Listen to interviews, features and community stories from the SBS Radio Amharic program, including news from Australia and around the world. - የአውስትራሊያና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን አካትቶ፤ ቃለ ምልልሶችን፣ ዘገባዎችንና የማኅበረሰብ ታሪኮችን ከኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ ፕሮግራም ያድምጡ።
Learn how to talk about swimming in English. - Learn how to talk about swimming in English.
በአማራ ክልል በባሕላዊ መንገድ ግጭቶች የሚፈቱባቸው የባሕል ፍርድ ቤቶች ሥራ ጀመሩ
Learn how to talk about the night sky and stargazing. - Learn how to talk about the night sky and stargazing.
ድምፃዊ፣ ሙዚቃ ቀማሪና የዳንስ መምህር ቫሔ ታልቢያ፤ ስለማንነት ጥያቄና ስለ ወደፊት የሙዚቃ ሕይወት ትልሞቹ ይናገራል። "በኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ወደ አውስትራሊያ ተጋብዞ የመምጣት ዕድል ካለ ለእኔ በጣም ትልቅ ክብር ነው' ይላል።
የኢሬቻ መልካ 2018 / 2025 ክብረ በዓል እሑድ መስከረም 18 / ሴፕቴምበር 28 በ Wilson Botanic Park Berwick ሜልበርን ተከብሮ ውሏል። ታዳሚዎች የበዓሉን አከባበር አስመልክተው አተያዮቻቸውን ያጋራሉ። መልካም ምኞቶቻቸውንም ይገልጣሉ።
ቫሔ ቲልቢያን፤ ኢትዮጵያዊ - አርመንያዊ ድምፃዊ፣ ሙዚቃ ቀማሪና ለዓለም አቀፍ የዳንስ መድረክ የበቃ ነው። አርመንያን፣ ኢትዮጵያንና ድፍን አኅጉሪቱን አፍሪካን ወክሎ በ2015 ዩሮ-ቪዢን የሙዚቃ ውድድር ላይ ተሳትፏል። ኢትዮጵያ እንደምን ከጥንታዊቷ ምዕራብ አርመንያ ግድ ተሰኝተው ለለቀቁቱ ቤተሰቦቹ ከ120 ዓመታት በላይ መኖሪያ ብቻ ሳትሆን ሀገርም ለመሆን እንደበቃች ያወጋል።
ቫሔ ቲልቢያን፤ ኢትዮጵያዊ - አርመንያዊ ድምፃዊ፣ ሙዚቃ ቀማሪና ለዓለም አቀፍ የዳንስ መድረክ የበቃ ነው። አርመንያን፣ ኢትዮጵያንና ድፍን አኅጉሪቱን አፍሪካን ወክሎ በ2015 ዩሮ-ቪዢን የሙዚቃ ውድድር ላይ ተሳትፏል። ኢትዮጵያ እንደምን ከጥንታዊቷ ምዕራብ አርመንያ ግድ ተሰኝተው ለለቀቁቱ ቤተሰቦቹ ከ120 ዓመታት በላይ መኖሪያ ብቻ ሳትሆን ሀገርም ለመሆን እንደበቃች ያወጋል።
አውስትራሊያ ከእሥራኤል ጋር ያላት የመከላከያ ውሎች እንድታቋርጥ ዳግም ጥሪ ቀረበ
ኢትዮጵያ የአንድ ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ዕዳዋን በአዲስ መልክ እንዲያዋቅሩላት ፓሪስ ላይ እየተነጋገረች ነው
ወ/ሮ ቆንጂት ጥላሁን የብሬቭኸርትስ ኢትዮጵያ መሥራች እና ዳይሬክተር ፤ የብሬቭኸርትስ የቦርድ አባላት እና የበጎ ፈቃድ አገልጋዮች ማርታ ቦረና ፤ ወ/ሮ ብርቱካን ቢያድግልኝ እና ወጣት ጊፍቲ በቀለ 'ብሬቭኸርትስ ኢትዮጵያውያንን ለመርዳት በኢትዮጵያውያን የሚመራ ግብረ ሰናይ ድርጅት በመሆኑ ሥራችንን በተለየ ፍቅር ፤ የኃላፊነት እና ባለቤትነት ስሜት እንድንሠራ ምክንያት ሆኖናል' ይላሉ።
ወ/ሮ ቆንጂት ጥላሁን የብሬቭኸርትስ ኢትዮጵያ መሥራች እና ዳይሬክተር ፤ የብሬቭኸርትስ የቦርድ አባላት እና የበጎ ፈቃድ አገልጋዮች ማርታ ቦረና ፤ ወ/ሮ ብርቱካን ቢያድግልኝ እና ወጣት ጊፍቲ በቀለ ፤ ብሬቭኸርትስ ላለፉት አሥራ አንድ ዓመታት በኢትዮጵያ በድህነት ውስጥ የሚኖሩ ታዳጊ ሕፃናት እና ወጣቶችን በማስተማር የተሻለ ዜጋ እንዲሆኑ እያበረከተ ያለውን አስተዋፅዖ ይገልጣሉ። ብሬቭኸርትስ በተለይም በአውስትራሊያ የሚገኙ የበጎ ፈቃድ አገልጋዮችን በመጠቀም ለታዳጊ ሕፃናት እና ወጣቶች በርካታ እርዳታዎችን ማበርከቱን አባላቱ ያስረዳሉ። በቅርቡም በሜልበርን ከተማ እያዘጋጁት ስላለው ልዩ ዝግጅት ይናገራሉ።
የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠን ባለበት ረግቶ እንዲቆይ ወሰነ
ጌታእንዳለ ዘለቀ ነገራ፤ የልብ ሕመም ምርምር ሳይንቲስት ናቸው። በስኳር ሕመም አስባብ የሚከሰትን የልብ ድካም አስመልክተው ያቀረቡት የጥናታዊ ምርምር ግኝታቸው ከአሜሪካ የልብ ማኅበር የ Paul Dudley White International Scholar Award ተሸላሚነት አብቅቷቸዋል። ለሽልማት የበቁበትን የግኝት ውጤታቸውን ነቅሰው ያስረዳሉ። የስኳር ሕመምና የልብ ድካም ተያያዥነትን አስመልክተውም ማኅበረሰባዊ ምክረ ሃሳባቸውን ያጋራሉ።
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአዕምሯዊ ንብረት ወጣቶች ድርጅት ዓመታዊ የፈጠራ ሪፖርት ኢትዮጵያ ከ139 ሀገሮች 134ኛ ደረጃ ላይ ተመደበች
መጋቢ አእላፍ ቀሲስ በቃሉ ዳዊት በሜልበርን ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የደመራ እና የመስቀል በአል ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ አንድምታ አስረድተዋል ።
ዶ/ር ፀጋዬ ደግነህ፤ የምጣኔ ሃብትና አስተዳደር ባለሙያ፣ በጀርመን የመኪና ኩባንያ የዘላቂ ልማትና ብዝኅነት ሥራ አስኪያጅ፤ የኤሌክትሪክ መኪና፣ ስኩተርና ብስክሌት ለኢትዮጵያ ያለውን ጠቀሜታ ከጀርመንና ቻይና ተሞክሮ ጋር አያይዘው ያስረዳሉ።
ዶ/ር ፀጋዬ ደግነህ፤ የምጣኔ ሃብትና አስተዳደር ባለሙያ፣ በጀርመን የመኪና ኩባንያ የዘላቂ ልማትና ብዝኅነት ሥራ አስኪያጅ፤ ከነዳጅና ናፍጣ ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል መኪና ሽግግርን ፋይዳዎች በንፅፅሮሽ አንስተው ያስረዳሉ።
የኢሬቻ ክብረ በዓል አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት ኦቦ አብደታ ሆማ እና ኦቦ በንቲ ኦሊቃ፤ እሑድ መስከረም 18 / ሴፕቴምበር 28 በ Wilson Botanic Park Berwick ተከብሮ ስለሚውለው የኢሬቻ ክብረ በዓል ሥነ ሥርዓትና ሂደት ይናገራሉ። የአብረን እንታደም የጥሪ ግብዣም ያቀርባሉ።
አባቴ በእኔ ስኬት ውስጥ ታላቅ ስፍራ አለው ፤ ዩኒቨርሳል ሙዚቃ ያቀረበልኝን ውል ስፈርም በእነሱ ቅድመ ሁኔታ ስይሆን በእኔ ምርጫ የተሻለ ውል እንድፈርም የረዳኝ የአባቴን ምክር እና የሕይወት ፍልስፍና መስማቴ እና መከተሌ ነው ፤ ይለናል ሁለገቡ አርቲስት ድምጻዊ ፤ ገጣሚ ፤ አቀናባሪ ፤ ዲጄ እንዲሁም ድምጻዊ ሮፍናን ኒሪ ሙዘይን ነው ።
የመንፈሳዊ ሕይወትና የበጎ አድራጎት አገልጋይዋ ፓስተር ደሲ ባይሳ ከእዚህ ዓለም በሕልፈት ተሰናብተዋል። "አታልቅስ፤ ነገ ይነጋል" ነበር የመጨረሻ ቃሏ ያሉትን ታላቅ ወንድማቸውን ተክሉ ባይሳ አክሎ፤ ቤተስብና ወዳጆች ጥልቅ ሐዘናቸውን ይገልጣሉ። የፓስተር ደሲ የቀብር ሥነ ሥርዓት እሑድ መስከረም 18 / ሴፕቴምበር 28 ከቀኑ 2:00 pm በ Bulla Cemetery Lane, Bulla ይፈፀማል።
የሙዚቀኛ ውጤት የሚታየው በሚዚቀኛው ጥረት ብቻ ሳይሆን በማህበረሰቡ የአስተሳሰብ አቅጣጫ ነው ። አገር ሰላም ሲሆን ማህበረሰብ ሲራጋጋ የኪነጥበብ ባለሙያዎችም ጥሩ ስራን ይዘን መቅረብ እንችላላን፤ የሚለን የሙዚቃ ስራውን በአውስትራሊያ እያሳየ ያለው ሁለገቡ አርቲስት ድምጻዊ ፤ ገጣሚ ፤ አቀናባሪ ፤ ዲጄ እንዲሁም ድምጻዊ ሮፍናን ኒሪ ሙዘይን ነው ።
አንቶኒዮ ጉተሬዝ በጋዛ የእስራኤልን ወረራን ተቃወሙ
የኢትዮጵያውያን 2018 አዲስ ዓመት አከባበር በኬንሲንግተን ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ ሜልበርን አውስትራሊያ።
እስራኤል የፍርስጤማውያንን ነጻ አገር የመሆን ጥያቄ መቼውንም ቢሆን እውቅናን አልሰጥም አለች፤
" ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር የመፈለግ መብቷን እንደግፋለን" - የሶማሌው ፕሬዝደንት ሀሰን ሼክ መሀመድ
በሕይወት ዘመናቸው "ኤርትራውያን ጀግናዎች ናቸው፤ ጥሩ ተዋጊዎች ናቸው። ለኢትዮጵያ ደማቸውን አፍስሰዋል፤ በኢትዮጵያ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ ስር ወድቀዋል። "አንድነት ኢትዮጵያ" ብለው የሔዱ ናቸው" ያሉን የቀድሞው የሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት አዛዥ፣ የብሔራዊ ውትድርና መምሪያ ኃላፊና የ "ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር" መጽሐፍ ደራሲ ብርጋዲየር ጄኔራል ውበቱ ፀጋዬ ሰሞኑን ከእዚህ ዓለም ተለይተዋል። ዝክረ መታሰቢያ ይሆናቸውም ዘንድ ቀደም ሲል በወርኃ ኖቬምበር 2014 ያካሔድነውን ቃለ ምልልስ ደግመን አቅርበናል።
ወ/ት ገነት ማስረሻ፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበር ምክትል ፕሬዚደንት፤ ቅዳሜ መስከረም 10 / ሴፕቴምበር 20 በ Kensington Town Hall በማኅበሩ አስተባባሪነት ስለሚከበረው የ2018 አዲስ ዓመት ልዩ ዝግጅት ይገልጣሉ።
እስከ አንድ ወር ጊዜ ይወስድ የነበረውን አዲስ የንግድ ምዝገባና ዕድሳት አሠራርን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል በመቀየር በሁለት ቀናት መጨረስ የሚያስችል ሥርዓት ይፋ ተደረገ
የኢትዮ - አውስትራሊያ አንድነት ዕድር ሰብሳቢ አቶ መስቀሉ ደሴ፣ ፀሐፊ ብሩክ ይማ እና የበዓል አስተባባሪ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ይልማ፤ ቅዳሜ መስከረም 10 / ሴፕቴምበር 20 የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት 2018 እና የመስቀል በዓል በጣምራ ከኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ማኅበረሰብ አባላት ጋር በፐርዝ ከተማ Koondoola Community Centre ለማክበር ስላሰናዱት የበዓል ዝግጅት ፕሮግራም ይናገራሉ። የአንድነት ጥሪም ያቀርባሉ።
የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሔደው ጦርነት ሳቢያ በኢትዮጵያ ላይ ጥለውት የነበረውን የተለያዩ ዕቀባዎችን የያዘው ፕሬዚደንታዊ ትዕዛዝ፤ በፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ለተጨማሪ አንድ ዓመት ፀንቶ እንዲቆይ ተወሰነ
ዶ/ር ሰለሞን ኃይለማርያም፤ ስለምን የሶስተኛ ዲግሪ የመመረቂያ የምርምር ፅሁፋቸውን ከዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ አውጥተው "Ethiopian Elites' Political Cultures: a critical juncture: The cases of Amhara, Oromo and Tigray" በሚል ርዕሰ ስያሜ ለመፅሐፍነት ለማብቃት እንደወደዱ ያነሳሉ፤ ጭብጦቹንም ነቅሰው ይናገራሉ።
የ "Ethiopian Elites' Political Cultures: a critical juncture: The cases of Amhara, Oromo and Tigray" መፅሐፍ ደራሲ ዶ/ር ሰለሞን ኃይለማርያም፤ መፅሐፋቸው ውስጥ ያሠፈሯቸውን አንኳር ምክረ ሃሳቦች ፋይዳ ነቅሰው ያስገነዝባሉ።
ዶ/ር ሰለሞን ኃይለማርያም፤ "Ethiopian Elites' Political Cultures: a critical juncture: The cases of Amhara, Oromo and Tigray" በሚል ርዕሰ ለሕትመት ስላበቁት መፅሐፋቸው ዋነኛ ይዘቶች ይናገራሉ።
ዶ/ር ሰለሞን ኃይለማርያም፤ ስለምን የሶስተኛ ዲግሪ የመመረቂያ የምርምር ፅሁፋቸውን ከዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ አውጥተው "Ethiopian Elites' Political Cultures: a critical juncture: The cases of Amhara, Oromo and Tigray" በሚል ርዕሰ ስያሜ ለመፅሐፍነት ለማብቃት እንደወደዱ ያነሳሉ፤ ጭብጦቹንም ነቅሰው ይናገራሉ።
የ"ክብረ በዓላት፤ ሃይማኖትና ባሕል" መፅሐፍ ደራሲ መላኩ ጌታቸው፤ ስለ ኢትዮጵያ ታሪካዊ የዘመን ቅመራና ባሕላዊ አከባበር ያስረዳል።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አባልና በኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብክት ሊቀ ጳጳስ አዲሱ አመት የአንድነት ፤ የመተባበር ፤ የሰላም እና ፍቅር እንዲሆንልን እንጸልያለን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
ዶ/ር ናትናኤል ገመዳ - በዘፀአት የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ፓስተር፤ አዲሱ ዓመት ወደ እግዚአብሔር የምንጠጋብት እና የምንታደስበት እንዲሆን እፀልያለሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
ሼህ አብዱራህማን ሀጂ ከቢር በአውስትራሊይ የእስልምና እምነት ተከታዮች መሪ አዲሱ የ2018 አመተ ምህረት የፍቅር ፤ የመቻቻል ፤ የሰላም እና ከድህነት የምንወጣበት ይሁንልን ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።
የአውስትራሊያ ፌዴራል ተቃዋሚ ቡድን መሪ ሱዛን ሊይ፤ ለኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት አደረሳችሁ ሙሉ መልዕክት።
"አንድ ስንሆን፤ ሳንለያይ ብዙ መስራት እንደምንችል ይህ [ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ] ትልቅ ምሳሌ ነው። እግዚአብሔርም የግርማዊ ጃንሆይን ሕልም ተሠርቶ ስላሳየን ስሙ ምስጉን ይሁን" ልዑል ኤርሚያስ ሳህለ ሥላሴ ኃይለ ሥላሴ
አቶ ጉግሳ አሊጋዝ "ለኢትዮጵያውያን ሁሌም የአባቶች ቀን ነው። እኛ ጥሩ አባቶች ነን። ልጆቼን እጅግ በጣም ነው የምወዳቸው፤ በእዚህ ምድር ላይ በጣም ያስደሰተኝ ነገር ቢኖር ከልጆቼ ጋር ያሳለፍኩት ጊዜ ነው " ሲሉ፤ አቶ ኃይለማርያም ኃይለየሱስ በበኩላቸው "እግዚአብሔር በልጆች ባርኮኛል፤ ልጆቼን በፍቅር ነው ያሳደግኳቸው። የወላጅ ግዴታዬን ተወጥቻለሁ ብዬ አስባለሁ። ልጆቼም ለእኔ ትልቅ ፍቅርና አክብሮት አላቸው፤ የአባቶችን ቀን በጣም ደስ ብሎኝ ነው ያከበርኩት" ይላሉ።
አኑዋር ሙክታር፤ በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተጠባባቂ አምባሳደር፤ የ2018 የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት።
በሰሜን ጎንደር ዞን ድርቅ ስጋት ማስከተሉ ተመለከተ
ከኢትዮጵያውያን ማንንት መገለጫ አንዱ ልዩ የሆነ የቀን መቁጠሪያችን ነው ። ምንጩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ቢሆንም አገልግሎቱ ግን ለመላው ኢትዮጵያውያን ነው በዚህም ልንኮራ ይገባናል፤ የሚሉን መጋቢ ምስጢር ቀሲስ ስንታየሁ በምስራቅ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት የሜልበርን ምእራፈ ቅዱሳን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያ አስተዳዳሪ እንዲሁም መጋቢ ጥበብ ቀሲስ ቴዎድሮስ በሜልበርን ደብረገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አገልጋይ ናቸው።
መጋቢ ምስጢር ቀሲስ ስንታየሁ በምስራቅ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት የሜልበርን ምእራፈ ቅዱሳን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያ አስተዳዳሪ ፤ እንዲሁም መጋቢ ጥበብ ቀሲስ ቴዎድሮስ በሜልበርን ደብረገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የጳጉሜ ወር ትርጓሜን ፤ ሀይማኖታዊ እና አገራዊ ጠቀሜታን አስረድተውናል
Learn how to talk about Autism Spectrum Disorder respectfully. Understand common autism symptoms and use simple language to describe autism in everyday conversations. - Learn how to talk about Autism Spectrum Disorder respectfully. Understand common autism symptoms and use simple language to describe autism in everyday conversations.
ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበር ፕሬዚደንት፤ የ2018 የኢትዮጵያ አዲስ ዓመትን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።
አቶ ካሪም ደጋል፣ የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ክብረ በዓል አስተባባሪ ኮሚቴ ዳይሬክተር፤ አቶ ኃይለሰማዕት መርሃጥበብ፣ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበር ዋና ፀሐፊና የአዲስ ዓመት አስተባባሪ ኮሚቴ አባል፤ ወ/ሮ ማርታ ከበደ፤ የአዲስ ዓመት አስተባባሪ ኮሚቴ አባልና የመድረክ መሪ፤ በሜልበር ፉትስክሬይ ክፍለ ከተማ ቅዳሜ ሴፕቴምበር 6 / ጳጉሜን 1 በሚካሔደው የአዲስ ዓመት ቅበላ ልዩ ዝግጅት ላይ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች እንዲገኙ ይጋብዛሉ።
አቶ ካሪም ደጋል፣ የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ክብረ በዓል አስተባባሪ ኮሚቴ ዳይሬክተር፤ አቶ ኃይለሰማዕት መርሃጥበብ፣ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበር ዋና ፀሐፊና የአዲስ ዓመት አስተባባሪ ኮሚቴ አባል፤ ወ/ሮ ማርታ ከበደ፤ የአዲስ ዓመት አስተባባሪ ኮሚቴ አባልና የመድረክ መሪ፤ በሜልበር ፉትስክሬይ ክፍለ ከተማ ቅዳሜ ሴፕቴምበር 6 / ጳጉሜን 1 ስለሚካሔደው የአዲስ ዓመት ቅበላ ልዩ ዝግጅት ይገልጣሉ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዳያስፖራ ማኅበረሰብ 50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት አዘጋጅቻለሁ አለ
የትራምፕ አስተዳደር ፍልስጥኤማውያንን የቤት ኪራይ ገንዘብ ሰጥቶ ከጋዛ ለማስወጣት መወጠኑ ተጠቆመ