔታ የማይመችና ተስፋ የሚያስቆርጥ ሊሆን ይችላል፣ በዚህ ሁሉ ግን የጠራን አምላክ ታማኝ ነውና በሚሆነው ሁሉ ከእምነት የሚያጎድለንን የሰይጣንን ድምጽ ሳይሆን ታማኝ የሆነውን የእግዚአብሔር የአምላካችንን ቃል ተስፋ አድርገን በስፍራችን እገዚአብሔርን መጠበቅ ይገባናል፣
እኛ ሁላችን ሃጢያተኞችና ፍርድ የሚገባን ሆነን ሳለን እግዚአብሔር በክርስቶስ እየሱስ ይቅር ብሎን በምህረቱ ልጆቹ ስላደረገን እንደተወደዱ ልጆች የእግዚአብሔር የአባታችንን ባህሪይ ልናንጸባርቅ ይገባናል፣ ምህረት ከእግዚአብሔር የተካፈልነው የህይወት ፍሬ ነው፣ ስለዚህ እንደ ምህረት ልጆቹ ለሌሎች መገለጥ የምንችለው በምህረት ነው::
እግዚአብሔር በኛ ጊዜ ላይገኝ ይችላል ነገር ግን ለኛ የዘገየ በመሰለን ሁሉ እርሱ ጻድቅ ነው፣ የእግዚአብሔር መዘግየት ምን ያህል እርሱን ተስፋ እንዳደረግነው አንዱ የሕይወታችን መፈተሻ መንገድ ነው፣ ነፍሳችንን የሚይዝ የእግዚአብሔር የባህሪው እውቀት ከሌለን መታገስ ያቅተናል በእርሱ ባህሪይ ውስጥ ስንሆን ግን ተረጋግተን እርሱን አንጠብቃለን፣
ከእግዚአብሔር ጋር ትክክል ካልሆንን የእግዚአብሔር ፊት ይሰወርብናል፣ ምህረቱ ብዙ ርህሩህና መልካም አባት በመሆኑ ለክፉዎች እንኳን ጸሃይን ያወጣል ሆኖም ግን እንደልባችን ማንንነት የሚገናኘን አምላክ ነው፣ እግዚአብሔር ቃሉና መንፈሱ ባለበት ቦታ ሁሉ ይገኛል ደግሞም ይናገራል፣ መኖሩን ግን ለማወቅና ድምጹን ለመስማት የልባችን ማንነት ይወስነዋል፣ መንገዳችን ግራ ከሆነ እንደመንገዳችን በግራ ሆኖ እናገኘዋለን፣ ልባችን ከቀና ደግሞ መልካምና ቸር ሆኖልን እናገኘዋለን::
እኛ ብርቱዎች ሆነን ሳይሆን እግዚአብሔር ግን ርህሩህ አባትና የታመነ አምላክ ስለሆንና የማንንም ጥፋት ስለማይፈቅድ ለሁላችን አስቀድሞ መንገዳችንን ይነግረናል፣ ሊታለፍ በማይቻልና ምርጫ በሌለበት ሁኔታ የእግዚአብሔር ድምጽ መጥቶ ወደ ፊት እንዲሄዱ ወይ ወደ ኋላ እንዲመለሱ የተናገራቸውና ድምጹን ሰምተው ከክፉ ያመለጡ ከሞትም የተረፉ ብዙ ስዎች አሉ፣ የልቡን ሃሳብ ለልጆቹ የሚነግር አምላክ ነውና እኛ ቀርበን ከጠየቅነው አይደብቀንም፣
የተጠራነው እግዚአብሔርን ለመከተልና የጌታን ነገር ከጌታ ጋር ለማድረግ ነው፣ እግዚአብሔርን መከተል ማለት ደግሞ ምህረትን ፍርድንና ጽድቅን መከተል፣ ትምህርቱን መቀበልና በትምህርቱ ውስጥ መገኘት ማለት ነው፣ በእግዚኣብሔር ትምህርት ውስጥ መሆን በእግዚአብሔር ፍጹም በረከት ውስጥ መሆን ነው፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. መንፈሱን የማይከለክል ሰው ቅጥር እንደሌለው ሰው ነው የሚለው ግልፅ ቢሆንልን። 2. ጌታን የሚከተል የህይወት ብርሃን ይሆንለታል ይላል ግን ለምንድን ነው ጌታን ተከትለን ብርሃን የማይበራበት የህይወት ክፍል የሚኖረን? 3. ስንፍ እና ባህሪ ማንነት ከሆነ እንኚህ ባህሪያት የሚታዩት ባልዳኑ ሰዎች ከሆነ በጌታ የሆንን እነኚህ ባህሪያት ካሉን እንዴት ነው ወደ አዲስ ፍጥረት መምጣት የምንችለው? 4. ወላጆች በልጆች ህይወት ምንድረስ ነው ጣልቃ መግባት የሚችሉት? 5. ከጌታ ጋር እየሄድን ያለን ነገር ሌላ ስለሚሆን ነው ወይ ለሰዎች ጌታን መስጠት የሚያቅተን?
ጌታ እያንዳንዳችንን ብቻችንን ይፈልገናል፣ ብቻውን ለእግዚአብሔር ያልተገኘ ሰው እግዚአብሔር በህይወቱ ስፍራ ያላገኘ ሰው ነው፣ ጌታ ብቻችንን ሲያገኘን ከእርሱ ጋር ጥሩ ህብረት ይኖረናል ደግሞም ባህሪውን እየተላበስን እንመጣለን፣ የባህሪው ተካፋዮች ስንሆን ለሌሎች መገኘት ወይም መትረፍ እንችላለን፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ኤፊሶን 4፡17 “...በአህምሮ ከንቱነት ከእንግዲህ እንዳትመላለሱ እላለሁ።” በአህምሮ ከንቱነት የሚለው ይብራራልን። 2. ታካች የሆኑትን ልጆች እንዴት ነው መመልስ የምንችለው? 3. ትንቢት ተነግሮላቸው ለህብረተሰቡ ሸክም እየሆኑ ያሉታን ልጆች እንዴት ነው ልንመራቸው የምንችለው? 4. ስልጣናችንን ካልተጠቀምን ልጆቻችን ሊታዘዙልን አይችሉም የሚለው ይብራራልን። 5. ትዕግስት ስናጣ የእግዚአብሔር ወደ ሚመስል ነገር ፈቀቅ እንላለን የሚለውን ብታብራራልን። 6. የምንሰብከው ህይወታችንን ይሁን እምነታችንን መሆኑን እንዴት ነው የምናውቀው? 7. ክርስቶስን ከሰበክን በመከራ ቀን እሱን ማሳየት ቀላል ነው ነገር ግን እምነታችንን ከሰበክን በችግር ጊዜ መቆም አንችልም የሚለው ይብራራልን።
የሰማነው የሕይወት ቃል ማንናታችን ሊሆን ይገባል፣ ክርስትናችን ደግሞ ሕይወት ብለን የያዝነው በጊዚያዊ መነካት የሚለካ ነገር ሳይሆን በመሆን የሚለካ ነው፣ በተለያየ ፈተና በመጠላት በመገፋት ስናልፍ እግዚአብሔርን በመፍራት በንጹህ ህሊና በገርነት በእውነትና በጽድቅ ማንነታችን ሊገለጽ ይገባል፣
አንዳንድ ጊዜ የማንወጣው የሚመስለን ችግርና መከራ ውስጥ ስንሆን መፍትሄ ወደምናገኝበት ልንሄድ እንችላለን ብዙ ጊዜ ግን እንዲደረግልን የምንጠብቀው ከሌለን ነገር እንደሚመጣ ነው፣ ጌታ ግን በእጃችን ያለውን ተስፋ የተቆረጠበትን አይጠቅምም አይበዛም ያልነውን ሊያበዛ የሚችል አምላክ ነው፣
እግዚአብሔር ካልተናገረ የመለኮት ሃሳብ ወደ ሰው የሚደርስበት መንገድ ስለሌለ በዘመናት ሁሉ እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን አስኪገባን ይናገረናል፣ ቃሉ እንደሚል ከእግዚአብሔር የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማል፣ በክርስቶስ የእውነት ልጆች ሆነን ተወደናልና እውንትን ለመስማት ልባችን ሁልጊዜ የተዘጋጀ ሊሆን ይገባል፣
መንፈሳዊ ስኬት ማለት እግዚአብሔርን ከፊት ማየት ነው፣ ዛሬ እያለፍንበት ያለነው ወይም ነገ በህይወታችን ለሚመጣው ማንኛውም ፈተና የመወጣጫ አቅም የሚኖረን ጌታን ከፊታችን ባየነው መጠን ነው፣ እግዚአብሔርን ከፊታችን ስናይ በማንኛውም የህይወት ማዕበልና ወጀብ ውስጥ ሳንታወክ ተረጋግተን እንኖራለን፣ እግዚአብሔርን ከፊት ማየት ሲጠፋብን ግን የሚያስጨንቀንንና ተስፋ የሚይስቆርጠንን የጠላት ድምጽ አስተናጋጆች እንሆናለን፣
የእግዚአብሔር ቃል በዋጋ ተገዝታችኍልና የራሳችሁ አይደላችሁም ስለሚል አካሉን ለመጥቀም በምንችልበት ሁሉ የምንቆምና ለበጎ ስራ ሁልጊዜ የተዘጋጀን ልንሆን ይገባናል፣ ለራስ መኖር ትልቅ ውድቀት ነው፣ እግዚአብሔርን መበደል መንፈስ ቅዱስን ማሳዘንና የሙላቱ መገለጫ የሆነችውን ቤተክርስቲያንን ማጎሳቆል ነው፣
የዛሬው ማንነታችን ነገ በህይወታችን ለሚሆነውና ሊገለጥ ላለው ደግሞም ለምንሆነው ዋናና ወሳኝ ነገር ነው:: የእግዚአብሔር ክብር በነገው ህይወታችን እንዲገለጥ በእኛም ደግሞ እንዲሰራ ዛሬ ትሁት ሆነን ፅድቅንም በመምረጥና እርሱን በመስማት በፊቱ ልንሆንያስፈልጋል::
የጸለይንበት ማለት እግዚአብሔር እንካችሁ ብሎ የሰጠን ነገር ማለት ነው፣ የእግዚአብሔር ስጦታ ፍጹም በረከትና መርገም የሌለበት ሲሆን በባህሪው ደግሞ ደግ አባት በመሆኑ የሰጠንን መልሶ አይወስድብንም፣ ልጅን የሚያክል ውብ ነገር ከምጥ በሗላ እንደሚገኝ አንዳንዴ ከውስጣችን የሚወለድ ነገር ካለ እግዚአብሔር እንድናምጥ ያደርገናል፣ በምጥና በስቃይ ውስጥ ስናልፍ በእግዚአብሔር ፊት ጥሩ ባልሆነው ነገር እንዳንያዝ በጥንቃቄ የእግዚአብሔርን ጥሩ ለማወቅ መጸለይና የእርሱን ጥሩ ለማድረግም ሆን ለመቀበል ዝግጁ መሆን አለብን፣
የጌታን ምጽአት ከዘመን ጋራ እንድናስተውል መጽሃፍ ቅዱስ ይነግረናል፣ ጸሎትም መጸለይ የሚቻለው እግዚአብሔር ዘመኑን ከገለጠበት ከበራልን ነው፣ ዘመኑን ካልተረዳን ጸሎትም አይኖረንም፣ እግዚአብሔር ለህዝቡ ሳይናገር ምንም የሚሆን ነገር ስለሌለ እርሱን ብቻ ከሰማን ሳንናወጥ እግዚአብሔር ያለው እንደሚሆን አውቀን መደረግ የሚገባውን ነገር እያደረግን መሆን የሚገባንን እየሆንን የመጣው ዘመን ሳያሰናክለን ጸንተን መኖር እንችላለን፣ ዘመንን ደግሞ ከእግዚአብሔር ካልሰማን እንዴትና ስለምን እንደምንጸልይ አንረዳም ከእግዚአብሔር ለሰሙ ሰዎች ደግሞ እንቅፋት እንሆናለን
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሳምሶን የእግዚአብሔር ቅባት አለው ነገር ግን ቤተሰቦቹ የሚሉትን አይሰማም ነበር ይህ ደግሞ አለማዊ ክርስትያንን ይመስላል የሚለው ይብራራልን። 2. እግዚአብሔርን መናፈቅ እና መጠማት ቃሉን ከተለያየ ቦታ እየሰሙ መሰብስብ ነው ወይ? 3. ፆምን እንዴት ነው የምንፆመው? 4. እንደ ቀልድ አድርገን በተናገርነው ነገር የተጎዱትን ልጆች እንዴት ነው መመለስ የምንችለው?
ንፅህና አንዱ የጌታ ባህርይ ነው:: ይህ የእርሱ ባህርይ በእርሱ ውስጥ ሆነን በተገኘንበት ለእኛ ሆኗል:: አማኝ በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ ያለና የክርስቶስን ህይወት እየኖረ መሆኑ የሚታወቀው በንፅህናው ነው:: ይህ ንፅህና የአይን የልብና የመንፈስ ንፅህና ነው:: ንፅህናችንን እንዳናቃልል ደግሞም እነዳንጥል ከንፅህና የጎደለም መመለስ አንዲሆን የዚህ መልዕክት ዋና ምክር ነው::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሰዎች ጌታ አለን በማለት ዶክተር ያዘዘላቸውን መድሐኒት ባለመውሰዳቸው የሞቱ ሰዎች አሉ እዚህ ጋር ምኑ ጋር ነው ስህተት ያለው? 2. እግዚአብሔር ከፊታችን ካላየነው ነጋችን ጨለማ ነው የሚሆነው የሚለው ይብራራልን? 3. እግዚአብሔር ያላስቀደመ የውድድር አቅሙ ደካማ ነው የሚለው ይብራራልን? 4. ጠንካራ አህምሮ ያለው ሰው ራሱን ደብቆ ለሌላ ሰው ሌላ ባህሪ ሊያሳይ ይችላል የሚለውን ወደ አማኝ ህይወት ስናመጣው እንዴት ነው? 5. የተጠላ ሰው ምንድን ነው ማድረግ ያለበት? 6. የምናልፍበትን ህይወቴ ነው ብለን እንደ ጳውሎስ መቀበል የሚያቅተን ለምንድን ነው?
ይህ ለኛ የደረሰንና ለሚመጣውም ትውልድ የሚተላለፈው የእግዚአብሔር ቃል ስዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው የጻፉት በአይናቸው ያዩትና በእጃቸው የዳሰሱት እንዲሁም ከሰማይ የሰሙት የእውነት ድምጽ ነው፣ ስለዚህ ነው ክርስትናን ልዩ የሚይደርገው ተረት ሳይሆን የተገለጠ ህይወት በመሆኑ ነው፣ አማኝ ወደ ከርስቶስ ከመጣ በኌላ ሁልጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያኖር እውቀት ያስፈልገዋል፣
የመዳናችን መንገድ የወንጌል እውነትና ስለ እግዚአብሔር ያለን እይታ ነው፣ የመዳናችን መንገድ በበራልን መጠን ህይወታችን ትክክለኛውን አቅጣጫ እየያዘ የሄዳል፣ እይታችን ከእግዚአብሔር ጋር ሲበላሽ እጃችን ላይ ያለው ክቡር የሆነው ነገር ሁሉ ይበላሻል፣ እይናችን ተከፍቶ የአምላክ እውቀት ሲገባብን ግን እርሱ የሚያየውን የሚያስፈልገንን በትክክት ማየት እንችላለን፣
ዕለት ዕለት ለመኖራችን ዋስትና የእግዚአብሔር ምህረት ነው፣ ይህንን የተካፈልነውን ሕይወት ደግሞ ለሌሎች ማካፈልን አምላካችን ስለሚጠብቅብን ሁልጊዜ ሰዎችን ሁሉ ለመማር የተዘጋጀ ልብ ሊኖረን ይገባል::
እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል ደግሞም ይፈውሳል፣ በወደደው መንገድ ወደ ወደደው ሰው ይደርሳል፣ በዘመናት ሁሉ ሰውን ከእርሱ ጋር ለማነካካት ምክኒያት የሚሆኑ ስዎች እግዚአብሔር አሉት እኛ እያንዳንዳችን ግን ከእርሱ በረከትና ፈውስ ጋር የምንነካካው ስንታዘዝና እርሱ የሚለንን ስናደርግ ነው::
አንዳንድ ጊዜ የማንወጣው የሚመስለን ችግርና መከራ ውስጥ ስንሆን መፍትሄ ወደምናገኝበት ልንሄድ እንችላለን ብዙ ጊዜ ግን እንዲደረግልን የምንጠብቀው ከሌለን ነገር እንደሚመጣ ነው፣ ጌታ ግን በእጃችን ያለውን ተስፋ የተቆረጠበትን አይጠቅምም አይበዛም ያልነውን ሊያበዛ የሚችል አምላክ ነው፣
ሰዎች በእግዚአብሔር ሰዎች ላይ ስለ ተናገሩት ተቃራኒ ነገር ተባብረን ውድቀታቸውን ማውራት የተገባ አይደለም፣ ከመፍረድ በፊት የምንናገረውን ሁሉ በእግዚአብሔር ቃል እየመረመርን ነው ማየት ያለብን፣ በዚህ መልክት ውስጥ የእግዚአብሔር ቃል ስለ የሃሰተኛ አስተማሪዎችና ነቢያቶችን ባህሪይ ምን አንደሚል እንማራለን፣
በጸሎት ውስጥ ያለ ማስተዋል ቆላ 2:2 ዳን 5
የነፍሳችን መዳን አንድ ጊዜ የተከናወነና በመንፈስ ቅዱስ ምስክርነት የተረጋገጠ ሲሆን ነገር ግን ዘወትር በእርሱ ማዳን የምንኖር ሰዎች ነን:: እግዚአብሔር ዘወትር ማዳን አለው ፥ መውጫ አለው ይህ ማዳን ደግሞ የማያቋርጥ ሒደት ነው እርሱ በማዳኑ የታመነ አምላክ ነው::
ጳውሎስ በተለይ በአይሁድ ወገኖቹ በኩል በመከራ ውስጥ ቢያልፍም የአይሁድ ሸክም ግን ሁልጊዜ በልቡ አለ:: አገልግሎቱን የሚያከበር እርሱ ከሚችለው በላይ እንደማይፈተን የተረዳ ነው:: በተሰጠን ዘመን ልናደርግ የሚጠበቅብን አንዱና ዋናው ወንጌልን ልንመሰከር እንደሆነ ጳውሎስ ምሳሌያችን ነው::
በጌታ ደስ ይበላችሁ ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ:: የክርስትና ህይወት ሁለት ዋና ነገሮች አሉት፤ ሰው ሁልጊዜ በጌታ ደስተኛ መሆንና ፥ ሰው ለአምላኩ ክብር መኖር::
ጌልጌላ እያሱ 4:16--5:12 በፓስተር ሰመረ እስራኤላውያን ጠላቶቻቸውን እያሸነፉ በድል እየገሰገሱ ቢሔዱም: ደግሞ ቆም ብለው ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ራሳቸውን የሚያሰማሙበት ደግሞም እረፍት የሚያደርጉበትና ለሚቀጥለው ጉዞ ምሪት የሚቀበሉበት ሰፍራ ነበረ ጌልጌላ:: - ዛሬም እኛ ቆም ብለን የጌታን ፈቃድ የምንጠይቅበት ደግሞም ምሪት የምንቀበልበት ጊዜና ቦታ ያስፈልገናል::
እግዚአብሔር ሰውን ወደራሱ ለመጥራት ውጫዊ ነገራችንን ሊጠቀም ይችላል:: ሰዎች ልባቸው በተሰበረበት ሰዓት አለኝ የሚሉትን ሲያጡ ሀዘን ሲጫናቸው ተስፋ ሲቆርጡ ወደ ጌታ ዘወር ለማለት ምቹ ሁኔታ ይፈጥርላቸዋል:: ይህንን ከሩት ህይወት እንማሰለን::
በአማኝ ህይወት ሊቀድም የሚገባውና ሁለንተናውን መግዛት ያለበት እግዚአብሔር ያለውን ቅድሚያው በማድረግ ነው:: በቀረው ነገር ላይ እግዚአብሔር አባት ነውና አትጨነቅ ይላል:: እግዚአብሔር ያለው አርሱ ቅድሚያችን ሲሆን እየተሞላን አንሄዳለን:: በእግዚአብሔር መንፈስ ልባችንና አዕምሮአችን የተጠበቀ ይሆናል:: በጥበብና በማስተዋልም እንጨምራለን::
የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችን በመንፈስ ቅዱስም መታተማችን መዳናችን በእምነት ነው:: በዚህ ምድር ስንሆን እንድንኖር የተፈቀደልን በእምነት ነው:: በዚህም ምክንያት ሰለሁሉ እንፀልያለን:: እንደዚሁም እውቀትና ምሪተም አሰፈላጊዎቻችን ናቸው:: በህይወት ጉዟችን ተፈትነን መንፈሳዊ ሆነን ያልተገኘንበት ያ የኛ ክፍተት ነው::
የምንኖርበት ይህ አለም በብዙ የሚያደክም ደግሞም የሚያታክት እንደሆነ ግልፅ ነው:: የእግዚአብሔርን ፊት በመፈለግና እርሱን በመጠበቅ ግን አንዳንታክት እንዳንደክምም ቅዱስ ቃሉ ይመክረናል:: በእምነት እግዚአብሔርን መጠበቅ በውስጡ ሀይል አለው ተስፋ አለው ክብር አለው:: እግዚአብሔር በቃሉ የታመነ ነውና::
በዚህ ክፍል ውስጥ ሐዋርያው በወንጌል ያገኛቸውን ወንድምና እህቶችን ካሳዩት ፍቅርና ስጦታ ምክንያት ይባርካል:: የአማኝ የኑሮ መርህ ያለኝ ይበቃኛል የምኖረው በፀጋው ነው በሚል መሆን አለበት:: ካለን ከሞላን ይልቅ በሌለን ላይ ጌታ በፀጋው ይገለጣል::
እግዚአብሔር በእያንዳንዳችን ላይ ያለውን መልካም ሀሳብ እንዲፈፅም እምነት ከእኛ ይጠበቃል:: በእምነት ለምነበረታ ለእኛ ደግሞ እውቀትና ምሪት ይሰጠናል:: በጌታ በእምነት የሆነ እውቀትና ምሪት በህይወታች ያለውን ክፍተት ይሞላል::
ሰው በጌታ በኢየሱስ ሊያምን የሚችለው ሰለተማረና ሰላወቀ ሰለተረዳ አይደለም:: ነገር ግን ጌታ ራሱ በሰው ልብ ውስጥ ባለው ጨለማ ላይ ብርሃን ያበራል:: ያን ጊዜ በበራለት ብርሀን ምክንያት ያምናል:: መንፈስ ቅዱስም ህይወትን ይቀይራለ:: **** ጌታ በፀጋው ጠራን በፀጋው ለየን በፀጋው አዳነን በፀጋው እንኖራለን በፀጋው እሩጫችንን እንፈፅማለን::
ሸክም ማለት ሰው ከእግዚአብሔር ነገረ (ሀሳብ ወይምፈቃድ) ጋር የሚነካካበት ማለት ነው:: በእግዚአብሔር ሸክም አስቀድመን ካልተያዝን በሰው ህይወት ውሰጥ ሀሳባችንን ህይወታችንን የሚቆጣጠሩ ሌሎች ነገሮች አሉ:: ከእግዚአብሔርም ሩቅ ያደርጉናል:: *** የራሳቸውን የተዉና ለጌታ ሸክም ራሳቸውን ባዶ በማድረግ የሰጡ እነርሱ ፀጋን የተሞሉ በእርሱ መገኘት ውስጥ የሚኖሩ ናቸው::
የብርሀን ወንጌል በህይወታችን ሲበራ በእኛ ላይ ከሚሰራው ነገር አንዱ ካለፈው ታሪካችን ያወጣናል ይገላግለናል:: የብርሀን ወንጌል የብርሀን ሰው ያደርገናል:: *** በብርሀኑ የተነካ እርሱ ለመማር ለመስተካከል ለመታረምም ራሱን ትሁት አድርጎ የሰጠ ነው::
የእግዚአብሔርን ባህርይ አሰራሩንም ባለማወቅ ወደ ህይወታችን ከሚመጣው ፈተና የተነሳ ለፀሎታችን መልስ ሳናገኝ ሰንቆይ የሚደግፍ አይዞህ የሚል ሲጠፋ ያንግዜ እግዚአብሔር ረሰቶኛል ማለት ነው? እንላለን:: እግዚአብሔር ህዝቡን ከቶውንም አይጥልም ነገር ግን አመጣጡን አሰራሩን አደራረጉን አሰፍተን እንድናይ እንድንጠብቅም ይፈልጋል:: በማናውቀው መንገድ ይመልሳል ይመጣልም::
የቤተክርስቲያን ጤንነት የሚጠበቀው ጌታ ባስተማረው ትምህርት ስንኖር ነው:: ዝቅ ማለት ከተቀበልነው የመዳን ፀጋ ሳንወጣ መኖርና እርስ በእርስ መቀባበል ዋናዎቹ ናቸው:: በትህትና በፍቅርና በመቀባበል ህብረት የተጠበቀ ይሆናል ተሀድሶና የመንፈሰ ቅዱስም ጉብኝት ይሆናል::
እውነተኛ ወንጌል በመጀመሪያ የሚያደርገው ሰው ኃጢአተኛ መሆኑን መግለጥ ነው:: ሰውም ይህ ብርሀን በበራለት ጊዜ ለተገለጠለት የወንጌል እውነት ይታዘዛል ይገዛል:: ወንጌልም በእምነት ብቻ በፀጋው የሆነ መዳንን የሚገልጥ ነውና:: ስለዚህ ጌታን መቀበል ማለት ኃጢአተኛ መሆንን ማመን በደለኛነትን መረዳትና በእኛ ምትክ ሰለኃጢአተ ስርየት ለመስዋዕት ራሱን የሰጠውን ጌታ ኢየሱስን ማመን ነው:: መዳን በእኛ ሳይሆን በእርሱ ችሎት ብቻ የሆነ ነውና::
እምነት በጌታ ላይ መደገፍን ሀሳብን በእርሱ ላይ መጣልና በነገር ሁሉ በጌታና በቃሉ ላይ መታመንን ሁሉ የሚመለከት ነው:: አማኝ ከእምነት ወደ እምነት እያደገ እንደሚሄድ ሁሉ በተቃራኒው ደግሞ ከእምነት እየተንሸራተተ የሚወርድበት ብሎም እምነቱን የሚጥልበት ጊዜ አለ:: እመነታችንን ከጌታ ጋር ያለን ህብረትና የህይወታችን ሁኔታ ፅድቅና ቅድስና ለቃሉም ያለን መታዘዝን መኖር ይወስነዋል::
Play Episode Listen Later Dec 26, 2020 43:40
አንድ አማኝ የመነፈስን ምሪት የሚያገኘው በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ ራሱን ባገኘበት ነው:: ወደ እርሱ መገኘት የሚያስገባን ደግሞ የሞተ ማንነታችን ነው:: የእኛ ብቃት ያለው በጌታ መገኘት ውስጥ ነው:: በዛ ውስጥ ለጥያቄ ሁሉ መልስ አለ:: ባልተመለሰውም ጥያቄ እንኳን በሚሰጠን ፀጋ በምስጋና ውስጥ ሆነን በእውነተኛ አምልኮ እንቀጥላለን::
አማኝ በጌታ መገኘት ውስጥ አየኖረ ነው የሚባለው እርሱ ሞቶ በሁለንተናው ጌታ የሚኖርበት ህይወት ሲኖር ነው:: በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ የሚኖር እርሱ የእኔ የሚለው እውቀት ትምክህትም የለውም በማናቸውም ሁኔታ ትምክህቱ ጌታ ነው:: ይህም ትምክህት ደግሞ የሚፈተንበት ቀን ይመጣል ያንጊዜም ከብሮ ይወጣል:: ክርስቶስን በህይወታችን የምንኖረው በእርሱ የተመካንበትን ያህል ነው::
እውነተኛ ወንጌል ሰውን አያቆላምጥም ወይንም ደግሞ አያባብልም:: ነገር ግን እውነተኛውን የእግዚአብሔርን ፅድቅ ይገልጣል የሰውንም ሀጢአተኛነት ይናገራል:: ደግሞም መዳንን ሰው ህግን በመጠበቅ በስራው የሚያገኘው ሳይሆን በፀጋው ብቻ በእምነት የሚገኝ መሆኑን ያበስራል:: በፀጋው ራሱን ያወቀ ሰው እርሱ ራሱን ይገዛል:: እኔ አልችልም የቻልኩትን ሁሉ የቻልኩት በፀጋው ነው ይላል:: ሰለዚህ የሚናገረውንና የሚሰራውን ሁሉ በማስተዋል ያደርጋል:: በደረሰበትና በተቀበለው ፀጋ ልክም ይመላለሳል::
አማኝ በጌታ መገኘት ራሱን ማግኘት የሚችለው ብቻውን የሆነውን ያህል ወይንም ለጌታ የተገኘውን ያህል ብቻ ነው:: ምክንያቱም ለእርሱ ከተገኘንበት በላይ ለመሆን ብቃት የለንምና ነው:: ለጌታ ብቻውን መገኘት የሚችለው እርሱ ሁሉን የተወ ጥያቄው እግዚአብሔር ብቻ የሆነው ነው:: ለብቻችን ለጌታ የተገኘንበት ማንነተ በአርሱ ሙሉ ከመሆኑ የተነሳ ወደጎን ከቅዱሳን ጋር ያለንም ግንኙነት በረከትና ሰላም ያለው ይሆናል ::
የእግዚአብሔርን ቃል መስማት እጅግ መልካምና ዋና ነገር ነው:: ነገር ግን የምንሰማው የእግዚአብሔር ቃል የሚጠቅመን በእምነት ከህይወታችን ጋር ሲዋሀድ ነው:: ይህ ሲሆን ፍሬ ማፍራት እንጀምራለን እግዚአብሔር ልንደርስ ወደሚፈልገውም ከፍታ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ መምሰል ህይወት እናድጋለን:: ሰው የሰማው የእግዚአብሔር ቃል የህይወቱ መሠረት እንዲሆንለት ፍሬም እንዲያፈራ ለሰማው ቃል መታዘዝና መወሰን ዋጋም ለመክፈል መጨከንን ይጠይቃል::
እግዚአብሔር የራሱን ፅድቅ ያቆመው ለሰው ሁሉ ሲሆን የሚያምኑትን ለማፅደቅ ነው:: ያለ ሥራ እንዴው በፀጋው ይፀድቃሉ:: የፀደቀም አማኝ እለት እለት ይቀደሳል:: ህግን በመፈፀምለመፅደቅ የሚታገል እርሱ ግን ከክርስቶስ ተለይቶ ከፀጋው ይወድቃል:: በእምነት በሆነ መስማማት በፀጋው የዳነ ህይወት የሚሰጠውንም መንፈስ ቅዱስን የተቀበለ አማኝ ለሀጢአት ሞቶ ለፅድቅ ይኖራል እንጂ ወደ ህግ አይመለስም::
ለብዙዎቻችን በምንወደው መደሰት ቀላል ነው፣ በጌታ ፈቃድ መደሰትን የተለማመዱ ክርስቲያኖች ግን ጥቂቶች ናቸው፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ አለመደሰት ማለት ለእግዚአብሔር አለመታዘዝ ማለት ነው፣ እኛ የማናየው ጌታ ግን የሚያየው ማንነት በውስጣችን ስላለ፣ አንዳንዴ በራሳችን ፈቃድ ስንሄድና የማንወጣው መከራ ውስጥ ስንገባ እርሱ ቸርና የፍቅር አምላክ በመሆኑ እጃችንን ይዞ ያወጣንና ከርሱ ፈቃድ ጋር ያገናኘናል፣
በደሙ ታጥበው ንስሐ በገቡ ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ እንደሚኖርና አንድ ሰው ከዚህ መንፈስ ቅዱስ ከተወለደበት ቀን ጀምሮ ለዘለአለም ይህ መንፈስ አብሮት እንደሚሆን የመከረን ያለውን የሚያደርግና የተናገረውን የሚፈጽም እውነተኛ አምላክ ጌታ እየሱስ ክርስቶስ ነው፣ ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ከኛ ጋር እንደሌለ አይምሮአችን እንዲያስብ መፍቀድ የለብንም፣
ብዙ ነገር ከሰው መሰወር እንችላለን ከጌታ ግን ለንሰውር የምንችለው ምንም ነገር የለም፣ እንዳንድ ጊዜ የአስተሳሰብ ውድቀት በህይወታችን ሲኖር ወይም ጥላቻ ቂምና በቀል በውስጣችን ሲኖር ከእግዚአብሔር ልንሰወር እንሞክራለን፣ ግን እግዚአብሔር በነገራችን ላይ የሚገለጠው ነገራችንን ለእርሱ በገለጥንበት ነው፣ ከእግዚአብሔር የደበቅነው የመሰለን ነገር ገዳያችን ሲሆን ለእርሱ የገለጥነው ነገራችን ደግሞ ፈውሳችን ነው፣ በተገለጠ ነገር ላይ ጌታ በክብር የገለጣል፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. መንፈሳዊነት እግዚአብሔርን የቀደምንበትን እና ያልቀደምንበትን ማወቅ ነው የሚለው ቢብራራልን። 2. ለሰላም አብሮ ለመኖር ተብሎ ሰው ሲያጠፋ እየታየ ዝም ይባላል ይህ እንዴት ነው ሊሆን የሚችለው? 3. ፍቅር ስለሌለ ነው ወንድሙን የሚጠላ ነፍሰ ገዳይ ነው የሚለው? 4. ለበጎ ነገር የሚነሳሳ ልብ ከሌለን ህይወታችን ትርጉም ሊኖረው አይችልም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. ሰዎችን ስህተታቸውን ስንነግራቸው የሚቆጡ አሉ ለእንደዚህ ላሉት እንዴት ነው ስህተታቸውን መንገር የምንችለው? 6. ሰው ጌታን ወደ ቤቱ አስገብቶ ጌታን ግን ወደ ልቡ ላያስገባ ይችላል የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 7. ስንፀልይ አንዳንድ ጌዜ ሀሳባችንን የምናሳይ ይመስለናል የሚለውን አብራራልን።
የእውነተኛ ትንቢት ምንጩ እርሱ እግዚአብሔር ነው:: አገልጋዩም ይህንኑ በመንፈሱ ከእግዚአብሔር የሰማውን መልዕክት ከራሱ ስሜትና ፈቃድ ጋር ሳይቀላቅል ይናገራል:: ከእግዚአብሔር የሆነው ትንቢትም ሊፈፀም የግድ ነውና መልዕክቱ የመጣለትም እንዲሁ ከራሱ ወይንም ከሁኔታዎች ጋር ሳያስተያይ በእምነት ሊቀበል ደግሞም በጥንቃቄ ሊጠባበቀው ይገባል:: ይህን ሀሳብ በተመለከተ በዚህ መልዕክት በስፋት እንማራለን::
እግዚአብሔር የሚጎበኝ አምላክ ነወ፣ እግዚአብሔር ሲጎበኝ ተስፋን ይፈጽማል፣ የሰጠንን የምንጠብቀውን ተስፋ እንድንጨብጠው ያደርጋል፣ ጸሎታችንን ይሰማል፣ እግዚአብሔር ሲጎበኘን እንጸናለን፣ ከመከራ የሚያወጡንን ሰዎች ያዘጋጅልናል፣ ጠላቶቻችንን ያዋርዳል ደግሞም እንጀራን ይሰጠናል::
ይቅርታ ማለት የጎዱንን ሰዎች መልሶ ለመጉዳት የሚቻለውን መብት መተው መብትን አለመጠቀም ማለት ነው፣ ይቅር አለማለት ጸሎታችን እንዳይሰማ ያደርጋል በእግዚአብሔር ፍቅር እንዳንመላለስና መራራ ህይወት እንዲኖረን ከማድረጉም በላይ በጤናችን ላይ ቀውስን ያመጣል፣ ጌታ እኛን ይቅር ሲለንና ሲወደን እንዲቀበለን የሚያደርግ አንዳች በጎነት ተገኝቶበን አይደለም፣ ይህንን የተካፈልነውን የይቅርታ ህይወት ለሌሎች ማካፈል ይጠበቅብናል::
በየዘመናቱ ወደኋላ እንድናይ የሚይደርጉን ብዙ ነገሮች አሉ፣ ጌታ ግን ያለፈውን በደላችንንና ሐጢያታችንን ላያስብ የእዳችንን ፅህፈት ደምስሶታል፣ ስለዚህ ያለፈውን በደል ማሰብ የአሮጌው ሰው ባህሪ ስለሆነ ወደፊት ለመሄድና ከፊታችን ያለውን ለመያዝ በትጋት ቃሉን ማጥናት መጸለይና ህብረትን ማድረግ ይጠቅመናል፣
አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ የጌታን መንገድ የተከተለ ሰው ነው፣ አካሄዳችንን ከእግዚአብሔር ጋር ስናደርግ በእግዚኣብሔር ፊት ቅኖች በሰውም ፊት በደል የማይገኝብን እንሆናለን፣ አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር ሲሆን የምናዝን የምንምር የዋሆች ጽድቅን የምንራብ ልበ ንጹሀንና የምናስተራርቅ እንሆናለን፣ አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር ሲሆን የእምነታችን ጀማሪና ፈጻሚ እስከ መጨረሻው እንድንዘልቅ ይረዳናል፣
እግዚአብሔር ሰውን የሚጎበኘው በራሱ ጊዜ ሲሆን በመንፈስ ቅዱስ ውስጥ የሆነ ሰው ሁልጊዜ ለእግዚአብሔር ጉብኝት የነቃ ነው፣ ዘወትር በመንፈሱ ውስጥ ስንሆን ከሐጢያት እየሸሸን በምናየውና በምንሰማው ስፍራችንን ሳንለቅ ተረጋግተን በንቃት እንኖራለን፣ በጌታ ከመጎብኘት የሚያጎድለን አንዱ አለመዘጋጀት ነው፣ ብዙዎቻችን እንጸልያለን እናመልካለን ደግሞም እናገለግላለን ለጌታ መገኝት ግን የነቃን አይደለንም ይህ ከአርሱ ጉብኝት ውጪ ያለው አደራረጋችን ይለመድና እርሱ ሊጎበኘን በመካከላችን ሲመላለስ አንረዳውም፣
በመንፈስ ቅዱስ እሳት የሚያጠምቀው እየሱስ ክርስቶስ እራሱ ሲሆን በዚህ መንፈስ ቅዱስ እስት ለመጠመቅ ሰው ንስሐ መግባትና በክርስቶስ እየሱስ ደም መዋጀት አለበት፣ በመንፈስ ቅዱስ እሳት ከተጠመቅን በኌላ ደግሞ እሳቱ እንዳይጠፋ በቃሉ በጸሎትና በቅዱሳን ህብረት እየተጋን ይህንን እሳት ማቀጣጠል የእያንዳንዳችን አማኞች ድርሻ ነው፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ስለ ፍቃዳችን ስንኖር የምንኖረው ኑሮ ልክ እንደ አለማዊ ሰው ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. መንፈሳዊ ህይወት ዘመኑን አውቆ መዋጀት ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 3. ቅዱሳን የሚለያዩት ስል ዘመኑ ሲነጋገሩ ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. ምን ዐይነት ፀጋ ሲኖረን ነው ዘመኑን መርምረን ከህይወታችን ጋር የምናወህደው? 5. ሰውን ለማቅናት ሰውን መውደድ አለብን የሚለው ሀሳብ ቤተሰብንም ይጨምራል ወይ? እኛም ደካማ ሰለሆንን ወደ ታች ወርደን ነው ሰውን ማቅናት ያለብን ማለት ነው? 6. ሰው እንዳይፈተን ሰውን ምን ያህል ነው ማመሰገን የምንችለው?
በዘመናት ሁሉ ብዙ ፈልገን ያላገኘናቸው ነገሮች አሉ፣ እግዚአብሔር ግን ከፈለግነው ይገኝልናል፣ እርሱን ፈልገን ካገኝነው ደግም ከመልካም ነገር ሁሉ አንጎድልም፣ ታሪካችንን ይቀይራል እውነተኛ እርካታ ወደ ህይወታችን ይመጣል ለራሳችን እንኖር የነበርን ያለንን ለሌሎች ማካፈል እንጀምርለን፣ እግዚአብሔር ባለበት በዚያ በረከት አለ፣ እድሳትና እርካታ አለ፣ ምርኴችን ይመለሳል ቜጠሯችን ሁሉ ይፈታል፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ፀሎት መናገር ብቻ ሳይሆን የሚሰማ ጆሮ ያሰፈልጋል የሚለውን ሀሳብ አብራራልን? 2. ያለ ግዜው እንዳንፈርድ ቃሉ ይለናል የሚለውን ሀሳብ ግልፅ አድርግልን። 3. ወደ ፀንቶ ደጅ መጥናት መድረስ የምንችለው እንዴት ነው?
ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን ከሞተ ህይወት ትንሣኤን ያገኘ ደግሞም ዳግም የተወለደ ሰው በእርሱ ውስጥ የጌታ መንፈስ አለ:: ስለዚህ ሁልጊዜ ናፍቆቱና መሻቱ ጌታን ነው:: ህይወታችን ከክርስቶስ ጋር ተሰውሯልና ከምድር በሆነው ከአመፀኝነት ከክፋትና ከትዕቢት ጋር አንተባበርም:: የትንሤኤ ልጆች ነንና በመንፈስ ቅዱስ እገዛ ከሁሉ የላቀውንና የከበረውን በላይ ያለውን ጌታ እየናፈቅን በትጋት እንኑር::
እግዚአብሔር የሚሰራው በጊዜ ውስጥ ነው፣ መንፈሳዊነት ደግሞ ከእግዚአብሔር ጊዜ ጋር መራመድና ጊዜውን ማስተዋል ነው፣ ለእያንዳንዱ ነገር ተወስኖ የተሰጠ ጊዜ አለ፣ ሁሉም ከጊዜው አያልፍም፣ ሁሉ በጊዜ የተወሰነ ነው፣ ሰው ግን በራሱ ጉዳይ ሲያዝ ዘመንን ለመዋጀት የእግዚአብሔርን ነገር የሚሰማበት ጆሮ የለውም፣ ጊዜን የሚሰማ ጆሮ ደግሞ ከሌለን የጊዜው ጸሎት የለንም የጊዜው ጸሎት ከሌለን ደግሞ የጊዜው መልስ የለንም፣ ከእግዚአብሔር ጊዜ ጋር ስንራመድ ጠቃሚዎች ለዘመኑ መልስና ለእግዚአብሔርም መልክተኞች እንሆናለን፣
የእግዚአብሔርን ሞገስ በህይወት ለማየት የመጀመሪያው ነገር ለእግዚአብሔር መቀደስ ነው፣ ለጌታ ለመቀደስ ደግሞ ማንነትን ማወቅ አስፈላጊ ነው፣ በክርስቶስ እየሱስ ደም ተዋጅተን ለእርሱ የተለየንና በእርሱ ደግሞ የተቀደስን መሆናችንን በማሰብ ህሊናችንን ከሚያቆሽሽ ማናቸውም ርኩሰት እራሳችንን መጠበቅ ይኖርብናል ደግሞም የጠራን ቅዱስ እንደሆነ በኑሮአችን ሁሉ ተቀድሰን እንድንኖር ይጠበቅብናል፣
መንፈሰ ቀና መሆን ለእግዚአብሔር በረከት መንገድን ይከፍታል፣ ከጌታ ጋር ለመራመድ የምንችለውና የበረከቱ ተካፋዮች የምንሆነው ልባችን የቀናውን ያህል ነው፣ ልባችንን ደግሞ የሚያቀናው ቃሉ ነው፣ የእግዚአብሔር ቃል ሲገለጥልን ህይወታችንን ይቀርጽና የቀና መንፈስ እንዲኖረን ያደርጋል መንፈሳችን በቀና ቁጥር ደግሞ ለእግዚአብሔር እሺ ባዮች ገርና ቅን ባህሪይ ይኖረናል ደግሞም ከሌሎች የእግዚአብሔር ሰዎች ጋር በቀና መንፈስ ለመራመድ አንቸገርም፣
ለዳንኤል የስኬት ምክንያቶች ለእግዚአብሔር በመቀደስ በጽድቅ ከመኖሩ ጋር በተጨማሪ የእምነት አጋሮችን ማግኘቱ ነው፣ ዛሬም እኛ በአካል ውስጥ እንዳሉ ብልቶች ከእግዚአብሔር በታች አንዳችን ለአንዳችን እናስፈልጋለን፣ በተከፈተው በር ሁሉ በመግባት ህብረት ማድረግ ሳይሆን በእውነት ጌታን ከሚወዱ በጽድቅ መንገድ ከሚሄዱ ከእግዚአብሔር ሰዎች ጋር ህብረት ማድረግ ያስፈልገናል፣ ቃሉም እንደሚያስተምረን በአንድነት ተስማምተን የምንጸልየው ጸሎት በእግዚአብሔር ይሰማል::
ህይወትን የተቀበልነው በነጻ ቢሆንም ይህን ህይወት ለመጠበቅ ግን ዋጋ ያስከፍላል፣ በጥንቃቄ ያልተጠበቀ ህይወት አጥር እንደሌለው ቤት ነው፣ ህይወትን በጥንቃቄ ለመጠበቅ ዕለት ዕለት ስጋችንን እየጎሸምን አይናችንንና ጆሮእችንን ከክፉ በመጠበቅ መንገዳችንን በቃሉና በጸሎት ማንጻት ይኖርብናል፣ በተጨማሪ በአንድ አማኝ በረከት ሌላው አማኝ ሁሉ ስለሚባረክ ለራሳችን ህይወት መጠንቀቅ ማለት ለህብረትም መጠንቀቅ ነው::
ለአንድ አማኝ ትልቅ በረከት በጌታ መገኘት ውስጥ ራሱን ማግኘት ነው፣ እምነት በእግዚአብሐር መገኘት ውስጥ እንድንገኝ ያደርገናል፣ ለቃሉ ታማኝ ስንሆን አንደ ቃልህ ወይም እንደፈቃድህ ይሁን ብለን ስንፈቅድ ለጌታ እንመቻለን፣ የምንኖረው ለህይወት እንጂ ኑሮአችን በህይወታችን ላይ ተፅእኖ እንዲያደርግ መፍቀድ የለብንም፣ የምናስበውን ለእግዚአብሔር ክብር ስናስብና በርሱ መገኘት ውስጥ ስንሆን ኑሮ ላይመቸን ይችላል ህይወት ግን ይመቸናል፣
መንፈስ ቅዱስ በሙላት የሚሰራብን እራሳችንን የሰጠነውንና የተጠማነውን ያህል ነው፣ የሰዎች ቋንቋ የተደበላለቀው ለክፉ ስራ ስለተባበሩ ሲሆን ይህንን የተለያየውን ቋንቋ ወደ አንድነት መንፈስ ለማምጣት ጌታ ለቤተ ክርስቲያን ይህንን የልሳን ስጦታ ሰጠ፣ ይህ ልሳን በእግዚአብሔር ቃል ላይ የተመሰረተ እውነት ለመሆኑ ምስክር አንዲሆን ሰው በሚሰማውና በሚረዳው ቋንቋ ይነገራል፣ አማኝ ከእግዚአብሔር ጋር የሚነጋገርበት የሚስጥር ቋንቋ ነው ደግሞም በሌሎች ሰዎች የሚተረጎምና ራሳችንን የምናንጽበት ነው፣ ይሀን ልሳን ለመቀበል ሰው ወደ እምነት መምጣት አለበት፣
የኋለኛው ቤተ መቅደስ ክርስቶስ ነው ደግሞም ቃሉ እንደሚል የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እኛ አማኞች በደሙ ነጽተን በክርስቶስ እየሱስ ልጆች የሆንን ሁላችን ነን፣ ይህንን ቤተ መቅደስ የሚበልጥ ያደረገው በሰው የተሰራ ሳይሆን አግዚአብሔር የሰራውና ህያው በመሆኑ ነው፣ ይህ ህያው ጌታ በመንፈሱ ለእርሱ በተሰጡ አማኞች ውስጥ ይኖራል፣ ከውጪ ሳይሆን በውስጥ ሆኖ ልጆቹን ይመራል፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ያለግዜው የአለም ብርሃን መሆን ካልተቻለ እንዴት ነው የአለም ብርሃን መሆን የሚቻለው? 2. የእምነት ሰው ልንሆን እንችላለን ነገር ግን ከጌታ ሀሳን ልንጎድል እንዴት ነው የምንችለው? 3. አዳም ለሰራው ሀጢአት ምህረት አግኝቷል ነገር ግን ይሁዳ ምህረት ያላገኘው ለምንድን ነው? 4. በምድር ላይ እያለ የጌታ የሆነ ሰው አድጎ ይጨርሳል ወይ? 5. የምንሰማውን የእግዚአብሔር ቃል ለመያዝ ማድረግ ያለብን ምንድን ነው? 6. እድገት የማይቆም ከሆነ ባላደግንበት ስህተት አለ ማለት ነው? ስህተት ካለ እንዴት ነው ሚዛናዊ ህይወት ሊኖረን የሚችለው?
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ህይወቱን የማይጠብቅ ሰው አጥር እንደሌለው ነው። የሚጠበቅበት ቃሉና ጸሎት ነው የሚለውን ሀሳብ ግልፅ ብታደርገው። 2. ጠንቃቃ ሰው ለመንፈሳዊ ህይወቱም ጠንቃቃ ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 3. አንድነት ከሌለ መንፈሱ አያልፍም የሚለውን አብራራልን። 4. ለክርስቶስ ለመታዘዝ አህምሮን ሁሉ እንማርካለን የሚለው ምን ማለት ነው? 5. ስንፍናም ትጋትም ማንነት ነው የሚለውን አብራራልን። 6. አንድ አማኝ ሁለት ማንነት ሊኖረው ይችላል የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
የሰው ንጽሀናው ራሱን በእግዚአብሔር ላይ የጣለውን ያህል ነው፣ የትኛውም አማኝ በአግዚአብሔር ላይ ከተጣለበት በላይ ሃይልም አቅምም የለውም፣ በችሎቱ የበረታ የማንንም እርዳት የማይፈልገው ጌታ በራሳችን ማስተዋል መደገፋችን አያስደስተውም፣ እግዚአብሔር አቅም የሚሆንን ከራሳችን አቅም ሰንወጣና በእርሱ ሀይል ችሎት የበረታን ስንሆን ነው፣ ስልዚህ ከራሳችን ብርታትና ማንነት ወጥተን በጌታ ታምነንና በጸጋው ተደግፈን ልንኖር ያስፈልገናል፣
የነቢያትና አስተማሪ የመሆን ጸጋ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ስጦት ሲሆን ጥሪውም የሚመጣው ከጌታ ነው፣ እግዚአብሔር አንድን ሰው ለዚህ ስራ ሲጠራ ጸጋውን የሚሰጠው በወሰነው ስፍራና ጊዜ ለፈቀደው ሰው ነው፣ እንዱ የሐሰተኞች ነቢያትና አስተማሪዎች መለያ በጥሪ ሳይሆን እራሳችውን ነቢያትና አስተማሪዎችዎች ብለው መሾም ሲሆን በዚህ ትምህርት ውስጥ ሌሎች ባህሪያችውንና የሚጠብቃችውን ፍርድ እንማራለን፣
እግዚአብሔር ላይ የታመነ ሰው ራሱን የጣለ ነው፣ እግዚአብሔርን በታመንነው መጠን ነው የአርሱ ማንነት በእኛ የሚገለጠው፣ እግዚአብሔርን ከመታመን ጋር አብረን ልናስኬድ የምንሞክራቸው የራሳችን የችግር መወጣጫ ዘዴና መላዎች መፍትሔ ሳይሆኑ ለጠላት መግቢያ ቀዳዳዎች ናቸው፣ የራሳችን ብልሃት ሁልጊዜ አደጋ ነው እንፈተንበታለን ደግመን ደግመን እንወድቅበታለን፣
ሰው ዛሬ ብዙ ነገር ከቤተሰቡ ሊወርስ ይችላል ግን ያ ሁሉ ያልፋል፣ የማያልፍ ዘለአለማዊ መንግስትና ሁሉን የሚገዛ የእግዚአብሔር መንግስት ነው፣ ይህ መንግስት ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጆች ለሆኑ ለቅዱሳን ሁሉ ተሰጥቷል፣ ይህንን መንግስት በትጋት ስንጠብቅ ለሚገጥሙን ችግሮች የምልፍበትን ጸጋ ከጌታ ብንቀበልም ክዚህ ዘለአለማዊ መንግስት ሊያጎድሉን ከሚችሉ ነገሮች ልንጠበቅ ይገባናል፣ እነዚህም መዳናችንን ቸል ማለት፣ የማይምን ክፉ ልብ፣ ክሕደት፣ ወደን የሐጢያት ባሪይ መሆንና ለጊዜው በሐጢያት የሚገኝ ደስታ ናቸው፣
ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፣ የእርሱ ልጆች ለመሆንና ለጽድቅ ለመኖር ከወሰንበት ቀን ጀምሮ እኛን ወደኋላ የሚስብ የሚያዘናጋና ከእግዚአብሔር ክብር እንድንጎል የሚተጋ መንግስት እንዳለ በማወቅ መንፈሳዊ ውጊያ ሁልጊዜ እንዳለ ልንረዳና የጦርነቱን አቅጣጫ ልናውቅ ይገባናል፣ ስለዚህም አንደ ትጉ ወታደር መዘናጋትን ከኛ አስወግደን ሁልጊዜ ቃሉን ታጥቀን ለጽድቅ ነቅተን እንኑር፣
እግዚአብሔር እጅ ትንሽ የምትመስል ግን ትልቁ የእግዚአብሔር በር ናት፣ የእግዚአብሔር አብሮነት በኛ የሚገለጠው ከአንድ ነገር ወደ ሌላ የምንሸጋገረው አቅጣጫችንንና እይታችንን የምትቀይረው በተዘጋ በር አዲስ ምዕራፍ የምትከፍተውና መከናወንን የምትሰጠው የእግዚአብሔር እጅ ስትመጣ ነው፣ ይህቺን የእግዚአብሔርን እጅ ከመቼውም በላይ በጸሎት በእግዚአብሔር በመታመንና ሰው ባለው ሳይሆን እግዚአብሔር ባለው መንገድ እየተራመድን በትጋት ልንሻት ይገባናል፣
ሰው ባልነቃበት እግዚአብሔር አያልፍም፣እግዚአብሔር ለጽድቅ የሚያነቃቃን ከአመፅ ነፃ ስንሆንና ከራሳችን ፈቃድ ወጥተን ለእግዚአብሔር ፈቃድ እራሳችንን ስናስገዛ ነው፣ እግዚአብሔርን መፈለግ አንዱ የመነቃቃት ምልክት ሲሆን ይህ በትጋት የፈለግነው ቃል በመንፈስ ቅዱስ ለጽድቅ ለቅድስናና እግዚአብሔርን በመፍራት እንድንነቃ ያደርገናል፣ ፍሬያማም የምንሆነው ለህይወት የነቃነውን ያህል ነው፣ በመንፈሳዊ ማንነት ስንመላለስ ስጋን እንንቀዋለን ሃጢያትንም እንጠየፈዋለን፣
Play Episode Listen Later Sep 23, 2021 36:24
ትልቁ እምላካችንና አባታችን እየሱስ ክርስቶስ እንኳን መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ነው ተአምራትን ማድረግ የጀመረው፣ እኛም ይህንን መንፈስ ዕለት ዕለት መሞላት ያስፈልገናል፣ በዚህ መንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር ስንሆን በመንፈስ መመላለስ እንጀምራለን፣ በእምነት በጽድቅና በቅድስና እንድንኖር ያግዘናል፣ ለአካሉም የምንመች እንሆናለን፣ በደልን የማንቆጥር ደግና ሩህሩህ ስለሚያደርገን ለአካሉም የምንመች እንሆናለን::
ጌታ ሲጠራን በምንም እንዳንጨነቅ ነው፣ ምክኒያቱም እርሱ የሚያስፈልገንን ሁሉ ስለሚያውቅና በጊዜው የሚያስፈልገንን ሁሉ ስልሚያደርግልን ነው፣ የተጠራነው የመንግስቱ ሚስጥር ተገልጦልን የመንግስቱ ወራሾች ለመሆን ነውና ይሄ ሚስጥር ገብቶን አንዳች ነገር ሳይስፈራን የምንከተለውን አውቀን መንግስቱን በትጋትና በጽድቅ መጠበቅ አለብን::
በእግዚአብሔር ፊት የሚታይ ማንነት ሲኖረን ጌታ ከማንኛውም ክፉ ነገር ይታደገናል፣ ጸሎታችንም የሚሰማው በእግዚአብሔር ስንታይ ነው፣ በእግዚአብሔር ፊት የሚታይ ማንነት እንዲኖረን ቅንነትና እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ለቃሉ የምንታዘዝ መሆን አለብን፣ ያለ ቅንነት በእግዚአብሔር ፊት የሚታይ ማንነት የለንም፣ ዛሬ ከብዙዎቻችን ቅንነት ጠፍቶ እንኳን አንገነዘበውም፣ ግን ሲጎድልብን እናያለን፣ ነገሮች ሲከብዱብን ጸሎታችን አልሰማ ሲል መውደድ ሲያቅተን መራራትና ምህረት ማድረግ ሲያቅተን፣ ይህን ሁሉ በዘመናችን እያየን ስለሆነ፣ ከመቼውም በበለጠ በፊቱ ሞገስ የምናገኝበትን ጸጋ መለመን አለብን፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በዚህ ዘመን አንድ አማኝ ሀጢያትን ሀጢያት ለማለት ምንድን ነው ማድረግ ያለበት? 2. ፀሎታችን ወደ እግዚአብሔር ሀሳብ መለወጥ የለበትም ወይ? እንዴት ነው ወደዚህ ሀሳብ ማዘንበል የምንችለው? 3. በፀሎት መቆየት ማለት በአካል መቆየት ማለት ነው? ስንጸልይ ብዙ የጸሎት ርዕሶች ይመጣልናልና ይህን ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? 4. አንዳንዴ ነገር የሚከብደን ጸልየን በትዕግስት ስለምንጠብቅ ነው የሚሆንብን? 5. ሰው ሊያምን ግን ላይጸልይ ወይም ሊጸልይ ግን ላያምን ይችላል ወይ? 6. ደጋግመን ከመጸለይ ወደ እግዚአብሔር ሀሳብ መግባት የምንችለው እንዴት ነው?
ክርስትና በመናገር ብቻ ሳይሆን በአኗኗር የምናሳየው እምነት ነው፣ እራስን ሙሉ ለሙሉ ለጌት በመስጠት ሲጀምር፣ የሚጠሉንን በመውደድ፣ በእውነተኛ ትሕትና ከራስ ይልቅ ሌሎችን በማስቀደምና እግዚአብሔርን በጊዜውም ያለጊዜውም በማምለክ እንደሚገለጡ ይህ መልዕክት በሰፊው ያስተምረናል፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. አንድ ክርስትያን ድግምት ቢደገምበት በሽታ ላይ ሊወድቅ ይችላል ወይ? 2. አንድ ክርስትያን የጸሎት ህይወቱ ደካማ ከሆነ እንዴት ነው ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኘው?
Play Episode Listen Later Sep 28, 2021 33:20
እግዚአብሔር ብቻውን ሁሉን ሊያደርግ የሚችል አምላክ ስለሆን እርሱ አሻግራለሁ ካለ ለማሻገር የማናችንንም ድጋፍ አይፈልግም፣ በህይወት ማዕበልና ወጀብ ብዛት እምነታችን እየተፈተነ ሊሆን ይችላል ግን በድካማችንም ቢሆን ወደ እርሱ ስንጮህ ነፋሳት ማዕበሉና ውጀቡ ለቃሉ የሚታዘዙለት ጌታ ማዕበልና ወጀቡን ጸጥ ያደርገዋል፣ የጠራን አምላክ የሚያደርስ እንጂ መንገድ ላይ የሚተው እባት ስላልሆነ እርሱ ከያዘን በምንም አይነት ማዕበል ውስጥ ካለመናወጥ እናልፋለን፣ እምነታችንን በእርሱ ላይ ካደረግን ደግሞ ምንም የሚጥለን ነገር አይኖርም፣
እምነት በሌለበት ጥርጣሬና ፍርሃት አለ፣ አማኝ በእምነት እንጂ በማየት ስለማይመላለስ እግዚአብሔር ታማኝና በስሙ የተጠሩትን ለመጠበቅ የሚተጋ አምላክ መሆኑን በመረዳት እኛም ለተቀበልነው የህይወት አደራ ጸንተን መጋደል አለብን፣ አንዱ የመንፈድሳዊ መዋጊያ መሳሪይችን የጽድቅ ጥሩር ሲሆን ከእኛ የሆን ምንም ጽድቅ እንደሌለን ደግሞ መረዳት አለብን፣ ሰይጣን በሚከሰን በማንኛውም ሁኔታ ልናሸንፈው የምንችለው በክርስቶስ እየሱስ ጽድቅ ስንገለጥ ነው፣
አለም ስጋና ሰይጣን አንዱ የመዋጊያ መንገዳቸው እኛን ከቅንነታችን እንድንጎድል ማድረግ ነው፣ ቅንነት ሲጎድለን በሰማነው መቆም ያቅተናል፣ እግዚአብሔር ጻድቅና በስራው ፍጹም የማይሳሳት አምላክ ስለሆን ቅን ለመሆን በገባንም ባልገባንም ነገር ከእግዚአብሔር ጋር መስማማት ነው፣ አንድ አማኝ በቅንነት ለመኖር ሲወስን ብዙ የማይመቹና ተስፋ የሚያስቆርጡ ነገሮች ይኖራሉ ሆኖም ግን ለአማኞች የተመረጠልን መንገድ ይህ ነው፣
ከጸሎት መራቅ ማለት ከእግዚአብሔር መራቅ ማለት ነው፣ እምነታችን በእግዚአብሔር ላይ ሲሆን በጸሎትም እየበረታን እንሄዳለን፣ ለብዙዎች እግዚአብሔርን ለሚያውቁ ሰዎች የህይወት ክንዋኔ አንደኛው መክኒያት ከእግዚአብሔር ጋር ግኑኝነትን ማድረግ ሲሆን የእግዚአብሔርን ጉብኝት እስኪመጣ ድረስ በጸሎት መትጋታቸው ነው፣ ዛሬም እኛ አማኞች ሃይልን ለመቀበለና የእግዚአብሔርም ጥሪ እንዲበራልን በጸሎት ልንተጋ ያስፈልገናል
ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ሲሞላ ፈሪ የነበሩ እንኳን በልዩ ብርታትና ሀይል ይቆማሉ፣ የተጠራነው ምስክር እንድንሆን ነውና በድፍረት ክርስቶስን ይመሰክራሉ፣ ደግሞም በልሳን ሲጸልዩ ሌሎች ሰዎች ይሰሟቸዋል፣ በሰላም የተሞሉ ናቸው፣ ሌሎች ሰምተው እንኪደነቁ የሚያመሰግኑ ደግሞ ናቸው፣
መንፈሳዊ ዕድገት ያለው በመቆየት ውስጥ ነው፣ እግዚአብሔር የሚያደርገውን ሁሉ ከክብሩ አኳያ ስለሚያደርግ ለአንዳንድ መልሶች ጌታ ለጥቅማችን ያቆየናል፣ ዘግይቶ የሚመጣበት ምክኒያት የመሸከም አቅም እንዲኖረን ነው፣ ደህንነታችንን የመያዝ አቅም በሚኖረን ጊዜ ሁሉን በጊዜው ያደርጋል፣ እኛም እግዚአብሔርን እንደ እግዚአብሔርለቱ ማክበር የምንችለው በቆየንበት ነው፣
እግዚአብሔርን ስንጠብቅ ኪስራ የለም። አለመጠበቅ ግን አመጽ ነው። እርሱን ጠብቆ ማፈር የለም።እግዚአብሔርን ከሁኔታ፣ ከእድሜ፣ከእድልፈንታ ጋር ሳናስተያይ ብንጠብቅ እንጠቀማለን።የምንጥብቅበትን ጸጋ አየሰጠ፣ አይዞህ አይዞሽ እያለ ወደ ጠበቅንበት መልሳችን ያደርሰናል።
እኛ የተጠራነው ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሀንን ሲሆን ለሌሎች እንድናበራና ሌሎች ለእግዚአብሔር ምስጋናን እንዲያቀርቡ ነው፣ የተጠራንበት ጥሪ የልጅነት ጥሪ ነው ደግሞም በሰውና በእግዚአብሔር መሀል ገብተን ለማስታረቅ ካህን ለመሆን ነው፣ እንግዲህ የተጠራነው እንደወደድን እንድንኖር ሳይሆን በብርሃን እንዳሉ በእግዚእብሔር እንደተወደዱ ልጆች ዕለት ዕለት እግዚአብሔርን ለመከተልና ለቃሉ ክብርን እየሰጠን ሳንፈራ ለክህነት ስራችን እንድንተጋ ነው፣
እግዚአብሔርን ብቁ ማድረግ ማለት ሁሉን ከእርሱ መጠበቅ ማለት ነው፣ አግዚአብሔርን የተጠጋ ሰው ብቁ ነው ብቃቱ የራሱ ሳይሆን አግዚአብሔር ራሱ ስለሆነ ነው፣ አንዳንድ ጊዜ ጌታን እየተከተልን በፈቃዳችን እርሱን በቂ ሳናደርግ ስንቀር በጎደለን ነገር እንጋለጣለን፣ የእውነትና የጽድቅ ጌታ እንዲሁም ለሁሉ በቂ ለሆነው አምላክ የነቀፌታ ምክኒያቶች እንሆናለን
የእግዚአብሔር ቃል የፀና ነው። በዚህ ትምህርት ውስጥ የቃሉን ወተት ሁልጊዜ ልንጠጣና፣ ልናድግ እንድሚገባን እንማራለን። ጴጥሮስ ወደ ጌታ መሄጃው ጊዜ እንደደረሰ አውቆ አምኞችን በእግዚአብሔር ቃል እንዲተከሉና እንዲያድጉ እየመከራቸውና እያሳሰባቸው፣ የእግዜብሔር ቃል ከየትኛውም ትንቢት የፀና እንደሆነ ይነግራቸዋል። ለእኛም በዚህ ብዙ አይነት የስህተት ትንቢትና ትምህርት በበዛት ዘመን ላለን የሚመክረንና የሚያሳስበን ይህንኑ ነው።
የእግዚአብሔር ሕዝብ የተሰጠው የክህነት አገልግሎት ስለሆነ የህዝብን ህጥያት ለብሶ በእግዚአብሔር ፊት ይጮሃል። በዚህ ትምህርት ውስጥ የብሉይ ኪዳን አገልጋዮች፣ ሙሴ፣ኤርሚያስ እንዴት ለህዝብ እንደማለዱ እንዲሁም ክርስቶስ በአዲስ ኪዳን እንዴት ባለ ብርቱ ጩሀት ምህረትን ፣ ፈውስን እና ይቅርታን ከአባቱ ዘንድ እንዳስገኘን በስፊው እንማራለን።
ጾምን አወጅን ስንል በመጀመሪያ ከክፉ ሀሳባችንና መንገዳችን በእውነተኛ ንሰሃ መመለስ ፤ ከምግብና ከሚጠጣ ብቻ ሳይሆን ከሚያዝናኑ ነገሮች ጭምት ሆነን በሁለንተናችን በእግዚአብሔር ፊት ራሳችንን በማዋረድ ፤ የምንፈልገው አንተንና ከአንተ ብቻ ነው በማለት አለመቻላችንን አውቀን ፤ እውቅናን ለልኡል እግዚአብሔር በመስጠት ትችላለህ እያልን ከእርሱ ብቻ ለመስማት ራሳችንን በፊቱ ማዋረዳችን ነው
በላይ ከፍ ያለውን የእግዚአብሔርን የመጥራቱን ሃሳብ ለመያዝ ስንገሰግስ አሉ የሚባሉ ችግሮች ሁሉ የምናልፋቸው ናቸው፤ ነገር ግን ወደዛ የማንገሰግስ ከሆነ እነዛ ችግሮች የሚያልፉ አይመስለንም፤ ይህም መከራ ያልፋል ማለት የምንችለው ከፍ ያለውን የእግዚአብሔርን ሃሳብ ማየት ስንችል ነው
ጌታን የምናገኘው በተውነው ልክ ነው፣ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ አምላክ ሆኖ ሳለ ከእግዚአብሔር ጋራ መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቆጥረውም፣ እራሱን ዝቅ ባደረገ ክብሩን በተወው ልክ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፣ ሙሴም ካደገ በኃላ ባደገበት ቤት ያደገበት ነገር ሳይሆን የወረሰው የተወለደበት አላማ ነው፣ ዛሬም እኛ በሰማነው ልክ ሳይሆን ስለ ክርስቶስ በተውነው ልክ የእግዚአብሔር ክብር በኛ ይገለጣል ደግሞም በተውነው ልክ ብድራት ይከፈለናል
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 29፣ 24 ከሰዎች ሁሉ የራሳችን ያልሆነውን ለመቀበል መጠንቀቅ አለብን ወይ? 2. ምሳሌ 29፤25 ሰውን ማክበር እና መፍራት ልዩነቱ ምንድን ነው? 3. ሮሜ 15፤3 ዕብራውያን 3፤16 ክርስቶስን ወደ መምሰል መምጣት የምንችለው እንዴት ነው? 4. ሰዎች ያደረጉትን መልካም ነገር ስንለወጥ እንዴት ነው በህይወታችን ማለፍ የምንችለው? 5. እንዴት ነው በህይወታችን የእግዚአብሔር ቃል የሚመራን? 6. ሰው ራሱን ለበግዛት በመንፈስ ቅዱስ መሞላት አለበት ወይ? 7. የማያምን የትዳር ጓደኛ ቢኖረኝ የሚያደርገው ነገር ከህይወቴ ጋር ይደባለቃል ወይ? 8. በመንፈሳዊ ህይወት ማሸነፍ ያለው ከመሸነፍ ህይወት ውስጥ ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 9. ምሳሌ 29፤20 ችኩል ሰው መንገሳዊ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
አይንን የፈጠር አምላክ ያያል በጨነቀን ግዜ ያያል፡ እግዜአብሔር ፍርድን አደላዳይ የሚያይ አምላክ ነው፤ እግዚአብሔር ያያል የሚለው እውቀትና መገለጥ በጥንቃቄ እንድንመላለስ፥ በጨነቀን ጊዜ አጉረምራሚ እንዳንሆን፥ ውለታውን እንዳንረሳ፥ እግዚአብሔርን እንዳንከስ፥ ባልተመቸ ቀን ያስጥለናል እንድንቆም ያድርገናል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 29፣24 የእኛ ያልሆነውን ነገር መውሰድ ሌብነው ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. ለአገልጋዮች ማድረግ ያለብን በጎ አድራጎት ምን ድረስ ነው? 3. ወደ ፊት እንዳንሄድ ህይወታችንን የያዚ ነገሮች አሉ ስለዚህ ብዙዎች ያላመለጡ ክነገሮች ጋር ያልተፋቱ ብዙዎች ናቸው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. ምሳሌ 29፣27 ሰዎች መልካም ሲያወሩልን እንጠንቀቅ የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. ጸጋን መቅመስና ተቀባይ መሆን የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 6. ያነበብነው ቃሉን መያዝ ካልቻልን እንዴት ነው ትንቢትን በቃሉ መመርመር የምንችለው? 7. ከሌላ ቤተ ክርስትያን መጥተው ትንቢትን ሲናገሩ ሀሰት መሆኑን እንዴት ነው የምናውቀው?
እግዚአብሔር ካልቀ ከተቆረጠ ምን እንሆናለን ካልንበት ነገር ውስጥ አዲስ ምዕርፍ አለው፤ በምናልፍበት ችግር ነው በምንለው ውስጥ እግዚአብሔር አለ እርሱ የሌለበት ችግር አልፈን አናውቅም፤ በሰው ልብ የሌለ በሰው ሃሳብ ውስጥ ያልታሰበ ነገር ግን ሁልጊዜ ባለቀ ነገራችን የሚያደርገውን የሚያውቅ የሰራዊት ጌታ ድንቅ ሠሪው በመካከላችን ከእኛ ጋር አለ፤ የእኛ ነገር ያለቀው እየሱስ ባለበት ነው። ዮሐንስ - 2:1-10
ከተቀበልነው ጸጋ አንዱ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፣እግዚአብሔርን መፍራታችን የመቀደሳችን ምልክት ነው፣ አካሄዳችን የተስተካከለ መሆኑ የሚታወቀው ቃሉን ከመዳፈርና መንፈሱን ከማቃለል ወጥተን ጌታን ስንፈራ ነው፣ እግዚአብሔርን እያወቅን ባደግን ቁጥር የእግዚአብሔር ፍርሃት በህይወታችን እየጨመረ ይሄዳል የሚያስፈራንና የሚይስደነግጠንም እርሱ ብቻ ይሆናል፣ ፣ አይምሮአችን በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር ካልሆነ ግን ሌላው ቅዱስ ያልሆነው ፍርሃት አይምሮአችንን ይቆጣጠረዋል በዚህ አይነቱ ፍርሃት ውስጥ ስንሆን ደግሞ እግዚአብሔር የተናገረንን በጎ ነገር ሁሉ ከጃችን ያስጥለናል እግዚአብሔርንም የመስማት አቅም እንዳይኖረን ያደርጋል፣
ጌታ ይቅር እንዳለን የበደሉንን ሁሉ ይቅር ማለት አለብን። በዚህ ክፍል ውስጥ የምንማርው ቂምና ጥላቻ ካለብን የእኛም ሀጥያት ይቅር እንድማይባልና ፀሎታችንም እንደማይመላስ ነው። ይህም ደግሞ ደስታችንን አና በረከታችንን ይይዛል። ስለዚህ ሁልጊዜ እራሳችንን እየመረመርን ከእንደዚህ እይነት ሀጥያት ልንመለስ ይገባል። ይቅር ማድረግ ፣ሰውን ሁሉ መውደድ ጌታን ደስ ማሰኘት ይገባናል።
ከእግዚአብሔርና ከቅዱሳን ጋር ያለን ህብረት ጤናማ እንዲሆን ያስፈልገናል። በዚህ ክፍል የምንማረው ለዚህ ጤናማ ህብረት የሚያስፈልጉንን ነገሮች እና እደራረጉን ነው።ይህም፣አለምዊ ምኞትን፣ የስጋ ምኞትን የአይን አምሮትን እና ስለ ገንዘብ መመካትን ማስወገድ ነው። ይህንን ስናደርግ ህብረታችንን በሁሉም አቅጣጫ ጤናማ ይሆናል።
እረፍት ኢየሱስ ነው:: ለእረፍት ተጠርተናል: እረፍት ከመዳናችን ጋር የተያያዘ ነው እንጂ ከሁኔታዎች መለዋወጥ ጋር የተያያዘ አይደለም:: እረፍት ውስጥ አለን ማለት ልባችን አይምሮአችን ሀሰባችን በክርስቶስ የተጠበቀ ነው ማለት ነው:: ማሳረፍ የእግዚአብሔር ባሃሪ ነው: እኛ ራሳችንን ማሳረፍ አንችልም::
እግዚአብሔር ባለበት በለቅሶ ሸለቆ ስፍራ በረከት በዚያ አለ፤፤ ኢዮሳፍጥ እግዚአብሔርን ሰምቶ አምኖአልና መከራውን ወደ ክብር ሸለቆ ለወጠለት፤፤ ዳዊት እግዚአብሔርን ታምኖአልና የስብራቱን ቀን ወደ በረከት ቀየረለት፤፤ ያቤጽም ጸልዪአልና እግዚአብሔር የመርገም ታሪኩን ወደክብር ቀየረለት፤፤ እግዚአብሔር ስለወደደን እርግማናችንን ወደበረከት ቀየረልን፤፤
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 29፡20 የሚቸኩል ሰው መንፈሳዊ ፍሬ ሊያፈራ አይችልም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. ምሳሌ 30፡1-5 በዚህ ዘመን ብዙዎቻችን ጌታን እናመልከዋለን እንጂ እናምነውም የሚለውን ሀሳብ ግልፅ አድርግልን። 3. መዝሙር 23፡24 ነገሬን ከሰው ጋር የማያይዝ ከሆነ በመንፈሳዊ ነገሬ እያደኩ አይደለም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. ክፉ ነገር ሁሉ ከሰይጣን አይደለም ወይ የሚመጣው? ታድያ እንዴት ነው ነገሬን ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር የማያይዘው? 5. እቅድ አውጥተን ባናደርገው እንደ ስለት ሊቆጠር ይችላል? 6. 1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡1-5 ኤጴስ ቆጶስ መሆን የሚፈልግ ህይወቱ ምን ዐይነት መሆን እንዳለበት ተገልጣል ግን አሁን ያለች ቤተ ክርስትያን ይህንን አትጠቀምም እንዴት ነው? 7. ራዕይ 22፡17 በዚህ ዘመን ለምንድን ነው አማኞች ማራናታ ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና የማይሉት?
እግዚአብሔር ብቻውን አምላክ እንደሆነና እውነተኛ አምላክ መሆኑ እንዲታወቅ ስለሚፈልግ ክብሩን በተለያዩ ስዎች ገልጧል፣ ዮሴፍም ከነዚህ ስዎች መካከል አንዱ ሲሆን ዛሬም እግዚአብሔር እንደ ዮሴፍ ራዕይን የተሸከሙ ሰዎች አሉት፣ ይህንን ራዕይ የተሸከሙ ሰዎች በተለያየ እንቆቅልሽ ውስጥ ያልፋሉ፣ ጌታ ስሙን ለማስከበር አንዳንዴ የራሱ የሆኑትን እንደንዚህ አይነት ሰዎችን በመከራ እንዲያልፉ ይፈቅዳል ግን በመከራቸው ክብሩ ይገለጣል፣
ዳዊትና ሌሎችም በመጽሀፍ ቅዱሳችን ውስጥ ብዙ የእግዚአብሔር ሰዎች በጭንቅ በመከራና በማይወጡበ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ግን እግዚአብሔርን በመታመን እንዴት ከነበሩበት ያለቀና የተቆረጠ ነገር ውስጥ ጌታ ደርሶ እንደታደጋቸው ተጠቅሷል፣ ዛሬም እኛ የክርስቶስ ተከታዮች የምንሰማውና የምናየው ደስ ባያሰኝ የታመንነው ቢከዳን ዙሪያችን በሚሆነው ሳንወሰድ ባለመታወክ ጸንተን ጌታን መጠበቅና ልባችንን ጌታ ፊት ማፍሰስ ይገባናል ምክኒያቱም ረድኤታችንና መታመኛችን እርሱ እግዚእብሔር ብቻ በመሆኑ፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. 1ኛ ቆሮንቶስ 14፡34-37 የሴቶችን አገግሎት በተመለከተ ይህ ክፍል እንዴት ነው የሚገለጠው? 2. ኤፌሶን 6፡18 “ በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ” ይህ ክፍል ይብራራልን። 3. ምሳሌ 29፡25 ሰውን በመፍራት እና በማክበር ያለው ልዩነት ምንድን ነው? 4. ሰው በሚያልፍበት ነገር ማንነቱ ይገለጣል የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. በምንሰማውና በምናየው ነገር ስንፈራ እንገኛለን ያ ማለት የእግዚአብሔር ፍርሀት የለንም ማለት ነው? 6. ኢዮብ 23፡10 የአማኝ እረፍቱ እሱ ያውቃል ማለቱ ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 7. 1ኛ ዮሐንስ 3፡21-24 የተጨበጠ መረዳት ከሌለን ስንቆሽሽ አናውቀውም ስለዚህ የእምነታችን መለኪያ ስሜታችን ነው የሚሆነው የሚለውን ሀሳብ ግልፅ አድርግልን። 8. 2ኛ ቆሮንቶስ 12፡8 ለችግሮቻችን አጥብቀን እንፀልያለን እንጂ እግዚአብሔርን ለመስማት ብቁ አይደለንም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
በእግዚአብሔር መንገድ ላይ ስንሆን፣ እርሱ እኛን በሚያገኝበት እኛም ለእርሱ በምንገኝበት ያደርገናል።በመንገዱ ስንሆን በምንም አንታለፍም።ከእኛ ያልሆነ ጥንካሬና ጉልበት ይሰጠናል።በመንገዱ ላይ መሆን ማለት በጉብኝት ቀናችን ላይ መሆን ማለት ነው።የመዳን ቀን ማለት እርሱ በሚያልፍበት ቀን የተገኝንበት ቀን ነው። በዚህ ትምህርት ውስጥ ይህንን በጥልቀት ያስተምረናል።
በጊዚያዊ መከራዎች ውስጥ ስናልፍ መታከት የለብንም። ምንም የውጭው ሰውነታችን በብዙ መከራ ቢጎዳ የውስጥ ሰውንታችን ግን ዕለት ዕለት ይታደሳል። በዚህ ክፍል ውስጥ በህይወታችን እንዳንታክትና ክርስቶስ በህይውታችን እንዲገለጥ ምን መሆን እንዳለብን በሰፊው ያስተምረናል።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በመንፈሳዊ ነገር ያደገ ሰው ያለውን ነገር ሙሉ በሙሉ ለጌታ የሰጠ ሰው አንዳንዴ ወጣ ገባ ሊል ይችላል ወይ? 2. በመንፈስ ካልታመንኩ ሰው የነገረኝን ሚስጥር መሰወር አልችልም ወይ? 3. የራስ ሸክም መንፈስ ቅዱስ ከሚሰጠው ሸክም ምንድን ነው ልዩነቱ? 4. ያደገ ሰው የእግዚአብሔር እውነት የእርሱ የሆነ ሰው ነው። የእኔ የእድገት ደረጃ እውነት ከሆነልኝ ነገር ነው የሚወሰነው ማለት ነው? ይህስ መረዳት ስለ ጌታ መረዳት ነው ወይ? በህይወቴ በሚሆነው መረዳት ይቻላል ወይ? 5. ወላጆች ሳይሆኑ ልጆችን የሚየሳድጉትን ምን ማድረግ እንዳለብን ብትመክረን?
የክርስትና ህይወት የውትድርና ህይወት ነው፣ ሁልጊዜ እራሳችንን በፊቱ እየመረመርን መንገዳችንን ልናነጻ ይጠበቅብናል፣ በንጽህናና በቅድስና ለመኖር ስንወስን ደግሞ ፈተና የለብንም ማለት ሳይሆን ነገር ግን እኛ ሃጢያተኛ እንደሆንን እና እርሱ ጌታ ብቻ ጻድቅ እንደሆነ በማመን በሙላት ህይወታችንን እንዲመራ ስንፈቅድለት ምድራዊው ፈተና በፊታችን እነደ ትቢይ ይሆናል፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. 1ኛ ሳሙኤል 9፡7 ሳዖል አህይ ፍለጋ ወጥቶ እግዚአብሔር በሚገኝበት ሥፍራ እንዲገኝ አድርጎታል ይህ መንፈስ ቅዱስ በሚመራበት ወቅት በህይወታችን ሊከናወን ይችላል? 2. የተለየን ቀን ልንስተው እንችላለን ወይ? ከሳትንስ ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? 3. ችግር ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ማቅረቢይ ነው? 4. በዚህ ዘመን በልጆቻችን ላይ ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? 5. ደካማ ሰው ሁልግዜ ተበቃይ ነው ጥበበኛ ሰው ግን ነገሩን ይንቃል በዚህ ውስጥ የበቀል ምኞት፣ የበቀል ጸሎት አለ የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 6. ትጋትና ኑሮዬ ይበቃኛል ማለት እንዴት ነው ወደ ህይወታችን ማምጣት የምንችለው? 7. 2ኛ ተሰሎንቄ 3፡3 “ነገር ግን የሚያጸናችሁ ከክፉም የሚጠብቃችሁ ጌታ የታመነ ነው።” የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
እግዚአብሔር ቀናተኛ አምላክ ነው በሙሉ ሀይላችን እርሱን ስንታመን ደስ ይለዋል ምንም የለኝም አንተ አለኃኝ እሚያየኝ የለም አንተ ታየኛለህ የሚሰማኝ የለም አንተ ግን ትሰማኛለህ እንድንለው ይወዳል፤፤ አይኖቻችን በእግዚአብሔር ላይ ብቻ ሲሆኑ እግሮቻችን ለመናወጥ አይሰጡም
ጌታ ኢየሱስ የሰጠን ሰላም የማይናወጥ አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ ሀሳባችንን የሚጠብቅ ሰላም ነው፤፤ አእምሮአችንን የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ በማሰላሰል እለት እለት ማስለመድ አለብን
ሁሉን ለጌታ የሚተው ትግስተኛ ሰው ነው፣ የመታገስ አቅም ያለው ሰው ነገርን ሁሉ ለጌታ የተወ ነው፣ ሰው እንደመሆናችን ነገርን መለወጥም ሆን መሸከም እንደማንችል በመረዳት ለመንፈስ ቅዱስ እውቅናን በመስጠት ፈቃዳችንን ለጌታ ስናስገዛና አለን የምንለው ጌታ ብቻ ሲሆን ነገራችንን ለጌታ ለመተው ብዙ አንቸገርም፣
አማኝ እግዚአብሔርን ሲከተል መስቀሉን ሊሸከም ይገባዋል። በዚህ የክርስትና ጉዞ ውስጥ በእምነት እና በደስታ፣ በመጽናት፣ ራስን በመካድ ልንከትለው ያስፈልጋል። በዚህ ትምህርት ውስጥ እንዴት መስቀላችንን ተሸክመን እስከመጨረሻው ጌታን እንደምንከተል እንማራለን።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. በደማቸው እንዲናገሩ የማይሰወሩ ነቢያት አሉ የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። ይህንንስ እንዴት ነው የምናውቀው? 2. ሰውን ይቅር ማለት ፈጽሞ ነገርን መተው ማለት ነው ወይ? 3. እግዚአብሔር በችግር ግዜ አዚሁ ተቀመጡ ቢለል ድምፁን እንዴት ነው የምንለይው? 4. አድርጉልን የምንል ከሆነ አላደግንም ማለት ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. ጠባዬ ነው ብለን የምናደርገውን ነገር እንዴት ነው ማስተካከል የምንችለው? 6. በአላፊነት ያለ ሰው በበቂ ምክንያት ሀላፊነቱን መወጣት እንደማይችል ቢናገር ይህ እድገት ሊሆን ይችላል? 7. በተቸገርን ሰዓት ብቻ ሳይሆን በተሳካልን ግዜ የተከፈተ ዐይን ሊኖረን ይገባል ማለት ነው? 8. እግዚአብሔርን መታዘዝ ማለት መሰወር ማለት ነው?
ዛሬ ምን ሰምታችኃል? ዛሬ የሰማነው ነገር እንዳያወርደን አብዝተን ልንጠነቀቅ ያስፈልገናል፤ የሰማነው ነገር ወደ እግዚአብሔር የማያቀርበን ከሆነ ያለመስማት ይመረጣል፤ ነገራችን ነጋችን በእግዚአብሔር እጅ ነው መራራው ይቀየራል ያስፈራራን ይለወጣል እርሱ ፍጻሚያችን ያውቃል
Play Episode Listen Later Nov 27, 2021 32:49
የአንድ አማኝ ዕድገት ትልቅ ከፍታ እኔ የጌታ ነኝ ማለት መቻሉ ነው፣ የተፈጠርነው የእግዚአብሔር ለመሆን እንደሆነ ሲገባን የመከራና የችግሮች መደራረብ ከክርስቶስ ፍቅር እየነጠሉን ሳይሆን የእርሱ መሆናችንን እያስረገጡልን ነው የሚሄዱት፣ እግዚአብሔርም ከጥንት ከመጀመሪያው የእርሱ ስላደረገን ባለቀቅነው ማንነታችን ወይም የእርሱ ሆንን ባልተገኘንበት የእርሱ ሆነን እስክንገለጥ ወደ እርሱ የሚይስጠጋንን የህይወት ማዕበልና ወጀብ ይፈቅዳል፣
የተስፋን ቃል የሰጠን የታመነ ነው፣ ተስፋን የተቀበልን አማኞች ቃሉን የህይወታችን መመሪያ በማድረግ በምናልፍበት ውጣ ውረድ ሁሉ በዚህ ታማኝ አምላክ መደገፍ ይገባናል፣ በተስፋችን ጸንተን አስከፍጻሜ እንዳንሄድ ከሚያደርጉን ነገሮች አንዱ ፍርሐት ሲሆን፣ እኛ ግን አይምሮአችን ወይም ሁኔታዎችን ሳይሆን ቃሉ የሚለንን በመስማት እና በመቀበል ተስፋ የሰጠን ጌታችን ደግሞ ተመልሶ እንደሚመጣና ወደ ራሱ አንደሚወስደን በማመን በትጋት እስከፍጻሜ መጽናት ይኖርብናል፣
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 30፡32 በዚህ ዘመን መጠየቅ ያለብን ምን በላን ሳይሆን በሰው ህይወት ውስጥ ምን ሠራን መሆን አለበት የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. በህይወታችን ውስጥ ማዕበል ጸጥ የማይለው እንዴት ነው? 3. እየሱስ ክርስቶስ ብቻ ካለን እለት እለት የሚያስፈልገንን ፀጋ ላንቀበል እንችላለን ወይ? 4. በተለያየ ነገር አድገን ጌታን ካልመሰልን እነዚህ ነገሮች በህይወታችን ምን ሊመስሉ ይችላሉ? 5. ያደገ ሰው ሰውን ያስተካልክላል ስለሚል አገልጋዮችን ሳናስቀይም እንዴት ነው ማስተካከል የምንችለው? 6. ቃሉን እንደ ቃል መውሰድ የምንችለው እንዴት ነው?
እውነተኛ ባለጸግነት ያለው በክርስቶስ ውስጥ ነው ይህም የሚገኘው በእምነት ነው፤ በክርስቶስ ውስጥ ያለውን ባለጸግነት ለማግኘት መክሰር የግድ ያስፈልጋል መጣል የግድ ያስፈልጋል፤ በክርስቶስ የተሰጠን ብለጸግነት መጠን የለውም፤ ይህ ጸጋ የሚለቀቀው ግን ስለ ክርስቶስ ስንከስር ነው፤ ለዚህ ምድር የምንጠቅመው አማኝ ስለሆንን አይደለም፡ በክርስቶስ ባለጸግነት ውስጥ ካለን ለዚህ ምድር እናስፈልገዋለን። 2 ቆሮንቶስ 6:10
ሰው እየሱስ ክርስቶስን እንድ ግል መድሀኒቱ እድርጎ ሲቀበል ከኩነኔና ከእር ግማን ነፃ ወጥቶአል። ነገር ግን በህይወት ጉዞ ውስጥ ደግሞ በጌታ ለማደግ የግዚአብሔር ፀጋ ያስፈልገውል።ምክንያቱም ከጌታ በፊት የነበሩንን የሀጥያት ልምምዶች የምንጥለው ፣ ባህርያችን የሚለወጠው ፣ ከእስራታችን የምንፈታው በፀጋው ነው። እንዲሁም በመከራና በአስጨናቂው አለም ውስጥ ስናልፍ የጌታ ሰላም እንጠበቃለን። በዚህ ክፍል ውስጥ ይህንን ብዝርዝር እንማራለን።
ጌታን በጽድቅ እየተከተልን ስንሄድ በህይወታችንበብልዩ ልዩ ፈተና አና መከራ እናልፋለን። በዚህ የህይወት ጉዞ ውስጠ እግዚአብሔር ለምን የሚል ጥያቄ ይፈጠርብናል። በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ እንደተፃፈው፣ ብዙ የእግዚአብሔር ሰዎችም ጠይቀዋል። እግዚአብሔር ዝም ሲል በህይውታችንን ሊከብር እና ለእኛም የበለጠ እና የተሻለን ነገር ስላየልን ነው። በዚህ ትምህርት ውስጥ ይህንን በጥልቀት እንማራለን።
የቤተክርስቲያን ዋና ተልዕኮ የእግዚአብሔርን በጎነት መናገር፣ መንፈሳዊ ቤት ሆኖ መሰራትና መንፈሳዊ መስዋዕትን ማቅረብ ነው፣ ታላቁ ትዕዛዝ ደግሞ አምላካችንን በፍጹም ልባችን ነፍሳችንና ሃሳባችን መውደድና ባልንጀራችንን ደግሞ እንደራሳችን መውደድ ነው፣ ጌታን መውደዳችንን የመንገልጸው ከአላማው ጋር በመተባበርና ለቃሉ በመታዘዝ ሲሆን በምድር ሲያስቀምጠን ትልቁ አላማው ደግሞ ወንጌልን ለፍጥረት ማድረስ ነው፣ ባልንጀራችንን እንደራሳችን እድርገን መውደዳችንን የምንገልፀው ለባልንጀራችን መልካም ነገርን በማድረግ ሲሆን ሰውን ሁሉ ወደ ዘለአለም ህይወት ከመምራት የበለጠ ደግሞ ምንም መልካም ነገር የለም፣ አማኞች ለዚህ ታላቅ ተልዕኮ ሁልጊዜ የተጋን እንድንሆን ጌታ ይርዳን፣
እግዚአብሔር መልካም ስለሆነ ለህዝቡ ለመልካም ቀን ይቀጥራል። እኛ ግን በመታመን መጠበቅ አለብን። እግዚአብሔር ካለን ይልቅ ሁኔታን አይተን መናወጥ የላብንም። እስራኤል እግዚአብሔርን ከመስማት ይልቅ ጠላት የሚላቸውን ይሰሙ ስለነበር በምድረብዳ ቀርተዋል። እኛም ከጥርጠና ፍርሀት ሀሳባችንን መጋረድ እለብን። በዚህ ክፍል ውስጥ ይህንን በስፍት እንማራለን።
የእግዚአብሔር ፈውስ ወደ እኛ የሚመጣውና የሚባርከን ክርስቶስን በምንመስልበት ነው፣ ጸሎት መልካም ነው ግን የምንጸልየው ለፈውስ ብቻ ሳይሆን ወደ ምሪት እንድንደርስ ነው፣ እንዳንዴ እግዚአብሔር እቅጣጫችንን ሲያሳየን በህይወታችን ያስቀደምነው ከርሱ ያስበለጥነውን ነገር ገልጦ ሊያሳየን ይችላል፣ ጌታ ሳይቀድም በረከትን መቀበል ስለማንችል ይህንን ከጌታ ያስበለጥነውን ነገር ካልጣልንና እግዚአብሔር በሰጠን አቅጣጫ ካልተመራን ከፈውሳችንና ከበረከታችን ጋር እንተላለፋለን::
መንፈሳዊ ነገርን በምድራዊ መስፈሪያ መስፈር አንችልም ብዙ ስዎች በመጽሐፍ ቅዱስ በምድራዊ ነገር ለሰው የከሰሩ በመሰሉበት አትርፈው እግዚአብሔርም ከብሮ እስከዛሬ ለብዙዎቻችን መልካም ምሳሌ ሆንውናል፣ የሰማዩን ስኬት የሚያመጣው የምድሩ ኪሳራ ነው፣ የምድሩን ኪሳራና አለመሳካት እንደበረከት አድርገን ካልቆጠርነው የእግዚአብሔር ቸርነትና በጎነት የሚገለጥበትን መንገድ ማየት አንችልም፣ እንዚህ ኪሳራዎች ወደ እግዚአብሔር ሐሳብ የሚያደርሱን ናቸው፣ ለኪሳራችን መወጣጫ በራሳችን መንገድ የምናዘጋጃቸው ዘዴዎች ከኪሳራ ወደ ሌላ ኪሳራ እኛን ከመክተት ሌላ መፍትሔ አይሆኑንም፣ መፍትሔው እግዚአብሔር ያየው እስኪመጣ ድረስ በስፍራችን ሆንን እርሱን መጠበቅ ነው::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. 1ሳሙ 13፡8-9 እግዚአብሔር ተናግሮን በመጠበቅ ፈንታ እርምጃን እንወስዳለን የሚለውን ሀሳብ ግልፅ ብታደርግልን? 2. እግዚአብሔርን መቅደም ማለት የራስን ጸሐይ ማውጣት ነው ይህ ደግሞ አይቻልም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 3. ምሳ 28፡8 በሥራ ቦታ አድሎ ሲደረግብን እርምጃ መውሰድ አለብን ወይስ እግዚአብሔር ጣልቃ እስኪገባ ድረስ መጠበቅ አለብን? 4. ስጋ ደሙን መውሰድ የሚችል ማን ነው? የሚከለከለውስ ምን ቢሆን ነው? 5. የአሳማ ሥጋ መብላት ተፈቅዳል ወይ? 6. ሲፀለይ እጅ ለእጅ በመያያዝ ፀጋ ይተላለፋል ወይ? 7. ህይወታችን ከክርስቶስ ጋር ተሰውራል የሚለውን አብራራልን። 8. ንስሀ መግባት ያለብን የጌታ ራት ስንወድ ብቻ ነው ወይስ ሁሌም ማድረግ አለብን?
የዛሬ ጥያቄዎች 1. አገልጋዮችን እንዴት ነው ማረም ያለብን? 2. ሰቆ ኤር 3፡27-29 “ሰው በታናሽነቱ ቀንበር ቢሸከም መልካም ነው። እርሱ አሸክሞታልና ዝም ብሎ ለብቻው ይቀመጥ። ተስፋ የሆነው እንደ ሆነ አፉን በአፈር ውስጥ ያኑር።” የሚለውን አብራራልን። 3. “በእርሱ መኖን” የሚለውን ሀሳብ ግልጽ አድርግልን። 4. እውነታኛውን ህመም ጠላት ሊፈትነን ካመጣው ህመም እንዴት ነው የምንለየው? 5. ክርስቶስ የተነሳው በአካል ነው ወይስ በስብከት? 6. የሚያምን ልብ ክብሩ እንዲገለጥ ያዘጋጅለታል የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 7. አትስከር እንጂ አትጠጣ ነው የሚሉ ሰዎች አሉና ብታብራራልን? 8. አብርሃም ባልታመነበት ነገር የራሱን መንገድ እንዳዘጋጀ አይተናልና ብታብራራልን?
በንስሐ ከሐጢያቱ የተመለሰ ደግሞም ከውሀና ከመንፈስ የተወለደ አማኝ የእግዚአብሔር መንግስት ወራሽ ኔው፣ አማኞች የሆንን ሁላችን የዚህ መንግስት ወራሽ መሆናችን እጅግ በጣም ሊይስደስተን ይገባል ምክኒያቱም የምንወርሰው የእግዚአብሔር መንግስት ሁሉን የምትገዛ የዘለአለም መንግስት ፍርድ አደላዳይ ጌታ ንጉስ የሆነባት መንግስት ናትና፣ የሰማይ መንግስት ወኪል የሆነ አንድ አማኝ ለምድራዊው መንግስት ብቻ ቢያስብና ቢለፋ ምንም ትርፍ የለውም፣
ተቀድሰን እንድንኖር የስላሴ ሐሳብ ነው፣ መንፈስ ቅዱስ ይቀድሰናል፣ የእግዚአብሔር ቃል የማንጻትና የመቀደስ ሀይል ስለአለው የሚቀድሰን እግዚአብሔር ቢሆንም ፍላጎቱና ፈቃደኝነቱ ከእኛ ይጠበቃል፣ የጠራን ቅዱስ ስለሆን ስጋና መንፈስን ከሚያረክስ ማንኛውም ነገር ነጽተንና ተቀድሰን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንደሚጠብቅ አማኝ በትጋት በእርሱ ውስጥ እንድንኖር ይጠበቅብናል፣ ስንቀደስ እግዚአብሔር በመካከላችን ድንቅ ነገርን ያደርጋል፣
ጌታን ስንከተል መከራ አለብን። በዚህም ደስ ልንስኝ ይገባል።ይህ መከራ በእኛ ብቻ የሚደርስ ሳይሆን በወንድሞች ሁሉ ላይ እንደሆነ ልንገነዘብ ይገባል። መጠንቀቅ ያለብን ክፉ አድርገን መከራ ብንቀበል ከጌታ ዘንድ ምንም ምስጋና እንደሌለን ነው።በምናልፍበት መከራ ውስጥ እግዜብሔር አይጥለንም።በተስፍ ይጠብቀናል፥ ከመከራውም ያወጣናል። ስለዚህ ጌታን ተስፍ እያደረግንና እያመንን በመከራ ውስጥ እንጽና ጌታንም እንጥብቅ፡፡
እግዚአብሔርን የሚፈራ ከሁሉ ይወጣል፣ እግዚአብሔር ታማኝና እንደቃሉ የሆን አምላክ ነው፣ በእርሱ የሚታመኑትንና በፍርሃት የሚያከብሩትን ያውቃል፣ እግዚአብሔርን በመፍራት የሚኖር ሰው ጠግቦ ይኖራል ከመልካም ነገር አይጎድልም፣ እግዚአብሔርን መፍራት አሁን ላለንበት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ለትውልድ የሚሆን በረከትን ማከማቸት ነው፣ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው የጊዜው መነጋገሪያ ሊሆን ይችላል መጎብኘቱ ግን የበዛ ነው፣
ሰው ሸምግሎ አርጅቶ በስራው ሁሉ በእግዚአብሔር ከመባረክ የበለጠ ምንም ነገር የለም፣ ወደዚህ በረከት ለመምጣት ሚስጥሩ መታዘዝ ሲሆን ለመታዘዝ ማመን ያስፈልጋል ለማመን ደግሞ መስማት ያስፈልጋል፣ ከዘለአለም ጥፋት ያዳነንና በክርስቶስ እየሱስ በሰማያዊ ስፍራ ያስቀመጠን እምላካችን የከፍታውን ስፍራ እንድንይዝ ይወዳል፣ ምንም እንኳን በምድር ብንኖር በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሾች ነንና በላይ ያለውን ለመሻት መትጋት አንዳለብን መፅሐፍ ቅዱሳችን በተደጋጋሚ ያሳስበናል፣ በህይወታችን የምንበረታውና የሰማዩን መንግስት በትጋት የምንጠብቀው ልባችን የተዘጋጀውን ያህል ነው፣
የጥሞና ጊዜ ማለት በእግዚአብሔር ፊት መገኘት፣ እኛና እግዚአብሔር በትክክል የምንገናኝበት ስፍራና ሰዓት ነው፣ በእግዚአብሔር ህልውና ውስጥ የሆን ሰው የራሱ መሆን አይችልም፣ እንደቀድሞው አይነት ሰው አይሆንም፣ በዚህ ትምህርት ውስጥ ለጥሞና ጊዜ የሚያስፈልጉንን ነገሮች፣ ልናደርግ የሚገቡንና የጥሞና ጊዜ ለአንድ አማኝ ለምን እንደሚያስፈልግ በዝርዝር እንመለከታለን፣
የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እኛ ነን፣ እንድ ቤት ሊከብር ካስፈለገ ባለቤት ሊኖረው ይስፈልጋል፣ በዋጋ ተገዝተናልና የራሳችን ስላልሆንን ለእኛ ለአማኞች ህይወት ባለቤት ሊሆንና ሊከብር የሚገባው ደግሞ ጌታ እየሱስ ክርስቶስ ነው፣ የከፍታችንና የሰላማችን ምንጭ እርሱ ነው፣ ስለዚህ ከማንነታችን ወጥተን ክርስቶስ በእኛ እንዲከብር በሚረዳን መንፈስ ቅዱስ ስር ዕለት ዕለት ራሳችንን በማስገዛት በቅድስና ልንኖር ይገባናል፣
አንድ መንፈሳዊ ሰው አልኝ የሚለው ትልቅ ሃብት/ስኬት የሚመጣው በመንፈስ ቅዱስ ለመመራት ከበቃበት ነው። ሰው በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው በመንፈስ ቅድስ ቁጥጥር ሲሆን ነው። እግዜአብሔር ሲመራን በመንፈስ ሃሴት እናደርጋለን።ምሪት እግዚአብሔር ወደ ሚከብርበት የሚያገናኝ መንገድ ነው። ለእኛም እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት የሚያስኬድ መንገድ ነው።
-የዛሬ ጥያቄዎች 1. አማኝ ሁሉ በልሳን መፀለይ ይችላል ወይ? 2. ምሳሌ 28፡17 ሰውን መጥላት መግደል ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 3. ነፍስን መንካት እግዚአብሔርን መንካት ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. ፀልየን ላልተመለሰ ፀሎት ለምን ብለን ለመጠየቅ ጊዜ አለው ወይ? 5. እግዚአብሔር በጸሎት ሲናገረን ባለማስተዋል ካለፍነው በህይወታችን ሊያስከትል የሚችለው ነገር ምንድን ነው? 6. የአባት ሀጢያት በልጅ ላይ ደግሞ ለማድረግ ተያያዥነት አለው ወይ? 7. በአባት ሀጢያት ምክንያት ወደ ልጅ እንዳይመጣ ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? 8. ፊሊ1፡9-11 ቅንነት ጌታን ስናገኝ የምንቀበለው ነው ወይስ በፀሎት የምናመጣው ነው? 9. ቅን ያልሆነ ብልጥ ሰው ከጌታ ሰላም የለውም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 10. ፀሎት የሚያቅተን ለምንድን ነው? 11. አማኝ ስኬት ተብሎ የሚጠራው መክሰኑ ነው ወይ?
የዛሬ ጥያቄዎች 1. 2ኛ ነገ5፡3 የደረስንበት የፈውሳችን መቀበያ በሩ እንደሆነ የምናውቀው እንዴት ነው? 2. አልፎ ማየት ያልቻለ አማኝ በር ከፍቶ ሰይጣንን እንደማስገባት ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 3. በጠዋት የምናደርገው ነገር ጣዖት ይሆንብናል እና በረከታችንን ይይዛል ብለን ተምረናል ግን አንዳንድ ሰዎች በጠዋት ተነስተን ቃሉን አንብበን ፀልየን በረከታችን ትይዞብናል ይላሉ ይህ የሚሆነው እንዴት ነው? 4. መንፈስ ቅዱስ እየመራን እንደሆነ እንዴት ነው የምናውቀው? 5. ሰውነታችንና መንፈሳችን የሚያረክሱ ነገሮች ምንድን ናቸው? 6. ጌታን ማወቅና ከጌታ ጋር መገኘት እንድነት አላቸው ወይ? 7. ቅንነትና ጽድቅ ይገናኛል ወይ? ቅንነት ባህሪ ነው ወይ?
ወንጌል መንግስትን ያህል ትልቅ ነገር ከጀርባው ያዘለ ታላቅ ሐይል ነው፣ ይህቺ መንግስት ደግሞ በሰማይ ሆና በዚህ ምድር ግዛትዋን የምታሰፋ ስትሆን በመጨራሻው ዘመን የዚች መንግስት መቅረብ ለአለም ሁሉ ይነገራል፣ መንግስቱ ከዚህ አለም ስለአይደለች ማንም የማይጋራት ሁሉን የምትገዛ መንግስትና ዋስትና ያለበት የዘለአለም አምላክ ገዢዋ የሆነ በመልካም ዕንቁ የተመሰለች መንግስት ናት፣ ሃጢያታችንን በመናዘዝ በወንጌሉ አምነን የእግዚአብሔር ልጆች የሆንን ሁሉ የላይኛው መንግስት ወራሾች ስለሆንን በምድራዊ ነገር ላለመያዝ መትጋት አለብን፣
በዚህ ትምህርት ውስጥ ስለ ፊልጵስዩስ መልእክት መቼ ማንና የት እንደተጻፈ እንማራለን፣ መልእክቱ የሚያተኩረው ደስተኛ ስለመሆን ነው፣ እውነተኛ ደስታ የሚገኘውና ለሁሉ ደግሞ መፍትሔ የሆነው ሁኔታ ወይም በምድር የምናገኛቸው ነገሮች ሳይሆኑ የምስራቹ ወንጌል መሆኑን ለማስርገጥ ዻውሎስ በሁሉ ደስ ይበላችሁ እያለ መልክቱን ሲያስተላልፍ በእስር ቤት ውስጥ ሆኖ ነበር፣
እግዚአብሔር የራሱን የልቡን ሀሳብ ነው እንዲናገረን የምንፈልግው ወይስ የእኛን የልባችንን ሀሳብ ነው እንዲነገርልን የምንፈልግው!! በዚ ስብከት ራሳችንን እንመረምራለን፤ እግዚአብሔር የራሱን የልቡን ሀሳብ ሲናገረን ግን ታሪካችን ይለወጣል፤፤
በአዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ጉባኤ ነች የጌታን አጀንዳ በምድር የምታስፈጽም፤ የኢየሱስ ሙሽራ ነች ዳግም ምጽአቱን የምትጠባበቅ፤ እግዚአብሔር ለአንድነት በአንድነት ቤተክርስቲያንን ጠራ፤ ቤቱ የእውነት አምድና መሰረት ነው
የጥሞና ጊዜ እግሂአብሔር ፊት ያለምንም ጥያቄ መሆን ነው። ቅድስና እና ንጽህና ባለበት ህይውት ጌታን የምንንገናኝበት ነው። የጥሞና ጊዜ, እግዚአብሄር ፊት ሆነን ፈቃዱን የምንሰማበት ነው እንጂ የአንድ ጊዜ ሁኔታን ፈጽመን ብዙ የጸሎት ርዕሶቻችንን ይዝን የምንንቀርብበት አይደለም።ነገር ግን እርሱን የምንሰማበት ጊዜ ነው።
እግዚአብሔር ስለ ስሙ የሚሰራ አምላክ ነው። ጌታ ስለ ስሙ ሲሰራ ጸሎቴ ነው ልመናዬ ነው ብለን ልንመካ አንችልም፣ ካልንም ትዕቢት ነው። እግዚአብሔር ማንኛውንም ነገር በህይወታችን የሚሰራው ስለትቀደሰ እና ስለ ታላቅ ስሙ ነው። በእኛ ላይ ስለተጠራው ስሙ ሲል የባርከናል የሚያስፈልገንን ይሰጠናል።ስለዚህ ልመናችንና ጸሎታችን ምስክርነታችን እንጂ ትምክህታችን ሊሆን አይገባም።ስሙ ከስሞች ሁሉ በላይ ነው። አጋንንትን ያንቅጠቅጣል ፣ ያስወጣል፣በሽታንም ይፈውሳል።
እግዚአብሔር የልቡን ሀሳብ በእኛ በባሪያዎቹ ያየውን አስደናቂውን ነገር አይችልምን ይችላል አይሆንምን ይሆናል እያደረገ አምጥቶ ክእኛ ህይወት ጋር የሚያገጣጥመው ራሱ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤፤
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ጌታን እንድንቀበል መንፈስ ቅዱስ እንዲያበራልን ያስፈልጋል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 2. መንፈስ ቅዱስ የማይመራው አማኝ ህይወቱ አደጋ ላይ ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 3. እግዚአብሔር እጃችንን ይዞ መንገዳችን ግን ለጠላት ሊሰጥ ይችላል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 4. በልጆቻችን ላይ እንዲሆን የምንፈልገው የእግዚአብሔር ፍቃድ ይሁን አይሁን እንዴት ነው የምናው ቀው? 5. እንደ አማኝ ህልም ስናይ ምንድን ነው ማድረግ ያለብን? እግዚአብሔር ህልም ይሰጣል ወይ? 6. በእምነት ለማደግ ከእኛ የሚጠበቀው ምንድን ነው?
ወደ ከበረው የእግዚአብሔር መዝገብ የምንገባው ፈቅደን ከተዋረድንበት ከተጣልንበት ነው፤፤ ከተዋረድንበት በጊዜው ያከብረናል ከተጣልንበት በጊዜው ያነሳናል ዝቅ ካልንበት በጊዜው ከፍ ያደርገናል፤፤ በምድር ላይ ጸንቶ የሚኖረው ክብር እግዚአብሔር ያነሳው ክብር ብቻ ነው፤፤
የዛሬ ጥያቄዎች 1. እግዚአብሔር የሚያደርግልን ስለ ስሙ እንጂ ስለ ፆምን እና ስለ ፀለይን አይደለም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 2. በህይወታችን በሚያልፈው ነገር እንዴት ነው ወደ ማጉረምረም ህይወት ልንገባ የምንችለው? 3. ምለን የገባንበት ነገር ስንነካ እግዚአብሔር እኛን ይነካል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 4. መስቀል በተለያየ ምክንያት የምናልፈው ችግር ነው ወይስ ስለ ክርስቶስ የምንቀበለው መከራ? 5. ሰው እንዴት ነው በአገልግሎት አድጎ በህይወት ላያድግ የሚችለው? 6. በመጠበቅ ውስጥ እንዴት ነው የእግዚአብሔርን ፍቃድ ልናውቅ የምንችለው?
ቤተ ክርስቲያን የተመሰረተችው በጌታ ላይ ነው ደግሞ ራስ የሆናትም ጌታ ነው፤ ቤተ ክርስቲያን ህያው በሆነው ክርስቶስ የተጠራች፣ የእርሱ የሆነች፣ የእኔ የሚላት፣ የሚመግባት፣ የሚንከባከባት፣ የሚያስውባት፣ የሚያሳድጋት፣ አካሉ ናት፤ እኛ ደግሞ በእርሱ ያምናምን ወደዚህ አካል ነው የገባነው፣ እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን፣ አንዳችን የአንዳችን ጉዳይ ይሰማናል ስለዚህ በማንፈስ አንድነትና በፍቅር ይህን አካል ላማነጽ እንትጋ፤
ሕዝቅያስ በእግዚአብሔር በመታመን በታላቁ በአሶር ንጉስ የመጣውን ታላቅ መከራ በድል እንደተወጣ ሁሉ፣ የእግዚአብሔር ልጆችም በእርሱ በመታመን ፣ ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ(በፀሎት) እንዲሁም እግዚአብሔርን በመጠበቅ በሚገጥማቸው የህይወት ፈተና በድል መወጣት ይችላሉ። ሁሉም ቅዱሳን አባቶች የመከራን ቀን ድል የነሱት እግዚአብሔርን በመታመን ነውና ።
ጌታ ተመልሶ እንደሚመጣ በብዙ የመጽሐፍ ቅድስ ክፍሎች እንደተናገረን ሁሉ ተዘጋጅተን እንድንጠብቀውም መክሮናል:: መንፈሱና ሙሽራው ና ይላሉ ምክንያቱም የሁሉ ጥያቄ መልስ ያለው ዳግም በመምጣቱ ውስጥ ነውና፣ ያቀን በድንገት እንደሌባ ይመጣልና ነቅተን በንፅህና እንጠባበቅ::
የዛሬ ጥያቄዎች 1. እግዚአብሔር ሰውን እንዲያነሳ ሰው በመጀመሪያ መጣል አለበት ወይ? 2. ከሁሉ መጣል በሗላ ነው መነሳት ያለው ወይስ ሌላ መታል አለ? 3. በሩን የዘጋሁት እኔ ልሁን እግዚአብሔር መሆኑን እዴት ነው እንዴት ነው የምናውቀው? 4. ሰው ባለፈበት ባልተፅናናበት ለሌላውን ሰው ማጽናናት ይችላል ወይ? 5. እግዚአብሔርን በመጠበቅ እንዴት ነው ህይወታችንን የምንመራው? 6. ሰው እግዚአብሔርን ከመፈለግ ሰደ አለመፈለግ መሄድ ይችላል ወይ?
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 29፡5 ከወዳጆቻችን ጋር ስህተትን ስህተት ካላልን የራሳችንን ፅድቅ የለንም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. ለወንድሙ መብራት መሆን ያልቻለ ጽድቅ የለውም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 3. ከምስጋና ህይወት እንዴት ነው ወደ ማጉረምረም ህይወት የምንመጣው? 4. እግዚአብሔር የደበቀውን አንዳንድ ግዜ እኛ ልናወጣው እንፈልጋለን ይህ ደግሞ ዋጋ ያስከፍለናል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 5. ለእስላም ወንጌልን ለመንገር ቁራን ማንበብ ጥሩ ሀሳብ አይደለም ወይ? 6. ሰማያዊ ጥበብን ከምድራዊ ጥበብ እንዴት ነው የምንለየው? 7. ሰማያዊ ጥበብ በህይወታችን የማይገለጠው በምን የተነሳ ነው?
እግዚአብሔርን ማንም አላየውም ነገር ግን አንድያ ልጁ ተረከው አንደሚል ቃሉ፣ እግዚአብሔርን በሚገባ የገለጠው ጌታ እየሱስ ነው። እንዲሁም ሐዋርያቱ አብረው ከጌታ ጋር ስለነበሩ ያዩትንና ከእርሱ የሰሙትን መስክረዋል። በዚህ ክፍል እኛም በክርስቶስ የሆንን የባህርይው ተካፍዮች ከሆንን ምስክሮቹ እንደሆንን እንማራለን። ይህም እግዚአብሔር ብርሀን እንደሆነ ጨለማም በእርሱ ዘንድ እንደሌለ ፤እኛም በብርሀን ልንመላለስ እንደሚገባንና ደግሞም ጨለማ በእኛ ዘንድ ካለ ንሰሀ መግባትና መመለስ እንዳለብን እንጂ በዚህ ዘመን እንደሚያስተምሩት በስጋ የሚደረግ ሀጢያት ምንም አይደለም ብለን እንዳንጠፋ ያስጠነቅቀናል።
እግዚአብሔር የስጠንን ደስታ የሚስርቁብን ነገሮች ምን እንደሆኑ ጠንቅቀን ተረድተን ከህይወታችን እንዴት ልናስወግዳቸው እንደምንችል ያስተምረናል። ደስታችንን የሚሰርቁብን ነገሮች ብዙ ናቸው። ነገር ግን በዚህ ትምህርት ውስጥ ፍርሀትን፤ገንዘብን መውደድና፤ ጭንቀትን እንመለከታልን። መፍትሄያቸውም፣ሁኔታን ስይሆን ጌታን መፍራት፤ ገንዘብን ሳይሆን ጌታን መውደድ፣ መጨነቅ ሳይሆን ጌታን ማመን እንደሆነ በሰፊው ያስረዳናል ።
እግዚአብሔር ሲመጣ ያልጠበቅነውን የክብሩን ስራ ሊያደርግ ነው፣ እግዚአብሔር ስውን ድንገት አይጎበኝም ነገር ግን ሰው ለጉብኝቱ የበቃ እንዲሆን የሚጎበኘውን ሰው ያበጃል ይሰራል ይመክራል ደግሞም ያስተምራል፣
የተወደደ ቀን እንዳለ ሁሉ የክፉ ቀንም እንዳለ ልንገነዘብ ያስፈልጋል። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደሆነ ፣እንደማይተወን ፣ያለ እርሱ ፈቃድ በህይወታችን ምንም እንደማያገኝን ልናውቅና ልንረዳ ያስፈልጋል። በስይጣን ሽንገላ እንዳንታለል አዕምሮእችንን ልንጠብቅ ይገባናል። የመጀመሪያና ትልቁ ነገር በዚህ እውነት ውስጥ ሆነን ምሽጋችንን መጠበቅ ነው። በዚህ እውነት ከቆምን ውጊያው የጌታ ስለሚሆን አሸናፊዎች ነን። ይህንን እውነት ጥለን ግን አዎ፣ ጥሎኛል፣ትቶኛል፤ ከእኔ ጋር የለም ካልን በሰይጣን ውሸትና ሽንገላ ተታለን እንወድቃለን።ሰይጣን ሸንጋይና ውሸታም ነው።
ትልቁ የአምላካችን የእግዚአብሔርን ድምጽ የምንሰማበት መንገድ ቃሉ ነው: ይሄ ህያውና ክቡር ቃሉ አይሻርም መዶሻ ነው እሳት ነው ዘላለማዊ ነው የሚሰራ ሁለት አፍ ካለው ስይፍ ይልቅ የተሳለ ነው::
ቤተክርስቲያን ህያው የሆነች የእግዚአብሔር ተቁዋም ነች፤ ወደ ክርስቶስ የፈለሱ አዲስ ፍጥረት የሆኑ ዳግመኛ የተወለዱ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ህይወት ያገኑ የዳኑ የቅዱሳን ስብስብ ነች ቤተክርስቲያን።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ኢዮብ 19፡25-27 እኛ የምናልፍበት ችግር ወይም መከራ የእግዚአብሔር ክብር መግለጫ እንደሆነ የማውቅበት መንገድ ምንድን ነው? 2. ትዕግስት የሌለን ሰው ከሆንን እግዚአብሔር አያገኘንም ማለት ነው? 3. ዮሐንስ 3፡13 ያለንን ጥበብ እና ማስተዋል የምናሳይበት መንገድ አለ ወይስ ቃሉን ማንበባችና መጸለያችን ነው? 4. ሰዎች በሰማያዊ ጥበብ ይናገሩን ወይም የራሳቸውን ጉድለት መሸፈን ይህን እንዴት ነው የምንለየው? 5. ብዙ አማኞች አሉ ነገር ግን ለተቀደሰ ሰልፍ ግን ብቁ አይደሉም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 6. ምሳሌ 29፡9 ጠቢብ ይጣላል ወይ? ጠቢብ የሚጣላው ከሀጢያት ጋር ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 7. በህይወታችን የሚይልፈው መፍራትና መታወክ መሆኑን እንዴት ነው የምናውቀው?
አንድ እውነተኛ ክርስቲያን የተጠራው ክርስቶስን ለመምሰል ነው። ስለዚህ ጳውሎስ ያለውን ሁል ስለክርስቶስ እንደ ጉድፍ ቆጥሮ እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ እንዳለ እኛም ስለክርስቶስ መተው ያለብንን ነገር እየተውን ለሌሎች ምሳሌ በመሆን ክርስቶስን እየመሰልን የእግዜአብሔርን ፍቃድ ምን እንደሆነ አውቀን፣ በፍቅር የተሞላ ህይወት ሊኖረን የገባል። 1ኛ ቆሮንቶስ 11:1
የእግዜአብሔርን ጸጋ መቀበያ መጠን፣ እግዚአብሔርን መስማት መጠን ነው፤ እግዚአብሔር እኛን ባገኘበት መጠን እኛ ድግሞ እራሳችን በሰጠንበት መጠን ነው እግዚአብሔር የሚናገረው። በእግዚአብሔር ከታቀደልን ከዘላለም ሃሳብ ጋር የምንገናኘው እነሆኝ እኔ ምን እንዳደርግ ትወዳለህ ብለን እግዚአብሔር ሲናገረን እኛ በሰማነው በኩል ነው። ከእግዚአብሔር የሰማ ሰው የሄደበትን ደግሞ አይሄድም የኖረውን ደግሞ አይኖርም። ሙሴ እግዚአብሔር ከተናገረው በኃላ አንድ በትር ይዞ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሊያወጣ ተነሳ።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ኢየሱስ ያልበቃው ሰው ምንም ነገር የማያረካው ሰው ነው እንዲህ አይነቱ ሰው በህይወቱ እድገት የለውም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. ኤፊሶን 2፡6-7 ማርቆስ 5፡36-39 ጌታ የሚሰጠንን ነገር ቁጭ በሉ በማለት ነው የጀመረው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 3. ዘፀ 14፡13 ቁጭ ያለ ሰው በመጨረሻ ቆሞ ይገኛል የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. ዮሐንስ 20፡23፣ ማቴ16፡19 18፡18 የሚሉት ይብራራልን። 5. ጌታን ከመከተል ወደ ጌታን አለማወቅ ልንገባ እንችላለን ወይ? 6. ወንድሞችን ማስቀደም ጌታን ከማስቀደም ጋር ያለው ልዩነት ምንድን ነው? 7. በጌታ የሚቀድሙንን እስከ ምን ድረስ ነው ማስቀደም ያለብን?
የአንድ አማኝ መንፈሳዊ ሀብቱ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ራስን በእግዚአብሔር ቃል ተስፋ በመለኮት ሀሳብ ውስጥ ማግኘቱ ነው
የጥሞና ጊዜ በእግዚአብሔር ላይ የማረፍ ህይወት ነው የጥሞና ጊዜ የለመዱ ሰዎች ፊቱን ይናፍቃሉ በእግሩ ስር መሆን ይወዳሉ ደስታና እረፍት በመንገዳቸው ነው አይናወጡም ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ስር ናቸው
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 30፡11-12 በወላጆቻቸው የተጎዱ ልጆች የእግዚአብሔር በረከት እንዲያገኛቸው እንዴት ነው እንደዚህ ዐይነት ልጆችን ማገልገል የምንችለው? 2. በግልፅ የሚደረግ ፀሎትና በስውር የሚደረግ ፀሎት ብታብራራልን? እንዴት ነው እንደዚህ ዐይነቶች ፀሎት መፀለይ የምንችለው? 3. ምሳሌ 31፡1-5 ልጅን በማሳደግ ውስጥ ልጆች በሚያልፉበት መንገድ የወላጆች ድርሻ በተመለከተ ምን ትመክረናለህ? 4. ከውጪ ያየነውንወደ ቤተ ክርስትያን ስላመጣነው ምን ትመክረናለህ? 5. ምሳሌ 31፡13 በማጉረምረም እና በማረም ላይ ልጅን በማሳደግ ላይ ያለው ልዩነት ምንድን ነው?
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ጌታ የሰጠን ፍቅር እሱን ብቻ እንድንወድ ሳይሆን የእርሱ የሆኑትን ጭምር እንጂ የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. የእርሱ የሆኑትን መውደድ የምንቸገረው ለምንድን ነው? 3. 1ኛ ቆሮንቶስ 1፡4 ያደገ ሰው በሞተ ፍቅር ላይ ህይወትን ይዘራር የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. የእግዚአብሔር እረፍት በእኛ የሚሆነው እሱ በአለን ውስጥ ስንገኝ ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. ራሳችንን እግዚአብሔር በተናገረን ካላየን መስኮት እንደሌለው ቤት ነው የምንሆነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 6. ዮሐንስ 5፡5 መንፈሳዊ ነገር ስንሆን አስመስለን የምንለው ነገር አለ እና ይህ ይብራራልን። 7. መኋልየ መኋልይ ዘሰለሞን 4፡12-16 የመከራ እና የድርቀት ንፋስ ካለመጣ ነገራችን አይከፈትም ወይ?
ከሰማይ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ህይወታችንን ኑሮአችንን ዛሬንና ነገአችንን ያቀናል ጌታ አስቀድሞ በህይወታችን በተናገረው ውስጥ እናልፋለን መልካሙን ገድል እንጋደላለን
እግዚአብሔር ያለውን የሚያደርግ ሉአላዊ አምላክ ነው ቅንነት ፊቱን ታየዋለች እግዚአብሔር መግቢያው የቀና ልብ ነው በረከቱ ወደ እኛ የሚመጣው በመታዘዝ ነው
የጥሞና ሕይወት የተለማመዱ ስዎች የእግዚአብሔርን ቅድስና ይለማመዳሉ የቅድስናውን ሕይወት ይካፈላሉ ከብዙ ነገር እራሳቸውን ይጠብቃሉ። ቅድስና ከእግዚአብሔር የምንካፈለው ነው በራሳችን ይምናመጣው አይድለም፤ መጽደቅ አንድ ግዜ ነው፡ ቅድስና ግን እለት እለት ይምንለማመደው ነገር ነው፤ ጽድቅ የተገለጠው በጌታ በእየሱስ ክርስቶስ ነው።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. የጌታ ወዳጆች ሀጢያተዮች ነበሩ የእኛስ ወዳጆች እነማን ናቸው? 2. እግዚአብሔር በተለያየ ጎዳና ሊያገኘን ይችላል። ጸሎታችንንም ሊመልስ ይችላል ነገር ግን ያልተገኘ የህይወት ክፍል ሊኖረን ይችላል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 3. ማቲዮስ 3፡16-17፤ 4፡1 ለእግዚአብሔር ለመገኘት ከጥምቀት በሗሏ በመስቀል ህይወት ማለፍ አለብን ወይ? 4. መኋልየ መኋልይ 4፡12 ምንጩን የምንደፍነው ራሳችን ነን ነገር ግን እግዚአብሔር ይከፍተዋል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 5. በህይወታችን ቅጣት ሲመጣ እንዴት ነው የምናውቀው? ይህንን እኛ ነን ወይስ ሌሎች ናቸው የሚይውቁት? ቅጣትስ ለምንድን ነው የሚመጣው? 6. 1ኛ ጥሞቴዎስ 2፡15 ይብራራልን። ምሳሌ 31፡15 ማለዳ የሚለው ግዜን ነው ወይ የሚያመለክተው? 7. ምግብ አብልታ ወደ ተግባር ታሰማራቸዋለች የሚለው ሀሳብ ቢብራራልን? 8. ኤፌሶን 2፡5 በአደገ ማንነታችን ጸጋን የምንፈልገው ከሀጢያት ለመላቀቅ ነው ይላደገው ማንነታችን ግን ጸጋን ለመሸፈን እንፈልገዋለን ይህንን ወደ እኛ ህይወት አምጥተ አብራራልን።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 31፡11 መንፈስ ቅዱስን የሚያሳዝን ሰው ይለፋል ፍሬ የለውም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. መዝሙር 53፡1 የሚጸጸት ህይወት ከሌለን የንስሀ ፍሬ የለንም የሚለው ሀሳብ አብራራልን። 3. ምሳሌ 16 ለትውልድ የምናተርፈው ነገር ምንድን ነው? 4. ምሳሌ 31፡17 የውሳኔ ሰው መሆን ያስፈልገናል የውሳኔ ሰው ያልሆነ ግን ህይወት አደጋ ላይ ነው ያለው ለእርሱ ብቻ ሳይሆን በአካባቢው ላሉ ጭምር መሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 5. ወደ እግዚአብሔር ስቀርብ እንደ ማይገባው ሰው መኦን አለበት የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 6. ምሳሌ 31፡18 አመስጋኝ ሰው መብራቱ አይጠፋም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 7. የአንዳንድ ሰው መብራት የሚታየው በቀን ብቻ ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። ይህ ብርሀን በቀን ብቻ እንደሚበራልን በማታ እንደማይበራ እንዴት ነው የምናውቀው? 8. 2ኛ ነገሥት 8 እግዚአብሔር የሚያየን ቃሉን እንዴት እንደ ተቀበልን ነው እንጂ ምን እንዳደረግን አይደለም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን።
እግዚአብሔር በማእበል በወጀብ ውስጥ መንገድ አለው ክብሩን ለመግለጥ እምነታችንን ለመጨመር እንባችንን ለመጥረግ የጎበጠ ነገራችንን ቀና ለማድረግ ለማስጣል ለማዳን ለመባረክ መንገድ አለው
የውስጥ ጥማት ካለ ለኔ አይሆንም የምንለው ምንም ነገር የለም፣ እግዚአብሔር ዘኪዮስን በጊዜው እንደጎበኘው፣ እኛ ክርስቶስን ለማግኘት ፍላጎትና ጥማት ይኑረን እንጂ ጌታ ማንንም አያሳፍርም፣ እርሱን ለማየት ብዙ ነገሮች በዙሪያችን ቢጋርዱን እንኳን የልባችንን መሻት የሚያውቅ አምላክ እግዚአብሔር በጊዜው በዙሪያችን ከጋረዱን ነገሮች አልፎ ወደእኛ ይመጣል
ሰማያዊ ዜግነትን ሰው የሚያገኝው ወንጌልን ሰምቶ ሲያምን ብቻ ነው ወንጌል ሁሉም አካል የሚሰራው ስራ ሲሆን አንዱ በመሄድ ሌላው በጸሎት በገንዘብ በሚያስፈልገው ሁሉ ይህን የምስራች በማድረስ ሰዎች ሲድኑ ደስ መሰኝት ለተቸገሩ መድረስ ነው
እግዚአብሔር ያለውን የምንሆነው በመለኮት ጥበቃ ውስጥ እንዳለን አይናችን ሲበራ ብቻ ነው፣ ያለዚያ እንታወካለን፣ ለፈቃዱ ወይም ለተጠራንበትም መኖር አንችልም፣ አይናችን ሲበራ ግን እራሳችንን ከሐጢያት የምንጠብቅበት ወይም ክፉውን የምንጸየፍበትና እግዚአብሔርን በመፍራት የምንኖርበትን ማስተዋልና ጥብብን የተቀበልነው ከመለኮት መሆኑን እንረዳለን፣ በእርሱም አርፈን እንኖራለን
እምነት ማለት በእግዚአብሔር ዘንድ የሚደረግልንን አይናችን ሳያይ ጌታ በተናገረን ውስጥ ሆነን ሁሉን ለርሱ በመተው እንደሆነልን እንደተደረገልን አምነን በሰላሙ ውስጥ ማረፍ ነው
አማኝ ከሁሉ በላይ የሚያስመካው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አብሮነትና መገኝት ብቻ ነው እግዚአብሔር በምህረቱና በቸርነቱ በህይወታችን ከሚያደርገው በጎነቱ የተነሳ የጊዜውን ነገር ብቻ እየተመለስ የምንኖር ሳይሆን በእምነት እንድናድግ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው
ኃጢያት ወደ ዓለም ሲመጣ ውርደት ይዞ ነው የመጣው፣ አዳምና ሕዋን ኃጢአትን በሰሩ ጊዜ ከእግዚአብሔር መንግሥት ጎሎዋል፣ውርደትን ለብሰዋል፣ መንፈሳዊ ውድቀት የሆነው በሰው ሕሊና፣ በሰው ልብ፣ በሰው አስተሳሰብ፣ በሰው አመለካከት ውስጥ ነው፥ ጌታ ኢየሱስ ስጋ ለብሶ ወደ ምድር የመጣው በኃጢያያት ምክያት ከአግዚአብሔር መንሥት የተለየውን የሰው ልጅ ወደ ክብሩ ለመመለስ ነው፤ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ ብሎ በቃሉ እንደ ተናገረ አምነው ለተከተሉት የሕይወት ተድሶ ለማድረግ ነው
ክርስትና በጨለማ ላለው ሕዝብ የሚመሰከው በመኖር ነው፥ ጌታ በቃሉ ስያስተምር፤ መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ ብሎዋል፣ ጌታ ሐዋርያትን በአፍ ከመመስከራቸውና ከመስበካቸው በፍት ክርስትናን ነረው እንድያሳዩ ነው የፈለገው፥ ክርስትና ኖረን በሕይወታችን የሚታይ መሆን አለበት፣ የጌታም ክብር ጎልቶ የሚታየው ያኔ ነው
እግዚአብሔር ለቃሉ የታመነ ነው፣ እርሱ እስራኤላውያንን ሊያድን ሲመጣ ለአባቶቻቸው የገባውን ቃል ነበር የሚያመለክታቸው፣ የእምነት አባቶችም የተስፋይቱን ምድር እንደሚወርሱ የተናገራቸው አምላክ እግዚአብሔር ታማኝ መሆኑን ተቀብለው ምድሪቱን እንደሚወርሱ አምነው ነው የሞቱት፣ አንዳንድ ጊዜ መከራው በዝቶብን አልፈን ማየት ቢከብደን እንኳን እግዚአብሔር አደርጋለሁ ያለውን የሚያደርግን ምንም የማያቆመው ታላቅ አምላክ መሆኑን ልናምን ያስፈልገናል፣ Activity
ሐዋርያት አንድ ላይ በመሆን ይተናነጹ ነበር፣ ዛሬም በዘመናችን ቤተ ክርስቲያን እንድትናነጽ አንዳችን ለአንዳችን መጸለይ የወንድማችን ወይም የእህታችን ነገር ተስምቶን ልንሸካከም ይገባናል፣ እንዲሁም የእግዚኣብሔርን እውነት እየገለጽን በመካከላችን ያለ እውቀት ያሉትን በቃሉ እግዚአብሔርን ወደማወቅ እንዲደርሱ ማስተማር፣ እርስ በእርስ በመዋደድና በመከባበር አብረን የሰማዩን መንግስት እንደምንወርስ ሁልጊዜ ማሰብ ያስፈልገናል
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሳምሶን የተቀባ አመንዝራ ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። እግዚአብሔር የቀባው ሰው እንደ ሳምሶን ዐይነት ህይወት ነው የሚባለው ምን አይነት ሲሆን ነው? 2. የቃሉ ሙላት የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 3. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከሌለ ለልጆቻችን ወንጌል ማድረስ አንችልም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። ወንጌል ሰምተው ሰዎች ወደ መዳን የማይመጡት ለዚህ ነው ማለት ነው? 4. ጌታ እየሱስ 30 ዓመት ለማገልገል መንፈስ ቅዱስ ስላልተሞላ ነው ወይስ ግዜው ስላልደረሰ? 5. ቃሉ ክርስቶስ ስለሆነ ቃሉ የሌለው ሰው ደስታ የለውም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
የዛሬ ጥያቂዎች 1. ነፃ የወጣ ሰው ነው ለእግዚአብሔር የሚሆነው ይህ ደግሞ እድገት ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 2. ጌታን ስንቀበል በመንፈስ ቅዱስ ታትመናል ልጅ ለመሆን ግን ገና መንፈስ ቅዱስ አልተሞላንም የሚለው ሀሳብ አብራራልን። 3. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚሄደው ከመታዘዝ ጋር ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. በመዳን ውስጥ ትልቅ ትንሽ የለም ወደ መንፈስ ቅዱስ ሙላት ስንመጣ ለእያንዳንዱ የተለያየ መለእክት አለው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ የአሸናፊነት አቅም የሚኖረው ህይወታችን ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
የቤርያ ሰዎች ልበ ሰፊዎች ነበሩና ነገሩ እንደዚሁ ይሆንን ብለው ዕለት ዕለት መጻሕፍትን እንደመረመሩ እንደ እግዚአብሔር ቃል ሆኖ ሲያገኙት ደግሞ ቃሉን በሙሉ ፈቃድ እንደተቀበሉ አማኝ ከቃሉ ጋር የሚንሰማውን ሁልጊዜ ማመሳከር አለበት
በእኛ መልካምን ስራ የጀመረው ልኡል እግዚአብሔር ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በህይወታችን የሚሰራው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው የታመነ አምለክእ ነው
የእግዚአብሔር የሆነው ሁሉ መንፈሳዊ ነው፣ አኛ አማኞች ቃሉን ሆነን የምንገኘው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው፣ ያለመንፈስ ቅዱስ የክርስቶስን ሙላት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለስዎች ማድረስ አንችልም፣ ይህንን መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ካልታዘዝን፣ ህሊናችን ንጹህ ካልሆነና ካልተጠማን መሞላት አንችልም፣ ጌታችን እየሱስ እራሱ ከመታዘዝ ጋር አያይዞታል፣ ትዕዛዛቱን ሁሉ ጥለን መንፈሱን መፈለግ አንችልም፣ ትዕዛዛቱን መጣል ማለት እታድርጉ የተባልነውን ማድረግና አድርጉ የተባልነውን ደግሞ አለማድረግ ነው፣
ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፣ ክርስቶስን የሚያውቅና የእርሱ ተከታይ የሆነ እማኝ ዋነኛው የባህሪው መገለጫ ፍቅር ሊሆን ይገባል፣ ጌታ እየሱስ እንኳን አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው ከሕግ የትኛይቱ ትእዛዝ ታላቅ እንደሆነች ሲጠይቀው የመለሰው መልስ፣ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍሥህም በፍጹም አሳብህም ውደድ ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም ባልንጀራህን እንደ ነፍሥህ ውደድ የምትለው ናት ብሎ ነው፣ እንግዲህ በዚህ ፍቅር ለማደግ የመጀመሪያው ይቅር ማለት ሲሆን በመቀጠል ፍቅርን መከታተልና ከቅዱሳን ጋር ጤነኛ ህብረትን በመፍጠር ልንገለጽ ይገባናል፣ ክርስቶስ በምን ያህል ፍቅር እንደወደደን ሲገባን ሌሎችን ለመውደድ አንቸገርም፣
ጠላት ይከሳል ነገር ግን የሚሰምርለት ከውስጥ ከአካል ተባባሪ ካገኘ ብቻ ነው። ምክንያቱም ጌታ የቅዱሳን ክስ ስለማይሰማ። ይህም ፀጋን ብቻ እንድንመለከት ነው።
ሰይጣን ደካማ ጎናችንን ያውቃል ነገር ግን ከዛ ውስጥ ጠንካራ ነገር ይወጣል። ይህ ጠንካራ ጎን የሚወጣው በሞትንበት ነው።
በንስሐ ወደ እግዚአብሔር እንደርሳለን፣ ጌታን እንደግል አዳኛችን አድርገን ስንቀበልና በሐጢያታችን ስንናዘዝ ጌታ ይቅር ይለንና ልጆቹ ያደርገናል፣ ዳግመኛ በእውነት ቃል ከማይጠፋው ዘር እንወለዳለን፣ ጌታን ካወቅን በኋላ ንስሐ ያልገባንበት ሐጢያት ካለ የእግዚአብሔር ለሆነው ነገር ጠንካሮች እንዳንሆንና በጉስቁልና እንድንኖር ያደርገናል፣ እግዚአብሔር ከሐጢያት ጋር ሕብረት ስለሌለው ከጌታ ጋር ህብረት እንዳይኖረንም ያደርጋል፣ ስለዚህ እራሳችንን ሁልጊዜ አየመረመርን በንስሐ የእግዚአብሔርን ፊት ልንፈልግ ይገባናል፣
እግዚአብሔርን በታሪክ ውስጥ ስናየው እምነታችን ይጨምራል፣ መንፈሳዊ ሰው የሚኖረው በእምነቱ ስለሆነ እምነታችን ሲያድግ አንዳንዴ እግዚአብሔር እየተናገረ ያለው ባዶ በሆነ ነገር ላይና ለሰው በማይመስል ነገር ላይ የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለማስተናገድ አንቸገርም፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለመበጥበጥ በሚመጣው ማንኛውም ነገር ባለመታወክ ፍቅሩንና ምህረቱን እያሰብን እግዚአብሔር የማያሳፍር አምላክ መሆኑንም በመረዳት፣ የሚታየውን የሚሰማውንና የምናስበውን ሳይሆን ጌታን ማየትና መስማት እንጀምራለን
መልአክና ሰው የተፈጠረው ለአምልኮ ስለሆነ ወንጌልም ወደ ሕይወት ካመጣን በኃላ ወደ አምልኮ ነው የሚያደርሰን፣ በትክክለኛ አምልኮ ከአምላካችን ጋር ስንገናኝ የእግዚአብሔርን ትልቅነት እያየንና እግዚአብሔር በስራው ጻድቅ መሆኑን እየተረዳን በምናልፍበት ሁሉ እርሱን ማመስገን እንጀምራለን፣ መርገማችንን ሽሮ የመንግስቱ ወራሾች ያደረገን አምላካችን እዚህ ምድር ላይ ያስቀመጠን ለመንግስቱ ስራ መሆኑ ሲገባን ዛሬ የምለምናቸው ነገሮች ያንሱብንና በምስጋና እንሞላለን፣ በምስጋና ደግሞ ብዙ ቀንበራችን ይሰበራል ብዙ ድልንም እንቀዳጃለን፣
እግዚአብሔር የታደገን ሊመራን ቢሆንም፣ እኛ አማኞች ደግሞ በእርሱ ዓላማና ሐሳብ የተያዝንና እርሱን ለመከተል ፈቃደኛ መሆን አለብን፣ እግዚአብሔር ያለን ሰዎች ሆነን ግን ብዙ ጊዜ በራሳችን መንገድ እንሄዳለን በራሳችን ደግሞ ሁሉን ለማድረግ እንሞክራለን ሆኖም በአንድ ቦታ መዞር መጥመልመልና ድካምን ነው የምናተርፈው፣ ተስፋ የሚጣልበት እውነተኛው አምላክ እግዚአብሔር ሲመራን ግን እርሱ መንገድ በሌለበት መንገድ በጨለማ ውስጥ ደግሞ ብርሀን ይሆንልናል፣
አንዳንዱ የጸሎት መልስ መፍትሄ የሚመጣው ሳይታክቱ የእግዚአብሔርን ፊት በመፈለግ በጾም ጸንቶና ተግቶ በጌታ ፊት በመሆን በትግስት በእምነት እስከመጨረሻው ጌታን በመጠባበቅ የሚገኝ ድል ጉብኝት አለ
አንዳንዱ የጸሎት መልስ መፍትሄ የሚመጣው ሳይታክቱ የእግዚአብሔርን ፊት በመፈለግ በጾም ጸንቶና ተግቶ በጌታ ፊት በመሆን በትግስት በእምነት እስከመጨረሻው ጌታን በመጠባበቅ የሚገኝ ድል ጉብኝት አለ
እግዚአብሔር የታደገን ሊመራን ቢሆንም፣ እኛ አማኞች ደግሞ በእርሱ ዓላማና ሐሳብ የተያዝንና እርሱን ለመከተል ፈቃደኛ መሆን አለብን፣ እግዚአብሔር ያለን ሰዎች ሆነን ግን ብዙ ጊዜ በራሳችን መንገድ እንሄዳለን በራሳችን ደግሞ ሁሉን ለማድረግ እንሞክራለን ሆኖም በአንድ ቦታ መዞር መጥመልመልና ድካምን ነው የምናተርፈው፣ ተስፋ የሚጣልበት እውነተኛው አምላክ እግዚአብሔር ሲመራን ግን እርሱ መንገድ በሌለበት መንገድ በጨለማ ውስጥ ደግሞ ብርሀን ይሆንልናል፣
መልአክና ሰው የተፈጠረው ለአምልኮ ስለሆነ ወንጌልም ወደ ሕይወት ካመጣን በኃላ ወደ አምልኮ ነው የሚያደርሰን፣ በትክክለኛ አምልኮ ከአምላካችን ጋር ስንገናኝ የእግዚአብሔርን ትልቅነት እያየንና እግዚአብሔር በስራው ጻድቅ መሆኑን እየተረዳን በምናልፍበት ሁሉ እርሱን ማመስገን እንጀምራለን፣ መርገማችንን ሽሮ የመንግስቱ ወራሾች ያደረገን አምላካችን እዚህ ምድር ላይ ያስቀመጠን ለመንግስቱ ስራ መሆኑ ሲገባን ዛሬ የምለምናቸው ነገሮች ያንሱብንና በምስጋና እንሞላለን፣ በምስጋና ደግሞ ብዙ ቀንበራችን ይሰበራል ብዙ ድልንም እንቀዳጃለን፣
እግዚአብሔርን በታሪክ ውስጥ ስናየው እምነታችን ይጨምራል፣ መንፈሳዊ ሰው የሚኖረው በእምነቱ ስለሆነ እምነታችን ሲያድግ አንዳንዴ እግዚአብሔር እየተናገረ ያለው ባዶ በሆነ ነገር ላይና ለሰው በማይመስል ነገር ላይ የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለማስተናገድ አንቸገርም፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለመበጥበጥ በሚመጣው ማንኛውም ነገር ባለመታወክ ፍቅሩንና ምህረቱን እያሰብን እግዚአብሔር የማያሳፍር አምላክ መሆኑንም በመረዳት፣ የሚታየውን የሚሰማውንና የምናስበውን ሳይሆን ጌታን ማየትና መስማት እንጀምራለን
Play Episode Listen Later Dec 28, 2021 13:38
ያደገ ሰው ወደ ውስጥ የሚያስገባውን እና ከውስጡ የሚያውጣውን በቃሉ እና በመንፍስ ቅዱስ ይመዝናል 1ኛ ቆሮ 2:13 2ኛ ነገ 13 ሐዋ 17:11-28
Play Episode Listen Later Dec 27, 2021 10:30
በመንፍሳዊ ህይወታችን ሰናድግ ፈረሃት አይገዛንም ዕብ 2:14-15 1ዮሐ 4:18 ኢሳ 8:13 መሳ 6:10 ራዕ 21:8
በንስሐ ወደ እግዚአብሔር እንደርሳለን፣ ጌታን እንደግል አዳኛችን አድርገን ስንቀበልና በሐጢያታችን ስንናዘዝ ጌታ ይቅር ይለንና ልጆቹ ያደርገናል፣ ዳግመኛ በእውነት ቃል ከማይጠፋው ዘር እንወለዳለን፣ ጌታን ካወቅን በኋላ ንስሐ ያልገባንበት ሐጢያት ካለ የእግዚአብሔር ለሆነው ነገር ጠንካሮች እንዳንሆንና በጉስቁልና እንድንኖር ያደርገናል፣ እግዚአብሔር ከሐጢያት ጋር ሕብረት ስለሌለው ከጌታ ጋር ህብረት እንዳይኖረንም ያደርጋል፣ ስለዚህ እራሳችንን ሁልጊዜ አየመረመርን በንስሐ የእግዚአብሔርን ፊት ልንፈልግ ይገባናል፣
ሰይጣን ደካማ ጎናችንን ያውቃል ነገር ግን ከዛ ውስጥ ጠንካራ ነገር ይወጣል። ይህ ጠንካራ ጎን የሚወጣው በሞትንበት ነው።
Play Episode Listen Later Dec 26, 2021 12:54
በህይወቱ ያደገ ሰው የሰማውን ቃል የመጠበቅ ብቃት አለው በአንጻሩ ያላደገው ሰምቶ የመጠበቅ ብቃት የለወም ሕዝ 3:10 ሉቃ 8:13-15 2ኛ ጢሞ1:14 ራዕ 3:3 ኢዮ 20
ጠላት ይከሳል ነገር ግን የሚሰምርለት ከውስጥ ከአካል ተባባሪ ካገኘ ብቻ ነው። ምክንያቱም ጌታ የቅዱሳን ክስ ስለማይሰማ። ይህም ፀጋን ብቻ እንድንመለከት ነው።
Play Episode Listen Later Dec 25, 2021 10:53
ሰው እግዚያብሔርን ተስፍ ካደረገበት በላይ የህይወት አቅም የለውም ሮሜ 8፡24 ሮሜ 8:12 ዘፍ 13:10
ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፣ ክርስቶስን የሚያውቅና የእርሱ ተከታይ የሆነ እማኝ ዋነኛው የባህሪው መገለጫ ፍቅር ሊሆን ይገባል፣ ጌታ እየሱስ እንኳን አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው ከሕግ የትኛይቱ ትእዛዝ ታላቅ እንደሆነች ሲጠይቀው የመለሰው መልስ፣ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍሥህም በፍጹም አሳብህም ውደድ ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም ባልንጀራህን እንደ ነፍሥህ ውደድ የምትለው ናት ብሎ ነው፣ እንግዲህ በዚህ ፍቅር ለማደግ የመጀመሪያው ይቅር ማለት ሲሆን በመቀጠል ፍቅርን መከታተልና ከቅዱሳን ጋር ጤነኛ ህብረትን በመፍጠር ልንገለጽ ይገባናል፣ ክርስቶስ በምን ያህል ፍቅር እንደወደደን ሲገባን ሌሎችን ለመውደድ አንቸገርም፣
የእግዚአብሔር የሆነው ሁሉ መንፈሳዊ ነው፣ አኛ አማኞች ቃሉን ሆነን የምንገኘው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው፣ ያለመንፈስ ቅዱስ የክርስቶስን ሙላት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለስዎች ማድረስ አንችልም፣ ይህንን መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ካልታዘዝን፣ ህሊናችን ንጹህ ካልሆነና ካልተጠማን መሞላት አንችልም፣ ጌታችን እየሱስ እራሱ ከመታዘዝ ጋር አያይዞታል፣ ትዕዛዛቱን ሁሉ ጥለን መንፈሱን መፈለግ አንችልም፣ ትዕዛዛቱን መጣል ማለት እታድርጉ የተባልነውን ማድረግና አድርጉ የተባልነውን ደግሞ አለማድረግ ነው፣
Play Episode Listen Later Dec 24, 2021 10:49
ሰው እግዚያብሔርን ተስፍ ካደረገበት በላይ የህይወት አቅም የለውም ሮሜ 8፡24 ሮሜ 8:12 ዘፍ 13:10
እግዚአብሔር መልካም ስለሆነ ለህዝቡ ለመልካም ቀን ይቀጥራል። እኛ ግን በመታመን መጠበቅ አለብን። እግዚአብሔር ካለን ይልቅ ሁኔታን አይተን መናወጥ የላብንም። እስራኤል እግዚአብሔርን ከመስማት ይልቅ ጠላት የሚላቸውን ይሰሙ ስለነበር በምድረብዳ ቀርተዋል። እኛም ከጥርጠና ፍርሀት ሀሳባችንን መጋረድ እለብን። በዚህ ክፍል ውስጥ ይህንን በስፍት እንማራለን።
ያደገ ሰው በጽጋ ይኖራል ሮሜ 7 ሮሜ 6:14 ሮሜ 6:11 ራዕ 12:10
Play Episode Listen Later Dec 22, 2021 11:07
ለሰዎች መሆን ክርስቶስን መምሰል ሲሆን ዋጋ ያስከፍላል ዘኍ 16:45 ኢያ 3፡13 ዘኍ 16፡41
ያደገ ሰው ጦር እቃው ምንድን ነው? ያላደገስ? 2ኛ ቆሮ 10 1ኛ ጵጥ 3
Play Episode Listen Later Dec 20, 2021 12:09
ባደገ ሰው ውስጥ ከሚታዮት ባህሪዎች ውስጥ ለሌሎችህ መስጠት ለራስ ከማድርግ በላይ ያስደስተዋል ዕብ 13:16 ሉቃ 6:38
በእኛ መልካምን ስራ የጀመረው ልኡል እግዚአብሔር ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በህይወታችን የሚሰራው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው የታመነ አምለክእ ነው
የቤርያ ሰዎች ልበ ሰፊዎች ነበሩና ነገሩ እንደዚሁ ይሆንን ብለው ዕለት ዕለት መጻሕፍትን እንደመረመሩ እንደ እግዚአብሔር ቃል ሆኖ ሲያገኙት ደግሞ ቃሉን በሙሉ ፈቃድ እንደተቀበሉ አማኝ ከቃሉ ጋር የሚንሰማውን ሁልጊዜ ማመሳከር አለበት
Play Episode Listen Later Dec 19, 2021 11:28
ክርስትያን የሚያድገው የፈርሰውን ያህል ነው ያደገ ሰው ይሰማል ምሳ 1:32-33 ሮሜ 10:10
የዛሬ ጥያቂዎች 1. ነፃ የወጣ ሰው ነው ለእግዚአብሔር የሚሆነው ይህ ደግሞ እድገት ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 2. ጌታን ስንቀበል በመንፈስ ቅዱስ ታትመናል ልጅ ለመሆን ግን ገና መንፈስ ቅዱስ አልተሞላንም የሚለው ሀሳብ አብራራልን። 3. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚሄደው ከመታዘዝ ጋር ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. በመዳን ውስጥ ትልቅ ትንሽ የለም ወደ መንፈስ ቅዱስ ሙላት ስንመጣ ለእያንዳንዱ የተለያየ መለእክት አለው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ የአሸናፊነት አቅም የሚኖረው ህይወታችን ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
Play Episode Listen Later Dec 18, 2021 13:16
ወዳጅነታችን እንደ ክርስቶስ ባህሪ የሆነ የማይለዋወጥ መሆኑ ማደጋችንን ያሳያል ምሳ 11:17
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ሳምሶን የተቀባ አመንዝራ ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። እግዚአብሔር የቀባው ሰው እንደ ሳምሶን ዐይነት ህይወት ነው የሚባለው ምን አይነት ሲሆን ነው? 2. የቃሉ ሙላት የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 3. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከሌለ ለልጆቻችን ወንጌል ማድረስ አንችልም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። ወንጌል ሰምተው ሰዎች ወደ መዳን የማይመጡት ለዚህ ነው ማለት ነው? 4. ጌታ እየሱስ 30 ዓመት ለማገልገል መንፈስ ቅዱስ ስላልተሞላ ነው ወይስ ግዜው ስላልደረሰ? 5. ቃሉ ክርስቶስ ስለሆነ ቃሉ የሌለው ሰው ደስታ የለውም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
ሐዋርያት አንድ ላይ በመሆን ይተናነጹ ነበር፣ ዛሬም በዘመናችን ቤተ ክርስቲያን እንድትናነጽ አንዳችን ለአንዳችን መጸለይ የወንድማችን ወይም የእህታችን ነገር ተስምቶን ልንሸካከም ይገባናል፣ እንዲሁም የእግዚኣብሔርን እውነት እየገለጽን በመካከላችን ያለ እውቀት ያሉትን በቃሉ እግዚአብሔርን ወደማወቅ እንዲደርሱ ማስተማር፣ እርስ በእርስ በመዋደድና በመከባበር አብረን የሰማዩን መንግስት እንደምንወርስ ሁልጊዜ ማሰብ ያስፈልገናል
Play Episode Listen Later Dec 17, 2021 9:17
ያደገ ማንነታችን ክርስቶስን በመምሰል ሲገለጥ ባላደገው ማንነታችን ደግሞ ስጋችን ይገለጣል ምሳ 20:22 1ኛ ጵጥ 3
እግዚአብሔር ለቃሉ የታመነ ነው፣ እርሱ እስራኤላውያንን ሊያድን ሲመጣ ለአባቶቻቸው የገባውን ቃል ነበር የሚያመለክታቸው፣ የእምነት አባቶችም የተስፋይቱን ምድር እንደሚወርሱ የተናገራቸው አምላክ እግዚአብሔር ታማኝ መሆኑን ተቀብለው ምድሪቱን እንደሚወርሱ አምነው ነው የሞቱት፣ አንዳንድ ጊዜ መከራው በዝቶብን አልፈን ማየት ቢከብደን እንኳን እግዚአብሔር አደርጋለሁ ያለውን የሚያደርግን ምንም የማያቆመው ታላቅ አምላክ መሆኑን ልናምን ያስፈልገናል፣ Activity
ያደገ ሰው ለሚወስነው ውሳኔ ሁሉ የእግዚያብሔርን ሃሳብ የሚጠይቅ ሰው ነው ያላደገ ስው ግን ስዎች የሚሉትን ብቻ ይሰማል 1ኛ ሳሙ 14:36 ሮሜ 8:14 መሳ18:5-
ክርስትና በጨለማ ላለው ሕዝብ የሚመሰከው በመኖር ነው፥ ጌታ በቃሉ ስያስተምር፤ መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ ብሎዋል፣ ጌታ ሐዋርያትን በአፍ ከመመስከራቸውና ከመስበካቸው በፍት ክርስትናን ነረው እንድያሳዩ ነው የፈለገው፥ ክርስትና ኖረን በሕይወታችን የሚታይ መሆን አለበት፣ የጌታም ክብር ጎልቶ የሚታየው ያኔ ነው
ኃጢያት ወደ ዓለም ሲመጣ ውርደት ይዞ ነው የመጣው፣ አዳምና ሕዋን ኃጢአትን በሰሩ ጊዜ ከእግዚአብሔር መንግሥት ጎሎዋል፣ውርደትን ለብሰዋል፣ መንፈሳዊ ውድቀት የሆነው በሰው ሕሊና፣ በሰው ልብ፣ በሰው አስተሳሰብ፣ በሰው አመለካከት ውስጥ ነው፥ ጌታ ኢየሱስ ስጋ ለብሶ ወደ ምድር የመጣው በኃጢያያት ምክያት ከአግዚአብሔር መንሥት የተለየውን የሰው ልጅ ወደ ክብሩ ለመመለስ ነው፤ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ ብሎ በቃሉ እንደ ተናገረ አምነው ለተከተሉት የሕይወት ተድሶ ለማድረግ ነው
አማኝ ከሁሉ በላይ የሚያስመካው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አብሮነትና መገኝት ብቻ ነው እግዚአብሔር በምህረቱና በቸርነቱ በህይወታችን ከሚያደርገው በጎነቱ የተነሳ የጊዜውን ነገር ብቻ እየተመለስ የምንኖር ሳይሆን በእምነት እንድናድግ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው
ያደገ ሰው የውስጡን ንጽህና ግድ ይለዋል ያላደገ ሰው ደግሞ ስው የሚያየው የውጭው ማንነቱ ግድ ይለዋል መዝ 51:10 ዘፍ 6:5 ዘፍ 8:21 ማቴ 5:8
እምነት ማለት በእግዚአብሔር ዘንድ የሚደረግልንን አይናችን ሳያይ ጌታ በተናገረን ውስጥ ሆነን ሁሉን ለርሱ በመተው እንደሆነልን እንደተደረገልን አምነን በሰላሙ ውስጥ ማረፍ ነው
በጌታ ያደገ ማንነት እና ያላደገ ማንነት ገላ 4 ሉቃ 11:5-13 ዕብ 4:16
ያደገ ሰው ፀሎት እና ያላደገ ሰው ፀሎት መዝ 32:6 ኤር 2:27 ሉቃ 22:46 መዝ 11
እግዚአብሔር ያለውን የምንሆነው በመለኮት ጥበቃ ውስጥ እንዳለን አይናችን ሲበራ ብቻ ነው፣ ያለዚያ እንታወካለን፣ ለፈቃዱ ወይም ለተጠራንበትም መኖር አንችልም፣ አይናችን ሲበራ ግን እራሳችንን ከሐጢያት የምንጠብቅበት ወይም ክፉውን የምንጸየፍበትና እግዚአብሔርን በመፍራት የምንኖርበትን ማስተዋልና ጥብብን የተቀበልነው ከመለኮት መሆኑን እንረዳለን፣ በእርሱም አርፈን እንኖራለን
ሰማያዊ ዜግነትን ሰው የሚያገኝው ወንጌልን ሰምቶ ሲያምን ብቻ ነው ወንጌል ሁሉም አካል የሚሰራው ስራ ሲሆን አንዱ በመሄድ ሌላው በጸሎት በገንዘብ በሚያስፈልገው ሁሉ ይህን የምስራች በማድረስ ሰዎች ሲድኑ ደስ መሰኝት ለተቸገሩ መድረስ ነው
የውስጥ ጥማት ካለ ለኔ አይሆንም የምንለው ምንም ነገር የለም፣ እግዚአብሔር ዘኪዮስን በጊዜው እንደጎበኘው፣ እኛ ክርስቶስን ለማግኘት ፍላጎትና ጥማት ይኑረን እንጂ ጌታ ማንንም አያሳፍርም፣ እርሱን ለማየት ብዙ ነገሮች በዙሪያችን ቢጋርዱን እንኳን የልባችንን መሻት የሚያውቅ አምላክ እግዚአብሔር በጊዜው በዙሪያችን ከጋረዱን ነገሮች አልፎ ወደእኛ ይመጣል
እግዚአብሔር በማእበል በወጀብ ውስጥ መንገድ አለው ክብሩን ለመግለጥ እምነታችንን ለመጨመር እንባችንን ለመጥረግ የጎበጠ ነገራችንን ቀና ለማድረግ ለማስጣል ለማዳን ለመባረክ መንገድ አለው
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 31፡11 መንፈስ ቅዱስን የሚያሳዝን ሰው ይለፋል ፍሬ የለውም የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. መዝሙር 53፡1 የሚጸጸት ህይወት ከሌለን የንስሀ ፍሬ የለንም የሚለው ሀሳብ አብራራልን። 3. ምሳሌ 16 ለትውልድ የምናተርፈው ነገር ምንድን ነው? 4. ምሳሌ 31፡17 የውሳኔ ሰው መሆን ያስፈልገናል የውሳኔ ሰው ያልሆነ ግን ህይወት አደጋ ላይ ነው ያለው ለእርሱ ብቻ ሳይሆን በአካባቢው ላሉ ጭምር መሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 5. ወደ እግዚአብሔር ስቀርብ እንደ ማይገባው ሰው መኦን አለበት የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 6. ምሳሌ 31፡18 አመስጋኝ ሰው መብራቱ አይጠፋም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 7. የአንዳንድ ሰው መብራት የሚታየው በቀን ብቻ ነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። ይህ ብርሀን በቀን ብቻ እንደሚበራልን በማታ እንደማይበራ እንዴት ነው የምናውቀው? 8. 2ኛ ነገሥት 8 እግዚአብሔር የሚያየን ቃሉን እንዴት እንደ ተቀበልን ነው እንጂ ምን እንዳደረግን አይደለም የሚለው ሀሳብ ይብራራልን።
የዛሬ ጥያቄዎች 1. የጌታ ወዳጆች ሀጢያተዮች ነበሩ የእኛስ ወዳጆች እነማን ናቸው? 2. እግዚአብሔር በተለያየ ጎዳና ሊያገኘን ይችላል። ጸሎታችንንም ሊመልስ ይችላል ነገር ግን ያልተገኘ የህይወት ክፍል ሊኖረን ይችላል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 3. ማቲዮስ 3፡16-17፤ 4፡1 ለእግዚአብሔር ለመገኘት ከጥምቀት በሗሏ በመስቀል ህይወት ማለፍ አለብን ወይ? 4. መኋልየ መኋልይ 4፡12 ምንጩን የምንደፍነው ራሳችን ነን ነገር ግን እግዚአብሔር ይከፍተዋል የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 5. በህይወታችን ቅጣት ሲመጣ እንዴት ነው የምናውቀው? ይህንን እኛ ነን ወይስ ሌሎች ናቸው የሚይውቁት? ቅጣትስ ለምንድን ነው የሚመጣው? 6. 1ኛ ጥሞቴዎስ 2፡15 ይብራራልን። ምሳሌ 31፡15 ማለዳ የሚለው ግዜን ነው ወይ የሚያመለክተው? 7. ምግብ አብልታ ወደ ተግባር ታሰማራቸዋለች የሚለው ሀሳብ ቢብራራልን? 8. ኤፌሶን 2፡5 በአደገ ማንነታችን ጸጋን የምንፈልገው ከሀጢያት ለመላቀቅ ነው ይላደገው ማንነታችን ግን ጸጋን ለመሸፈን እንፈልገዋለን ይህንን ወደ እኛ ህይወት አምጥተ አብራራልን።
የጥሞና ሕይወት የተለማመዱ ስዎች የእግዚአብሔርን ቅድስና ይለማመዳሉ የቅድስናውን ሕይወት ይካፈላሉ ከብዙ ነገር እራሳቸውን ይጠብቃሉ። ቅድስና ከእግዚአብሔር የምንካፈለው ነው በራሳችን ይምናመጣው አይድለም፤ መጽደቅ አንድ ግዜ ነው፡ ቅድስና ግን እለት እለት ይምንለማመደው ነገር ነው፤ ጽድቅ የተገለጠው በጌታ በእየሱስ ክርስቶስ ነው።
እግዚአብሔር ያለውን የሚያደርግ ሉአላዊ አምላክ ነው ቅንነት ፊቱን ታየዋለች እግዚአብሔር መግቢያው የቀና ልብ ነው በረከቱ ወደ እኛ የሚመጣው በመታዘዝ ነው
ከሰማይ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ህይወታችንን ኑሮአችንን ዛሬንና ነገአችንን ያቀናል ጌታ አስቀድሞ በህይወታችን በተናገረው ውስጥ እናልፋለን መልካሙን ገድል እንጋደላለን
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ጌታ የሰጠን ፍቅር እሱን ብቻ እንድንወድ ሳይሆን የእርሱ የሆኑትን ጭምር እንጂ የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 2. የእርሱ የሆኑትን መውደድ የምንቸገረው ለምንድን ነው? 3. 1ኛ ቆሮንቶስ 1፡4 ያደገ ሰው በሞተ ፍቅር ላይ ህይወትን ይዘራር የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 4. የእግዚአብሔር እረፍት በእኛ የሚሆነው እሱ በአለን ውስጥ ስንገኝ ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን። 5. ራሳችንን እግዚአብሔር በተናገረን ካላየን መስኮት እንደሌለው ቤት ነው የምንሆነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን። 6. ዮሐንስ 5፡5 መንፈሳዊ ነገር ስንሆን አስመስለን የምንለው ነገር አለ እና ይህ ይብራራልን። 7. መኋልየ መኋልይ ዘሰለሞን 4፡12-16 የመከራ እና የድርቀት ንፋስ ካለመጣ ነገራችን አይከፈትም ወይ?
የዛሬ ጥያቄዎች 1. ምሳሌ 30፡11-12 በወላጆቻቸው የተጎዱ ልጆች የእግዚአብሔር በረከት እንዲያገኛቸው እንዴት ነው እንደዚህ ዐይነት ልጆችን ማገልገል የምንችለው? 2. በግልፅ የሚደረግ ፀሎትና በስውር የሚደረግ ፀሎት ብታብራራልን? እንዴት ነው እንደዚህ ዐይነቶች ፀሎት መፀለይ የምንችለው? 3. ምሳሌ 31፡1-5 ልጅን በማሳደግ ውስጥ ልጆች በሚያልፉበት መንገድ የወላጆች ድርሻ በተመለከተ ምን ትመክረናለህ? 4. ከውጪ ያየነውንወደ ቤተ ክርስትያን ስላመጣነው ምን ትመክረናለህ? 5. ምሳሌ 31፡13 በማጉረምረም እና በማረም ላይ ልጅን በማሳደግ ላይ ያለው ልዩነት ምንድን ነው?
የቤተክርስቲያን ዋና ተልዕኮ የእግዚአብሔርን በጎነት መናገር፣ መንፈሳዊ ቤት ሆኖ መሰራትና መንፈሳዊ መስዋዕትን ማቅረብ ነው፣ ታላቁ ትዕዛዝ ደግሞ አምላካችንን በፍጹም ልባችን ነፍሳችንና ሃሳባችን መውደድና ባልንጀራችንን ደግሞ እንደራሳችን መውደድ ነው፣ ጌታን መውደዳችንን የመንገልጸው ከአላማው ጋር በመተባበርና ለቃሉ በመታዘዝ ሲሆን በምድር ሲያስቀምጠን ትልቁ አላማው ደግሞ ወንጌልን ለፍጥረት ማድረስ ነው፣ ባልንጀራችንን እንደራሳችን እድርገን መውደዳችንን የምንገልፀው ለባልንጀራችን መልካም ነገርን በማድረግ ሲሆን ሰውን ሁሉ ወደ ዘለአለም ህይወት ከመምራት የበለጠ ደግሞ ምንም መልካም ነገር የለም፣ አማኞች ለዚህ ታላቅ ተልዕኮ ሁልጊዜ የተጋን እንድንሆን ጌታ ይርዳን፣
የጥሞና ጊዜ በእግዚአብሔር ላይ የማረፍ ህይወት ነው የጥሞና ጊዜ የለመዱ ሰዎች ፊቱን ይናፍቃሉ በእግሩ ስር መሆን ይወዳሉ ደስታና እረፍት በመንገዳቸው ነው አይናወጡም ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ስር ናቸው
የአንድ አማኝ መንፈሳዊ ሀብቱ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ራስን በእግዚአብሔር ቃል ተስፋ በመለኮት ሀሳብ ውስጥ ማግኘቱ ነው
In order to claim this podcast we'll send an email to with a verification link. Simply click the link and you will be able to edit tags, request a refresh, and other features to take control of your podcast page!
An email is on the way to from mike@ivy.fm with a verification link. Simply click the link and you will be able to edit tags, request a refresh, and other features to take control of your podcast page!