Listen to interviews, features and community stories from the SBS Radio Amharic program, including news from Australia and around the world. - የአውስትራሊያና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን አካትቶ፤ ቃለ ምልልሶችን፣ ዘገባዎችንና የማኅበረሰብ ታሪኮችን ከኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ ፕሮግራም ያድምጡ።

በሥርዓተ ትምህርት፣ የሴቶችና መድብለ ባሕል ተኮር የሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ምርምራቸውን በሀገረ እንግሊዝ ኤክስተር ዩኒቨርሲቲ እያካሔዱ ያሉት ወ/ት ናዲያ ሞናያ፤ ከፊል የምርምር ግኝቶቻቸውንና ፖሊሲ ነክ ጉዳዮችን አንስተው ያስረዳሉ።

በዩኒቨርሲቲ Exeter የሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ተማሪ ናዲያ ሞናያ፤ ምርምራቸው ስለሚያተኩርበት ለውጥ የሚያሻቸው የሴቶች ጉዳዮችና የመድብለ ባሕል ፋይዳዎችን አንስተው ያናገራሉ። ከግጥም ሥራዎቻቸው በቅርቡ "I Hugged a Tree" በሚል ርዕስ ለአባታቸው ዝክረ መታሰቢያ ከፃፉት የስንኝ ቋጠሯቸው በቅንጭቡ ያስደምጣሉ።

ናዲያ ሞናያ - በሀገረ እንግሊዝ ኤክስተር ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ተማሪ ናቸው። ውልደትና ዕድገታቸው አዲስ አበባ ነው። የኢትዮጵያዊት፣ ኤርትራዊትና ጣሊያናዊት ዝንቅ ብሔራዊ ማንነትን አጣምረው ይዘዋል። ሁለት ሀገርኛና አምስት የውጭ ሀገራት ቋንቋዎች ተናጋሪ ናቸው። የውልደት፣ ዕድገትና የትምህርት ሕይወታቸውን ነቅሰው ያጋራሉ።

የአውስትራሊያ ከተሞች የራሳቸውን የነዳጅ ክምችት ለርመፍጠር ቅድመ ዝግጅት ጀምረናል አሉ

Workplace discrimination, gender-based violence and financial inequality—these are just some of the reasons why women need dedicated legal services. You don't have to navigate the legal system alone. In Australia, free legal services exist to advocate for vulnerable women in ways that are safe, confidential and culturally appropriate. - ሴቶች የተለየ የህግ ባለሙያዎች እንዲያስፈልጋቸው ከሚያደርጉት ምክንያቶች መካከል ፤ በስራ ቦታ የሚፈጸም መድልዎ ፤ ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃት ፤ በገቢ ላይ የሚደረግ ማበላለጥ የሚሉት ጥቂቶቹ ናቸው ፡፡ በአውስትራሊያ የህግ ተቋማትን ብቻዎትን ማፈላልገ አይጠበቅብዎትም ፡፡ በችግር ላይ ያሉ ሴቶች ደህንነታቸ በተጠበቀ ሁኔታ ፤ ምስጢራቸው እና ባህላቸውን ባገናዘበ መልኩ ነጻ የህግ አገልግሎት አለ፡፡

በሱዳን ከ 21 ሚልዮን በላይ ዜጎች ለጽኑ ረሀብ እና የምግብ እጦት ተጋልጠዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ወኪል አስታወቁ

በኢትዮጵያ ከአንድ ሚሊየን በላይ ከደቡብ ሱዳን ፤ ኬንያ ፤ ኤርትራ እና ሶማሊያ የተፈናቀሉ ስደተኞች እንደሚኖሩ ተገለጸ

የነዳጅ ዋጋ መጨመርን ተከትሎ የኡበር አሽከርካሪዎች ደንበኞቻቸውን ተጨማሪ ዋጋ እንዲያስከፍሉ ደንብ ወጣ

መልአከ ፀሐይ መንግሥቱ ኃይሌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያ የምስራቅ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ አኅጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የብሪስበን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የበዓለ ትንሣኤን ትርጓሜ ያስረዳሉ። የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።

ወንጌላዊ የምሩ ታደሰ፤ በዘፀዓት የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን አገልጋይ፤ የፋሲካ በዓልን አስመልክተው የ ‘እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን' መልካም ምኞት መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።

ወ/ሮ ገነት ቤተ ጌራወርቅ፤ በደብረ ብርሃን ከተማ የኤፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና በደብረ ብርሃን መጠለያ ቻይና ካምፕ ተጠላይ እናት ሩቂያ አሕመድ ስለ ተፈናቃዮች ሕይወት፣ በደቡብ አውስትራሊያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር አስተባባሪነት ሁለት ወላጆቻቸውን ላጡ ሕፃናት ስለተደረገላቸው ሰብዓዊ እርዳታ አንስተው ይናገራሉ። ልባዊ ምስጋናቸውንም ያቀርባሉ።

የደቡብ አውስትራሊያ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት ዶ/ር ለገሰ ጋረደው፣ የደቡብ አውስትራሊያ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት አቶ ጥላዬ ተከተልና አቶ መሐመድ በያን፤ እንደምን የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት ከወለጋ ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፖች ውስጥ ለሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖች ልገሳቸውን እንደቸሩ ይናገራሉ።

የአደራ ቃል "አውስትራሊያ ላላችሁ ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፤ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን ከልባችሁ አታውጡ። ምንም ይሁን ምን - እንደ ሀገር የሚሆን ነገር የለም" ድምፃዊ ተሾመ ምትኩ (ዳግም የቀረበ)

አንጋፋው ድምፃዊ ተሾመ ምትኩ፤ ገጣሚና ሙዚቃ ቀማሪም ነው። ከሙዚቃ ዓለም አዘላለቁ እስከ ስደት ሕይወቱ አንስቶ ያወጋል። (ዳግም የቀረበ)

የዩናይትድ ስቴትስ ኮንግረስ አባል ፕሬዚደንት ትራምፕን ኮንግረስ ከፕሬዚደንታዊና ከጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥነት ስልጣናቸው እንዲያነሳቸው ጥሪ አቀረቡ

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከ50 በላይ ሴቶች እንዲደፈሩና ከ100 በላይ ሰዎችም ለሞት እንዲዳደረጉ ምክንያት ነው ያለውን ተጠርጣሪ ሕገ ወጥ አዘዋዋሪ ትግራይ ክልል ሽሬ ከተማ ውስጥ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ

በወርኃ ማርች በአንድ ወር ውስጥ ብቻ በአውስትራሊያ ታሪክ ከፍተኛውን ሬኮርድ የያዘ የአዲስ ኤክትሪክ መኪና ሽያጭ ተመዘገበ

አውስትራሊያ ለተጨማሪ አንድ ወር የሚበቃ የነዳጅ አቅርቦት እንዳላት የፌዴራል መንግሥቱ አስታወቀ

ኢትዮጵያ በቡድን 20 ማዕቀፍ ስር ከቻይና ያለባትን ዕዳ መልሶ ለማዋቀር ከቻይና መንግሥት ጋር መግባባት ላይ መድረሷ ተነገረ

"አንዱ ዓላማችን ማኅበረሰቡን ማገልገል ነውና በአቅም ውስንነት የመንጃ ፈቃድ ለሌላቸው አንዲት ሴትና አንድ ወንድ ነፃ የመኪና መንዳት ስልጠና እንሰጣለን" ያሉት አቶ ግዛቸው መኮንን፤ የፍቅር ለማጅ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ ስለ ማሰልጠኛቸው የምሥረታ ዓላማና የአገልግሎት ዘርፎች ይናገራሉ።

ለወ/ሮ ሶስና ወጋየሁ፤ የጋሞ ሰርከስ ትምህርት ቤት መሥራችና የኢትዮ - ሰርከስ ኢንተርቴይንመንት ዳይሬክተር፤ ላቋቋመችው የጋሞ ሰርከስ ትምህርት ቤት በሜልበርን- አውስትራሊያ ሚሊኒየም ሃውስ የማኅበረሰብ ማዕከል የተካሔደ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ድጋፍ።

ፕሬዚደንት ትራምፕ የኢራን ጦርነት ለፍፃሜ መቃረቡን ገለጡ

Learn useful English for talking about animals, nature, and protecting wildlife. Practise everyday phrases for discussing threats to animals, expressing concern, and describing the environment. - ስለ እንሰሳት፣ ተፈጥሮና የዱር እንሰሳት ጥበቃ ጠቃሚ እንግሊዝኛን መናገር ይማሩ። እንሰሳት ላይ የተደቀኑ አደጋዎችን አስመልክቶ መወያየትን፣ ስጋትን ማመላከትና የተፈጥሮ አካባቢን የዕለት ተዕለት አዘቦታዊ አባባሎችን መግለፅን ይለማመዱ።

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፤ የዩናይትድ ስቴትስ፣ እሥራኤል፣ ኢራን ጦርነት ከሁለት እስከ ሶስት ሳምንታት ጊዜያት ውስጥ ሊያከትም እንደሚችል አመላከቱ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበቱ ወደ ነጠላ አሃዝ ዝቅ እንዳለ ገለጠ

አቶ ዘሪሁን ተከተል፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳያስፖራ ባንክ ክፍል ሥራ አስኪያጅ፤ ሰሞኑን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት መካከል የተካሔደውን የመግባቢያ ሰነድ ፍረማ ፋይዳዎችን አንስተው ያስረዳሉ።

የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኅን ባለስልጣን በአንድ ዓመት ውስጥ ከማኅበራዊ ሚዲያዎች በናሙና ከታዩ 32 ሺህ ይዘቶች መካከል ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑት የጥላቻና ሐሰተኛ መረጃዎች መሆናቸውን በጥናት መለየቱን አመለከተ

በኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ፀሐፊ፣ አዘጋጅ፣ ዳይሬክተርና መምህር ሶፎኒያስ ታደሰ፤ የኢትዮጵያን የፊልም ኢንዱስትሪ የዕድገት ደረጃና የአሠራር ሂደቶች ነቅሶ ያመላክታል።

በኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ፀሐፊ፣ አዘጋጅ፣ ዳይሬክተርና መምህር ሶፎኒያስ ታደሰ፤ በቅርቡ በአቦል ቴሌቪዥን ለታዳሚዎች ዓይነ ገብ ለመሆን የዕይታ መሰናዶው ስለተጠናቀቀለት ባለ 260 ክፍል ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ጭብጥ ቀንጭቦ ያጋራል።

ወ/ሮ ጌጤ ነጋሽ፤ በሀገር ቤት ጎሠኝነትን፣ በሀገረ አውስትራሊያ ዘረኝነትን እምቢኝ ያሉ፤ በኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በእጅጉ የኩራት ሞገስን የተላበሱ ናቸው። ልጃቸው ዕድሜው አምስት ዓመት ሊሞላ ደርሶ ሳለ የገጠመው የቀለም ልዩነት ያሳደረባቸውን ሥነ ልቦናዊ ሁከት እንደምን የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ፈውስ ሆኗቸው ከእነ ልጃቸው እንደተቋቋሙት ይናገራሉ። ያም አስባብ ሆኗቸው "አድዋና ሜልበርን" ያሏትን የስንኝ ቋጠሮ ያስደምጣሉ።

ወ/ሮ ወርቅነሽ ጥላሁን ካሳ (ቤዛ) ለሶስት ዓመታት ከማኅፀን ካንሰር ጋር ያካሔዱት ፍልሚያ አክትሞ ከእዚህ ዓለም በሕልፈተ ሕይወት ተለይተዋል። ባለቤታቸው አቶ አብርሃም ተዘራ፣ የቤተሰባቸው ወዳጅ አቶ ፍቅሬ (ራያ) ረታ እና የንስሃ አባታቸው መልአከ ፅዮን ቀሲስ እንግዳ ችሩ፤ የሜልበርን መካነ ሰላም ልደታ ለማርያም ወገብርኤል አስተዳዳሪ፤ የወ/ሮ ወርቅነሽን የሕይወት ዘመን አንስተው፤ ጥልቅ ሐዘናቸውን በመግለፅ ይዘክራሉ። የወ/ሮ ወርቅነሽ ጥላሁን ካሳ (ቤዛ) የቀብር ሥነ ሥርዓት ቅዳሜ ማርች 28 ቀን 2026 / መጋቢት 19 ቀን 2018 በወረቢ ቤተ መቃብር Corner Cemetery Rd & Railway Avenue 10:00 am ይፈፀማል።

የግሪንስ ፓርቲ አውስትራሊያ ያለ ፓርላማ ይሁንታ ወደ ጦርነት እንዳትገባ የሚደነግግ ሕግ እንዲኖራት ፓርቲያቸው ዳግም መጠየቁን አስታወቁ

በኢትዮጵያ የዩናይድ ስቴትስ ኤምባሲ ኢትዮጵያውያን የንግድና ጉብኝት ቪዛ አመልካቾች እስከ 15 ሺህ ዶላር የሚደርስ የማስያዣ ገንዘብ እንዲያሲይዙ የሚጠይቀው አሠራር ከመጋቢት 24 ቀን 2018 ጀምሮ ግብር ላይ እንደሚውል አስታወቀ

የዶሃ - ኳታር ነዋሪ ሰዓሊ ተሰማ ተምትሜ አሥራቴ፤ የእሥራኤል - ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ጦርነት በእሳቸውና በቤተሰባቸው፣ እንዲሁም፤ በኳታር ነዋሪ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት ላይ ስላሳደረውና እያሳደረ ስላለው ተፅዕኖ አንስተው ያስረዳሉ።

ኧን ዴቪ የFlying Fruit Fly Circus አርቲስቲክ ዳይሬክተርና ማርታ ቦረና የጋሞ ሰርከስ ትምህርት ቤትና የኢትዮ-ሰርከስ ኢንተርቴይንመንት ማዕከል ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል፤ ቅዳሜ ማርች 28 / መጋቢት 19 ስለሚካሔደው የድጋፍ እራት ፕሮግራምና የእገዛ ፋይዳዎች ይናገራሉ።

አውስትራሊያ ለአንድ ወር ያህል የሚበቃ የነዳጅ፣ ናፍጣና የአውሮፕላን ነዳጅ ክምችት እንዳላት አስታወቀች።

ወ/ሮ ሶስና ወጋየሁ፤ የጋሞ ሰርከስ ትምህርት ቤት መሥራችና የኢትዮ - ሰርከስ ኢንተርቴይንመንት ዳይሬክተር፤ ከጋሞ ሰርከስ ትምህርት ቤት እስከ እንጦጦ ፓርክ እያስገነባችው ስላለው የሰርከስ ማዕከል ተልዕኮዎችን አንስታ ትናገራለች። የአውስትራሊያ ጉብኝት ዓላማዋንም አስመልክታ ቅዳሜ ማርች 28 / መጋቢት 19 በሚሊኒየም ሃውስ የማኅበረሰብ ማዕከል 296 Nicholson St, Seddon ተገኝታ ታስረዳለች።

የሕግ ከለላ የላቸውም የተባሉ 8000 ኢትዮጵያውያን እሥራኤልን ለቅቀው ሊወጡ ነው

በ66 ዓመታቸው ከእዚህ ዓለም ለተለዩት የSBS ነባር ዜጎች አረጋዊትና የዊድጃቡል ዋይባል ሴት የሐዘን መግለጫዎች እየደረሱ ነው። ከማኅፀን ካንሰር ጋር ሲያካሂዱት የነበረው አጭር ፍልሚያ ቅዳሜ ማርች 21 / መጋቢት 12 ከቀትር በኋላ በሕልፈተ ሕይወት አክትሟል።

ሲስተር ሃሊ ሙዘይን የጤና ባለሙያ፣ የሬዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ፣ ደራሲ፣ አርታኢና የበጎ ፈቃድ አገልጋይ ናቸው። በተሰማሩባቸው መስኮች ትድግናን ስለሚሹ ሀገራዊ ጉዳዮችና የሙያ አስተዋፅዖዎቻቸው ይናገራሉ።

ሼህ አብዱራህማን ሐጂ ከቢር፤ በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ እስልምና ሃይማኖት ተከታዮች መሪ፤ የ2026 የኢድ አል-ፈጥር መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።

Learn useful English for talking about unusual or strong flavours. Practise everyday phrases for reacting to new foods, sharing opinions, and encouraging someone to try something new. - ያልተለመደ ወይም ወጣ ያለ ጣዕም ስላላቸው ምግቦች ለመናገር ጠቃሚ እንግሊዝኛን ይማሩ። አዲስ ምግቦችን አስመልክቶ ስሜትዎን ለመግለጥ ወይም አተያዮን ለማጋራትና ሰዎች አዳዲስ ነገርን እንዲሞክሩ አበረታች አዘቦታዊ አባባሎችን ይልመዱ።

በአውስትራሊያ የሜልበርን ነዋሪ ስለ ነበሩትና ከእዚህ ዓለም በሕልፈተ ሕይወት ስለ ተለዩት ወ/ሮ ዕሌኒ ብርሃኑ፣ ልጆቻቸው፣ እህታቸውና ወዳጆቻቸው ጥልቅ ሐዘናቸውን ይገልጣሉ። መልካም ሰብዕናቸውን አንስተው ይዘክራሉ። ቅዳሜ መጋቢት 12 / ማርች 21 ለወ/ሮ ዕሌኒ ብርሃኑ በደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን ከ7: 00 am ጀምሮ ፀሎተ ፍትሐት ይደረግላቸዋል። የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው በMaddingley General Cemetery, 67 Griffith St, Bacchus Marsh ይፈፀማል።

ፕሬዚደንት ትራምፕ አውስትራሊያን ጨምሮ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአጋርነት ለመሳተፍ ፈቃደኛ ያልሆኑ ሀገራት ላይ የሰላ ትችት ሰነዘሩ

የኢትዮጵያ የዲጂታል ግብይት ከ18 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር በላይ መሻገሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ኩባን በበላይነት ለመቆጣጠር እንደሚሹ ገለጡ

እሥራኤል ትልሟ ግቡን እስኪመታ የሊባኖስና ኢራን ጥቃቷን እንደምትቀጥል አስታወቀች

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 31 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ በአየር መንገዶች የማስፈፀም አቅም ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነ

ባደረባቸው ሕመም ምክንያት ከእዚህ ዓለም በሞት ስለ ተለዩት የሁለት መንታ ሴት ልጆች አባት አቶ ሩፋኤል ተሰማ፤ መልካም ሰብዕና እና ትውስታዎችን ነቅሰው የቅርብ ወዳጆችና የትግል አጋሮች በስንብት ቃሎቻቸው ይዘክራሉ።

አቶ በፈቃዱ ወለሎ፤የ Bef Homes Australia መሥራችና ባለቤት፤ ድርጅታቸው በምዕራብ አውስትራሊያ፣ ቪክቶሪያና ኩዊንስላንድ ስለሚሰጣቸው አግልግሎቶች ይናገራሉ። የመኖሪያና ሙዋዕለ ንዋይ ቤት ግዢና ሽያጭ መንገዶችን ያመላክታሉ።

አውስትራሊያ ለመቅረት ጥገኝነት ከጠየቁት ሁለት ተጨማሪ የኢራን የሴት እግር ኳስ ተጫዋቾች ውስጥ አንደኛይቱ ሃሳቧን ቀይራ ወደ ኢራን ልትመለስ ነው።