Listen to interviews, features and community stories from the SBS Radio Amharic program, including news from Australia and around the world. - የአውስትራሊያና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን አካትቶ፤ ቃለ ምልልሶችን፣ ዘገባዎችንና የማኅበረሰብ ታሪኮችን ከኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ ፕሮግራም ያድምጡ።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባለፈው አንድ ዓመት በሀገሪቱ በርካታ አሳሳቢ የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታዎች እንደተከሰቱ፤ በተለይም በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በመንግሥት ኃይሎችና ታጣቂ ቡድኖች መካከል የሚካሔዱ የትጥቅ ግጭቶች በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነትና የነፃነት መብቶች ጥሰቶችን እንዳስከተለ በዓመታዊ ሪፖርቱ አመለከተ።
"የቁንጅና ውድድር በቁንጅና ብቻ የተወሰነ አይደለም። ማኅበረሰባትና ኢንዱስትሪዎችንም ለማገናኘት እንደ ድልድይ የሚጠቅም ነው። ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን የምናነሳባቸው፤ ያልተሰሙ ድምፆችን የምናስተጋባበት ነው" የሚል አመኔታዋን ያነሳቸው ልዕለ ሞዴል ሩት ይርጋዓለም፤ ከወይዘሪት አዲስ አበባ እስከ ዓለም አቀፍ ወይዘሪት ልዕለ ሞዴልነት የቁንጅና ዘውድ ደፍታለች፤ በልዩ አልባሳት ተሽሞንሙና የፋሽን ትዕይንቶች ላይ ግዘፍ ነስታለች። ከራሷ አልፋም የሀገረ ኢትዮጵያን ስም በማለፊያነት አስጠርታለች።
የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚና የፍልስጥኤም ባልስልጣን ፕሬዚደንት ማሙድ አባስ በስልክ ተወያዩ - አውስትራሊያ 25 ሺህ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን በ2026 ልትቀበል ነው
ድምፃዊ ይሁኔ በላይ ከባሕዳር ዩኒቨርሲቲ ዕውቅና ተቸረው
ዩቲዩብን ጨምሮ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች በሆኑ አውስትራሊያውያን ታዳጊ ወጣቶች ላይ የማኅበራዊ ሚዲያ ተደራሽነት ዕገዳ ሊደረግ ነው
ከኢትዮጵያ ሕዝብ ግማሹ ለጤናማ አመጋገብ የሚያስፈልጉ ምግቦችን ለመግዛት የሚያስችል ምጣኔ ሃብታዊ አቅም የለውም ተባለ
የኢትዮጵያውያን ቢዝነስ ማኅበር መሥራችና ተሳታፊዎች ለሶስተኛ ጊዜ ሜልበርን ከተማ ውስጥ ስላካሔዱት የኢትዮጵያውያን ንግድ ማኅበረሰብ ውይይት ፋይዳዎች ይናገራሉ።
ከአምስት አንድ አውስትራሊያውያን የመብራትና ጋዝ ክፍያ ለመክፈል እየተሳናቸው እንደሁ አንድ አዲስ ሪፖርት አስታወቀ
የትምህርት ሚኒስቴር፤ ከኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች በከፍተኛ ማዕረግ የሚመረቁ ተማሪዎች የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ አስታወቀ።
Learn polite ways to request a job reference from managers or colleagues. - Learn polite ways to request a job reference from managers or colleagues.
የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር 135.3 ሚሊየን መድረሱን የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ሕዝብ ፈንድ 2025 ሪፖርት አስታወቀ
የአውስትራሊያ ሠራተኞች ማኅበር የአውስትራሊያ የሥራ ቀናት በሳምንት አራት ቀናት እንዲሆን ጠየቀ
የቀድሞው ጋዜጠኛ፣ ደራሲና ታጋይ የነበሩት ኦቦ ኩምሳ ቡራዩ ከእዚህ ዓለም በድንገት ተሰናብተዋል። የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ቅዳሜ ጁላይ 26 / ሐምሌ 19 በፐርዝ ከተማ ይከናወናል።
በኢትዮጵያ ከሚፀንሱ 100 ሴቶች መካከል 21ዱ ፅንሶቻቸውን ያቋርጣሉ
ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር፣ ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ፣ አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚና ቦርድ አባል፣ ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ በመቋጫ የመወያያ አጀንዳነት አማራጭ መፍትሔዎችን ያመላክታሉ፤ ምክረ ሃሳቦችንም ለኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር በቪክቶሪያ / የኢትዮጵያውያን ማኅበር በቪክቶሪያ ይቸራሉ።
ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር፣ ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ፣ አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚና ቦርድ አባል፣ ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ በተከታይ የመወያያ አጀንዳነት በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር / የኢትዮጵያውያን ማኅበር በቪክቶሪያ ያስፈልገዋል ወይስ አያስፈልገውም በሚል የመወያያ ነጥብ ላይ ግለ አመለካከታቸውን ያካፍላሉ።
ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር፣ ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ፣ አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚና ቦርድ አባል፣ ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ በተከታይ የመወያያ አጀንዳነት በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር / የኢትዮጵያውያን ማኅበር በቪክቶሪያ የገጠሙትን ተግዳሮችና ያስከተሏቸውን መዘዞች አስመልክተው ግለ አተያያቸውን ያንፀባርቃሉ።
ዶ/ር ቢቾክ ዋን፤ በቪክቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ መምህር፣ ደራሲ አዳሙ ተፈራ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፣ አቶ ዓለማየሁ በዛብህ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ዋና ፀሐፊ፣ አቶ አሕመድ ዳውድ፤ የቀድሞው በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚና ቦርድ አባል፣ ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የቀድሞው በታዝማኒያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ በቀዳሚ የመወያያ አጀንዳነት በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር የ38 ዓመታት ጉዞ በከፊል ነቅሰው ግለ አተያያያቸውን ያጋራሉ።
አውስትራሊያ እና ቻይና የፍራፍሬ ንግድ ስምምነትን ተፈራረሙ
የኢትዮጵያውያን የእድር መረዳጃ ማህበር በቪክቶርያ ባሳለፍነ ሰሞን አጠቃላይ የአባላት ስብሰባ ማድረጉ ይታወሳል ፡፡ የማህበሩ ሊቀመንበር ወ/ሮ ማህሌት ማስረሻ ፤ ወ/ሮ ቅድስት ሰለሞን ጸሀፊ እንዲሁም አቶ ዮናስ ደገፋ ገንዘብ ያዥ ፤ እድሩ ከነበረበት ተነስቶ በአሁን ሰአት ምን ደርጃ ላይ እንዳለ እና እና የወደፊት እቅዶቻቸውን በተመለከተ ሀሳባቸውን አጋርተውናል ፡፡
ከኢትዮጵያ ከሀምሳ አምስት እስከ ሰማኒያ በመቶ የሚሆነው ገንዘብ በህገ ወጥ ንግድ ሳቢያ ከአገር ወስጥ እንደሚወጣ የአፍሪካ ልማት ባንክ አስታወቀ፡፡
ወ/ሮ መሠረት አሰፋ፤ የ Habesha Spices and Events መሥራች፤ መጪውን የኢትዮጵያውያንን አዲስ ዓመት 2018 ቅበላና የኤርትራውያንን ቅዱስ ዮሐንስ በዓላት እንደምን በጋራ ድምቀትን በተላበሰ ሁኔታ ለማክበር መሰናዶ ላይ እንደሚገኙ ይገልጣሉ።
በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ጋሻው አንለይና በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ታጠቅ መንጂ፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ማኅበር መተዳደሪያ ደንብ አፈፃፀም፣ በቦርድ አስፈላጊነት እና አላስፈላጊነት ላይ ያሉ አተያዮችን አስመልክተው አቋማቸውን ያንፀባርቃሉ።
በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ጋሻው አንለይና በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ታጠቅ መንጂ፤ ከማኅበር እስከ ቦርድ ምሥረታ የነበሩ ሂደቶችንና በቦርድና የማኅበሩ የሥራ አስፈፃሚ አባላት መካከል ተከስተው ያሉ የሥራ ግንኙነቶች መሻከርን አንስተው ይናገራሉ። የመፍትሔ ሃሳቦችንም ይቸራሉ።
The representation of Indigenous Australians in media has historically been shaped by stereotypes and exclusion, but this is gradually changing. Indigenous platforms like National Indigenous Television (NITV) and social media are breaking barriers, empowering First Nations voices, and fostering a more inclusive understanding of Australia's diverse cultural identity. Learning about these changes offers valuable insight into the country's true history, its ongoing journey toward equity, and the rich cultures that form the foundation of modern Australia. Understanding Indigenous perspectives is also an important step toward respectful connection and shared belonging. - የአውስትራሊያ ነባር ዜጎች የሚዲያ ውክልና ታሪካዊ ተሞክሮው በጅምላ ፍረጃና መገለል የተቀነበበ ነው፤ ምንም እንኳ በዘገምታ በመለወጥ ላይ ያለም ቢሆን። እንደ ብሔራዊ የነባር ዜጎች ቴሌቪዥን (NITV) እና ማኅበራዊ ሚዲያ ያሉ መድረኮች ጋሬጣዎችን በጎን አልፈው፤ የነባር ዜጎችን ድምፆች እያሰሙና የአውስትራሊያን ዝንቅ ባሕላዊ ማንነት በላቀ አካታችነት እየታደጉ ይገኛሉ። ስለ እኒህ ለውጦች፤ የሀገሪቱን እውነተኛ ታሪክ ፣ ያልተቋረጠ የፍትሕ ፍለጋ ጉዞና የበለፀገው ባሕል እንደምን ለዘመናይቱ አውስትራሊያ መሠረት እንደሆነ ጥልቅ ግንዛቤን ለማስጨበጥ ጋባዥ ነው። የነባር ዜጎችን አተያዮች መረዳት ከበሬታን ወደ ተላበሰና የጋራ ጉድኝት ወደ አቆራኘ ጠቃሚ እርምጃ አምሪ ነው።
Learn how to describe people who inspire you. - Learn how to describe people who inspire you.
ቻይና የኢትዮጵያ አኩሪ አተር ምርቶች ወደ ሀገሯ እንዲገቡ ፈቃድ ሰጠች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስጋትን፣ ግጭትን፣ ጥርጣሬንና አለመተማመንን የሚፈጥር ድርጊት ፈፅመዋል ያላቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎች ከምዝገባ እንዲሰርዝ ስልጣን የሚሰጥ አዲስ የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ለፓርላማ ቀረበ
አቶ ዳንኤል አለማር፤ የጎጆ ካፌና ሬስቶራንት ባለቤት የቡናና ምግብ አቅርቦታቸው ለሽልማት የመጨረሻ ማጣሪያ ከቀረቡት 15 የሜልበር ምርጥ ካፌዎች አንዱ ለመሆን በመብቃቱ "የሬስቶራንቴ ስም 'ጎጆ የኢትዮጵያ ካፌ እና ሬስቶራንት'፤ ሀገርን ተሸክሞ ያለ ትልቅ ስም ያለው ነው። ሀገሬን በማስጠራቴ ትልቅ ኩራት ተሰምቶኛል" ሲሉ፤ እህታቸውና ሥራ አስኪያጅ መሠረት አለማር ፤ ሕልማቸው በዕጩነት ከ15 ምርጥ የሜልበርን ካፌና ሬስቶራንት ውስጥ አንዱ ለመሆን በመብቃት እንደማይገታ ይናገራሉ።
ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ ለሰኔ 29 / ጁላይ 6 በሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ለመላ የማኅበረስብ አባላት ስለቀረበው የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪና የመነጋገሪያ ዋነኛ አጀንዳዎች ያስረዳሉ።
የኢራን ፕሬዚደንት ኢራን ለዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጄንሲ ትብብሯን እንድትነፍግ የሚፈቅድ ሕግ አፀደቁ
የአውስትራሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ የአራትዮሹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ፍሬያማ ነበር አሉ
የሕወሓትን ክፍፍል ተከትሎ ለሁለት የተከፈሉት የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ወደ እርስ በእርስ ግጭት ሊያመሩ ነው የሚል ስጋት ተፈጥሯል ተባለ
ደራሲ ተሾመ ብርሃኑ ከማል፤ አዲስ ለሕትመት ባበቁት "ፕሮፌሰሮቹ" መጽሐፋቸው ስለምን ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ፕሮፌሰሮች ሙያዊ አስተዋፅዖዎች ላይ ለማተኮር እንደወደዱ ይናገራሉ።
በሥነ ጽሑፍ ሥራዎቻቸው 32 መፃሕፍትንና ከ2000 በላይ መጣጥፎችን ለአንባቢያን ያበረከቱት አንጋፋ ደራሲ ተሾመ ብርሃኑ ከማል፤ ሰሞነኛ ስለሆነው "ፕሮፌሰሮቹ" መጽሐፋቸው ተልዕኮና ይዘት ያስረዳሉ።
"በቤተ ክርስቲያንም ተከፋፍለን፣ በማኅበረሰብም ተከፋፍለን፣ በዘርም ተከፋፍለን ያሳለፍናቸው ምንም አልጠቀሙንም። አንድ ከሆንን፤ ከተባበርን፤ ከእዚህ በላይ መሥራት እንችላለን። ኅብረት የውስጥም የውጭም ጩኸቴ ነው!" አቶ ዳንኤል አለማር፤ በሜልበርን የዘፀዓት ኢትዮጵያውያን ወንጌላውያን ኅብረት አሠሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ
ኢትዮጵያን ጨምሮ 39 ሀገራት በግጭቶችና አለመረጋጋቶች ምክንያት የከፋ ረሃብና ድህነት ማዕከል እየሆኑ ስለመሆናቸው የዓለም ባንክ ባወጣው ይፋ ሪፖርት አመላከተ
ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን በሚቀጥለው ሳምንት የቀጥታ ሁለትዮሽ ውይይት ሊጀምሩ ነው
አማኑኤል የአዕምሮ ልዩ ሆስፒታል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ100 ሺህ በላይ ለሆኑ ተገልጋዮች የሕክምና አገልግሎት መስጠቱን ገለጠ
አቶ ዳንኤል አለማር ከዘጸአት የኢትዮጵያውያን ወንጌላውያን ህብረት የህንጻ አሰሪ ሰብሳቢ ፤ በሜልበርን ከተማ በመጪው ቅድሚ የሚመረቀው የቤተክርስቲያን ህንጻ ፤ ህብረተሰቡ ከሌለው አቅሙ ቀንሦ ለትውልዱ እና ለመጪው ትውልድ ያሳነጸው ሲሆን ፡ በህንጻ አሰሪው ኮሚቴው ስም ምስጋናዪን አቀርባለሁ ብለዋል ። አያይዘውም በምርቃቱ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲገኙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ።
የፈረንሳዩ ፕሬዚደንት ኢማኑኤል ማክሮን "ኢራን ውስጥ የሥርዓት ለውጥ ማድረግ ካስፈለገ በኢራን ሕዝብ እንጂ በቦምብ አይደለም" ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስን የሥርዓት ለውጥ ዕሳቤ ተቹ
በሳዑዲ ዓረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ 37 ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ይጠብቃቸዋል
በሺህዎች የሚቆጠሩ አውስትራሊያውያን ኢራንና እሥራኤልን ለቅቀው ወደ አውስትራሊያ ለመመለስ ተመዝግበዋል
አውስትራሊያ በሩስያ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦችን ጣለች
በወንጀል የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ በማስመሰልና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀሎችን የሚመረምሩ አካላት አስገዳጅ ሆኖ ሲገኝ ከግድያ በስተቀር ያሉ የምርመራ መንገዶችን የሚፈቅደውና አነጋጋሪ የሆነው አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ
Learn how to congratulate someone on their work or wedding anniversary. - Learn how to congratulate someone on their work or wedding anniversary.
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት አሜሪካ እንደምትደግፍ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር አስታወቁ
Learn how to ask for medical help when in an emergency department. - Learn how to ask for medical help when in an emergency department.
ኳንታስ የጄት ስታር እስያ በረራውን ገታ፤ የሲድኒ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጠናቀቀ
ፕሪሚየር ጀርሚ ሮክሊፍ ክፍለ ሀገራዊ ምርጫ እንዲካሔድ የታዝማኒያን እንደራሴ ጠየቁ