Listen to interviews, features and community stories from the SBS Radio Amharic program, including news from Australia and around the world. - የአውስትራሊያና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን አካትቶ፤ ቃለ ምልልሶችን፣ ዘገባዎችንና የማኅበረሰብ ታሪኮችን ከኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ ፕሮግራም ያድምጡ።
የSBS አማርኛ አገልግሎት ራዲዮ ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ ከጋዜጠኛነት ሙያ ጅማሮው ተነስቶ የSBS ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞን ከአማርኛ አገልግሎቱ ጋር አሰናስሎ ማኅበረሰባዊና ሉላዊ አስተዋፅዖዎችን ያነሳል።
ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ በኢትዮጵያ የSBS አማርኛ አገልግሎት ዋና ዘጋቢ ነው። የSBSን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል አስመልክቶ የግል የሙያ ተሞክሮዎቹን፣ የSBS እና የSBS አማርኛ አስተዋፅዖዎችን ነቅሶ ግለ አተያዩን ያጋራል።
አውስትራሊያ ውስጥ የተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች ምጣኔ ሃብት ላይ የ2 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ወጪን ማስከተላቸው ተመለከተ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 7.7 ቢሊየን ብር ተዘርፏል ቢባልም 'የዝርፊያ ሙከራ እንጂ ዘረፋ አልተካሔደብኝም' አለ
Australia has a dark chapter of history that many are still learning about. Following European settlement, Aboriginal and Torres Strait Islander children were removed from their families and forced into non-Indigenous society. The trauma and abuse they experienced left deep scars, and the pain still echoes through the generations. But communities are creating positive change. Today these people are recognised as survivors of the Stolen Generations. - አውስትራሊያ አሁንም ድረስ አያሌዎች እየተማሩት ያለ የጨለማ ታሪክ ምዕራፍ አላት። የአውሮፓውያን ሠፈራን ተከትሎ፤ የአቦርጂናልና ቶረስ መሽመጥ ደሴት ሕፃናት ከወላጆቻቸው በኃይል ተነጥቀው ነባር ዜጎች ወደ አልሆነው ሕብረተሰብ ተወሰዱ። በውስጡ ያለፉበት የስሜት ሁከትና ጉስቁልና ጠባሳዎችን ጥሎባቸው አለፈ፤ ሕመሙ ከትውልድ ትውልድ ተሸጋግሮ እስካሁንም አለ። ይሁንና ማኅበረሰባቱ አዎንታዊ ለውጥን እየፈጠሩ ነው። ዛሬ እኒህ ሰዎች በተሰረቀው ትውልድ ተቋቋሚነት ይነሳሉ።
SBS ከ1975 አንስቶ የአውስትራሊያ መድብለባሕል የማዕዘን ደንጊያና ድምፅ ማጉሊያ ሆኖ እስከ 2025 የተጓዘበትን የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞውን ጁን 9 / ሰኔ 2 ያከብራል። ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት ምልሰታዊ ምልከታቸውን ያጋራሉ።
የአቶ ብዙአየነህ ኃይለማርያም ይፍጠር ድንገተኛ ሕልፈተ ሕይወት ከቤተሰብ እስከ ማኅበረሰብ አባላት ብርቱ ሐዘንን ፈጥሯል። ሕልፈታቸውንም ተከትሎ አብሮ አደጋቸው አቶ ኬኔዲ ገብረየሱስ "ብዙአየነህ በማኅበረሰቡ ውስጥ ጥሩ ስም ነበረው። ሕልፈቱ በጣም የሚያስደነግጥ፤ በጣም የሚያሳዝን ነው፤ ማኅበረሰቡ ይጎዳል" ሲሉ፤ የረጅም ጊዜ ወዳጃቸው አቶ ልዑል ፍስሃ "ብዙአየነህ ላመነበት ነገር በትጋት የሚሠራ፤ ለዕውቀት ከፍተኛ ቦታ የሚሰጥ፤ ትልቅ ሰው ነበር። ሐዘናችን ጥልቅ ነው" ብለዋል። የአቶ ብዙአየነህ ፀሎተ ፍትሐት ሐሙስ ግንቦት 21 ቀን 2017 / ሜይ 29 ቀን 2025 በሜልበርን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከጠዋቱ 9:00 am ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ይፈፀማል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 14.5 ሚሊየን መንገደኞችን አጓጓዘ፤ 5.6 ቢሊየን ዶላር ገቢ አገኘ
Alfred is an Indonesian migrant, and Clinton is an Aboriginal man from Western Australia. Their friendship changed the way Alfred understood his identity as a migrant Australian. - አልፍሬድ የኢንዶኔዥያ ፍልሰተኛ ሲሆን፤ ክሊንተን የምዕራብ አውስትራሊያ ነባር ዜጎች ሰው ነው። ወዳጅነታቸው ከአልፍሬድ አውስትራሊያዊ ፍልሰተኛ ማንነት ግንዛቤ ጋር ተያይዞ ለመለወጥ በቅቷል።
ጋዜጠኛ ማርታ ፀጋው፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ በምልሰታዊ ምልከታና ከአድማስ ባሻገር የመጪ ጊዜያት አገልግሎት አተያይዋንና መልካም ምኞቷን አጣምራ ታወጋለች።
የኢፌዴሪ ፖሊስ 47 የጤና ባለሙያዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሔደ መሆኑን አስታወቀ
"ጌታሁን በጣም ጥሩ ሰው ነው፤ ተፈጥሮን የሚያደንቅ ነበር። ብንለያይም በሕልፈቱ በጣም አዝኛለሁ" በመኪና አደጋ ሕይወቱ ያለፈ የጌታሁን ዝግታ የቀድሞ ባለቤት ዳናዊት ሕሉፍ። የወጣት ገዛኸኝ ታደሰ ፀሎተ ፍትሐት ቅዳሜ ግንቦት 16 / ሜይ 24 በደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን 9:30 am ከተከናወነ በኋል የቀብር ሥነ ሥርዓቱ የሚፈፀም ሲሆን፤ የአቶ ጌታሁን ዝግታ የቀብር ሥነ ሥርዓት በቅርቡ ይከናወናል።
በአሁኑ ወቅት በሕይወት የሌሉት የቀድሞው የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ስዮም መስፍን በሕይወት ሳሉ ከSBS አማርኛ ጋር ባካሔዱት ቃለ ምልልስ የኢትዮ - ቻይና ዲፕሎማሲያዊና ምጣኔ ሃብታዊ ግንኙነቶችንና የወደፊት ውጥኖቻቸውን አጋርተው ነበር (የSBS 50ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ዳግም የቀረበ)።
በአሁኑ ወቅት በሕይወት የሌሉት የቀድሞው የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ስዮም መስፍን በሕይወት ሳሉ ከSBS አማርኛ ጋር ባካሔዱት ቃለ ምልልስ ከትጥቅ ትግል ጅማሯቸው ተነስተው፤ ከሕወሓት አመራር በፈቃዳቸው ስለምን እንደተሰናበቱ አስረድተው ነበር (የSBS 50ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ዳግም የቀረበ)።
የአማራ ክልል ዳኞች በፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊ ወይም አወዛጋቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በማናቸውም ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሃሳብ እንዳይሰጡ የሚከለክል ደንብ ፀደቀ
በ77 ዓመታቸው ከአንድ አሠርት ዓመት በፊት ከእዚህ ዓለም ከመለየታቸው በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪ፣ ደራሲ፣ ጋዜጠኛና ዲፕሎማት ከነበሩት አምባሳደር ዘውዴ ረታ ጋር በሙያ ሕይወታቸው፣ የሥነ ፅሁፍ በረከቶቻቸውና ዲፕሎማሲ ዘርፍ ዙሪያ አተያያቸውን አጋርተውናል። የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግም ዳግም አቅርበነዋል።
የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠን ቀነሰ
በሜልበርን የኢሬቻ ቱሉ / አፍራሳ ክብረ በዓል አስተባባሪዎች ኦቦ ዓለማየሁ ቁቤ፣ ኦቦ በንቲ ሆሉቃና አደይቱ ሚደቅሳ የክብረ በዓሉን ፋይዳዎችና የአከባበር ሂደቱን አንስተው ያስረዳሉ።
ሰሞኑን በሀገር አቀፍ ደረጃ 'ከፊል' ያሉትን የሥራ ማቆም አድማ በማድረግ ላይ ያሉት የጤና ባለሙያዎች ያነሷቸው የደመወዝ፣ የጥቅማ ጥቅምና ምቹ የሥራ ሁኔታ ጥያቄዎቻቸው ምላሽ ካላገኙ 'ሙሉ' የሥራ ማቆም አድማ ሊያደርጉ እንደሚችሉ አሳሰቡ፤ የጤና ሚኒስቴር አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀ።
"የፉትስክሬይ ሮታሪ ክለብ፣ በጎ ፈቃደኞች፣ የአውስትራሊያ የሕክምና ተቋማትንና ለ19ኛ ዙር የተለያዩ የእርዳታ ቁሳቁሶችን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ የወጪ ድጋፋቸውን የቸሩ ኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን የማኅበረሰብ አባላትን በአውስትራሊያ ኢፌዴሪ ኤምባሲ ስም አመሰግናለሁ" አምባሳደር አንዋር ሙክታር መሐመድ
Learn how to talk about time. - Learn how to talk about time.
The migration system is complex and confusing. Experts say a lack of accessible support and credible information is leading to visa abuse. - የፍልሰት ሥርዓት ውስብስብና አደናጋሪ ነው። ጠበብት ተደራሽነት ያለው ድጋፍና ተአማኒነት ለአግባብ የለሽ የቪዛ ተፅዕኖ እንደሚያመራ ይናገራሉ።
በኢትዮጵያ የልጅነት እርግዝና 13 በመቶ መድረስ አሳሳቢ ሆኗል
ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚን ጨምሮ አዲሱ የሌበር መንግሥት ካቢኔ አባላት ቃለ መሐላ ፈፀሙ
'በሕገ ወጥ የማዕድን ቁፋሮና ዝውውር ውስጥ የክልሎችና የአካባቢ ባለስልጣናት እጆች አሉበት' አሉ የምክር ቤት አባላት
ወ/ት ሰላማዊት ወሰን ከብሪስበን "በተለይ ያለ አባት ልጆቻቸውን ላሳደጉ እናቶች 'እንኳን ለእናቶች ቀን አደርሳችሁ' ማለት እፈልጋለሁ" ሲሉ፤ ወ/ሮ ቤተልሔም ጥበቡ ከሜልበርን "እናትነትን በቃላት መግለፅ አይቻልም፤ እናትነት ትልቅ ስጦታ ነው" ይላሉ፤ ወ/ሮ ሜሮን ተስፋዬም "የእናቶችን ቀን ማሰብ የሚገባን በየዕለቱ ነው" በማለት የእናቶችና የእናት ተምሳሌዎችን የክብር መዘከሪያና ሞገስ ማላበሻዋን "የእናቶች ቀን" አስመልክተው የእናትና ልጅ ግለ ሕይወታቸውን አጣቅሰው ያጋራሉ። አቶ ኢዮብ ቀፀላም ከሲድኒ፤ ሀገር ቤት ለሚገኙት ውድ እናታቸው የእናቶች ቀን መልካም ምኞታቸውን ያስተላልፋሉ።
በመላው አለም ለምትገኙ እናቶች በሙሉ እንኳን ለእናቶች ቀን አደረሳችሁ ። " እናቶችን ማክበር ማለት ሰላምን መፍጠር ለእኩልነት መቆም ማለት ነው " በሚል መርህ የተነሳቸው አሜሪካዊቷ አና ጃርቪስ ቀኑ ሲከበር ዛሬም ድረስ የእናቶች ቀን እናት በመባል ትታወሳለች።
ቴዎድሮስ ተሾመ ከበደ፤ ፀሐፊ፣ ዳይሬክተርና ተዋናይ ነው። በቅርቡ ሰሞነኛ የነበረውን ዓባይ ወይስ ቬጋስ ፊልሙን 'የኢትዮጵያ ኔትፊሊክስ' ሲል በጠራው Habeshaview TV አማካይነት ለሕዝብ ዕይታ አቅርቧል። ስለ ፊልሙ ጭብጥ፣ በባሕር ማዶና ሀገር ቤት ያሉ የሩቅ ርቀት ፍቅርና ፈተናዎችን ከሌሎች ፈታኝ ማኅበራዊ የሕይወት ጉዞዎች ጋር አሰናስሎ ይናገራል።
ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ፤ ሀገር ቤት የጋዜጣና መፅሔት አሳታሚና ባለቤት ሆኖ ዘግቧል። በድምፅ ሰጪነትም ተሳትፏል። በኬንያ የስደት ሕይወቱም ድኅረ ምርጫ ያስከተላቸውን የሕይወት ጥፋትና የንብረት ውድመት ትኩረት ሰጥቶ ተመልክቷል። በሀገረ አውስትራሊያም ፍልሰተኛ ሆኖ የምርጫ ክንውኖች በቅርበት ተከታትሏል። የአውስትራሊያን ዜግነት ከተላበሰ ወዲህ ግና በሀገር አቀፍ ምርጫ የአውስትራያን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ለመቅረፅና ለመገንባት በድምፅ ሰጪነት ቀጥተኛ የዜግነት ድርሻውን ሲወጣ የዘንድሮው የ2025 ፌዴራል ምርጫ የመጀመሪያው ነው። ምልሰታዊ ምልከታውን ከአሁናዊ ተሞክሮው ጋር አሰናስሎ ንፅፅሮሹን ያጋራል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ 86 አብላጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበሮችን ይዘው የሁለተኛ ዙር አስተዳደራቸውን ጀመሩ፤ የምርጫ ድምፅ ቆጠራው ሲጠናቀቅ የሌበር ፓርቲ የምክር ቤት ወንበሮች እስከ 90 ሊደርሱ እንደሚችሉ ግምት አለ።
የሊብራል ፓርቲ በሌበር ፓርቲ ዕጩ ድል ተነስተው የምክር ቤት ወንበራቸውን ያጡትን የቀድሞው መሪውን የመተካት ሂደት ጀመረ
የአውስትራሊያ ማዕድን አሳሽ አስካሪ ሜታልስ ኩባንያ በኢትዮጵያ ሥራ ጀመረ
On election day the Australian Electoral Commission anticipates one million voters to pass through their voting centres every hour. Voting is compulsory for everyone on the electoral roll, so all Australians should familiarise themselves with the voting process before election day. - የአውስትራሊያ ምርጫ ኮሚሽን በምርጫ ዕለት በሰዓት አንድ ሚሊየን መራጮች በምርጫ ማዕከላት ውስጥ እንደሚያልፉ ግምት አለው። ምርጫ ከግዴታ ጋር ተያያዥነት ስላለው ማናቸውም አውስትራሊያውያን ከምርጫው ቀን በፊት ስለ ምርጫ ሂደቱ በቂ ግንዛቤ መጨበጥ አለባቸው።
ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ የማኅበረሰብ አመራርና ግለ ተሞክሯቸውን አጣቅሰው ይናገራሉ።
ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አመራር አባላት "ከአንድ የሥራ ዘመን ወይም ሶስት ዓመታት በላይ ማገልገል የለባቸውም" ይላሉ። ስለምን? አተያያቸውን ያጋራሉ።
ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት፤ ስለ ማኅበሩ ወቅታዊ እንቅስቃሴዎች ያስረዳሉ።
የካናዳ ተቃዋሚ ቡድን መሪ የምክር ቤት ወንበራቸውን አጡ
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን 'የትግራይ ሊብራል ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ' በሚል ስያሜ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ሊያቋቁም ነው።
የጋዛ ጦርነት ቅዳሜ ሜይ 3 በሚካሔደው የአውስትራሊያ ፌዴራል ምርጫ፤ በሁለቱ ዋነኛ ፓርቲዎች ሌበርና ሊብራል/ናሽናልስ ላይ አንዱ ዋነኛ የፖሊሲ ተፅዕኖ አሳዳሪ ጉዳይ ሆኗል።
ለተሽከርካሪዎች ኢንዱስትሪ ራሱን የቻለ የሥርዓተ ደንብ ረቂቅ ፖሊሲ እየተዘጋጀ ነው
The differing and diverse religious beliefs Australians hold will influence their vote this election. - አውስትራሊያውያን ይዘዋቸው ያሉት የተለያዩና ዝንቅ ሃይማኖታዊ እምነቶች በዘንድሮው ምርጫ ድምፅ አሰጣጣቸው ላይ ተፅዕኖን ሊያሳድርባቸው ይችል ይሆናል።
አውስትራሊያ ረጅም እድሜን የሚኖሩ ሰዎች አሉባት ከሚባሉ አገራት መካከል አንደኛዋ ናት ።በአማካኝ አንድ አውስትራሊያዊ የ83ተኛ የልደት በአሉን ያከብራል። ነገር ግን የአቦርጅናል እና ቶርስት ስትሬት አይላንደር ሕዝቦች ከተቀረው አውስትራሊያውያን የእድሜ ጣራ ጋር ሲነጻጸሩ የእድሜያቸው ጣሪያ በስምንት አመት አመት ያንሳል። ይህንንም ለመቀየር ክፍተትን ማጥበብ የሚለው ሀሳብ በብሄራዊ ደርጃ የተቀረጸ ነው። የቀደምት ነዋሪዎችን ጤና እና ደህንነት በማሻሻል ፤ ሌሎች ነባር ያልሆኑ አውስትራሊያውያን የሚኖሩቱን ጥራት ያለው ህይወት እና እድሎችን እንዲያጣጥሙ ማድረግ ይቻላል።
ቀሲስ አብርሀም ሀብተ ስላሴ በዋሽንግተን ዲሲ ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም አገልጋይ ፤ “ ባህላችን ጥንታዊ ነው የተቀዳውም ከመጀመሪያዎቹ የክርስትና አማኞች ነው ፤ ቅዱስ በሆነ ባህል እናምናለን መጽሀፍ ቅዱስም አለን ፤ እነዚህ ሁለቱ በምንም ይነት መልኩ የማይነጣጠሉ ናቸው ይላሉ፡፡ ‘'
የፖፕ ፍራንሲስ የቀብር ስነ ስርአት በመጪው ቅዳሜ በቫቲካን ይፈጸማል ፤ ታላላቅ ሰዎች እና የአገራት መሪዎች በቀብሩ ላይ እንደሚገኙ ማረጋገጫን ሰጥተዋል ፡፡
የናይጄርያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ቢያንካ ኦጁኩ ፤ በአቡጃ ናይጄርያ ከኢትዮጵያ አምባሳደር ለገሰ ገረመው ጋር ሰሞኑን በተወያዩበት ወቅት ነው ጥያቄውን ያቀረቡት ፡፡
ዘማሪና ፓስተር ዳንኤል አምደሚካኤል ወደ አውስትራሊያ ለወንጌላዊ አገልግሎት በመጡበት ወቅት በክርስቲያናዊ ህይወታቸው እና አገልግሎታቸው ዙሪያ ላነሳልላቸው ጥያቄዎች ምላሻቸውን ሰጥተውናል ። በዝማሬ ህይወታቸውም ስምንት ሙሉ አልበሞችን የሰሩ ሲሆን ጥቂቶችንም በድምጻቸው አሰምተውናል ።
ፖፕ ፍራንሲስ የመጨረሻውን የፋሲካ በአል መልእክታቸውን ከቅዱስ ጴጥሮስ ባሲሊካ በረንዳ ላይ ካስተላለፉ ከአንድ ቀን በኋላ ነው ክዚህ አለም በሞት የተለዪት።
18 ሚሊዮን የሚሆኑ አውስትራሊያውያን ለቅድሚይ ምርጫ የተመዘገቡ ሲሆን ፤ 60 ሚሊዮን የሚሆን የምርጫ መስጫ ወረቀቶች መታተማቸውንም የምርጫ ኮሚሽን አያይዞ አስታውቋል ፡፡
129 የፌደራል መሰሪያቤት ሰራተኞች ፤ የትምህርት ማስረጃቸው ሀሰተኛ ሆኖ ተገኝቷል ሲል የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
መላክ ጸሃይ ቀሲስ መንግስቱ ሀይሌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያ የምስራቅ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ አህጉረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም የብሪዝበን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የፋሲካን በአል አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።