Listen to interviews, features and community stories from the SBS Radio Amharic program, including news from Australia and around the world. - የአውስትራሊያና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን አካትቶ፤ ቃለ ምልልሶችን፣ ዘገባዎችንና የማኅበረሰብ ታሪኮችን ከኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ ፕሮግራም ያድምጡ።

ሰሞኑን ከእዚህ ዓለም ለመጨረሻ ጊዜ ለተለዩት የማኅበረሰብ መሪ፣ ቅን አገልጋይ፣ የሶስት ልጆች አባትና መልካም ወዳጅ ዶ/ር ብርሃኑ ወልደኪዳንን ሕልፈተ ሕይወት አስመልክቶ ልጃቸው ሚካኤል ብርሃኑና የቅርብ ወዳጆቻቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ይገልጣሉ። ለዶ/ር ብርሃኑ ቤተሰቦችና የማኅበረሰብ አባላት በሙሉ መፅናናትን ይመኛሉ።

ዶ/ር ዮናታን ድንቁ - በአውስትራሊያ ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ እና ዶ/ር ደሴ ታርቆ - በአደላይድ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ፤ የ2026 የአውስትራሊያ ዓመታዊ የፌዴራል በጀት ትሩፋቶችንና እንከኖችን ነቅሰው ያመላክታሉ።

ዳን ጎቴ ለማዳበሪያ ፋብሪካ የመደበውን 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ወደ 4 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማድረጉን አስታወቀ

ኢመረተስ ፕ/ር ባየ ይማም፤ በአዲስ አበባና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች የቋንቋ መምህርና "የአማርኛ ሰዋሰው" መጽሐፍ ደራሲ፤ በመጽሐፋቸው ውስጥ ስላነሷቸው የአማርኛ ሰዋሰው አወዳደቅ ሂደትና ደረጃ፣ የሆህያት አጠቃቀምና ጥቅል የቋንቋ ሥርዓተ ትምህርትን አስመልክተው ምክረ ሃሳባቸውን ያጋራሉ።

ኢመረተስ ፕሮፌሰር ባየ ይማም፤ በአዲስ አበባና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች የቋንቋ መምህር፤ በቅርቡ ለአንባቢያን እነሆኝ ባሉት "የአማርኛ ሰዋሰው" መጽሐፋቸው አማርኛ ግዕዝንና አገውኛን ተክቶ እንደምን ለቤተ መንግሥት ቋንቋነት እንደበቃ፤ የቋንቋን ውልደትና ሞት ጊዜ ፈጂነት ከሌሎች አንኳር ሃሳቦቻቸው ጋር አያይዘው ይናገራሉ።

በአዲስ አበባና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች የቋንቋ መምህር፤ ኢመረተስ ፕሮፌሰር ባየ ይማም፤ በቅርቡ ለሕተመት ስላበቁት "የአማርኛ ሰዋሰው" መፅሐፋቸውን ትሩፋቶች ነቅሰው ያስረዳሉ።

በኩዊንስላንድ ተጨማሪ የቤት ግንባታዎች እንደሚካሔዱ የፌዴራል በጅሮንድ ጂም ቻልመርስ አስታወቁ

በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን ዩናይትድ ስቴትስ አስታወቀች

ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ የቪክቶሪያ ኢትዮጵያውያን ማኅበር ፕሬዚደንት፤ የበርበሬና ሽሮ ወደ አውስትራሊያ የማስገባት ፈቃድን ተከትሎ በኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላትና የጉምሩክ ተቆጣጣሪዎች ዘንድ ያሉ ብዥታዎችን አንስተው ያመላክታሉ። የማኅበሩን ወቅታዊ እንቅስቃሴዎችና ውጥኖችንም ይገልጣሉ።

ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበር ፕሬዚደንት፤ ማኅበሩ ስለምን ለኢትዮጵያውያን የሚውል የመቃብር ሥፍራ ለማግኘት ተነሳሽነት እንደወሰደ ያስረዳሉ። የማኅበረሰብ አባላትን አተያዮች ይጠይቃሉ።

የቻይና በኢትዮጵያ ቀጥተኛ ሙዋዕለ ንዋይ ፍሰት ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መድረሱ ተነገረ

Australia's petrol and diesel prices remain under pressure. The RBA's decision to hike the cash rate this month is adding to the financial strain facing many households. We look at some free and independent support services that are available to help people manage financial stress. - የአውስትራሊያ የነዳጅና ናፍጣ ዋጋዎች ጫናዎች ሳይረግቡ አሉ። የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠን ጭማሪም አያሌ ቤቶች ላይ ታካይ የፋይናንስ ሸምቀቆውን አጥብቋል። በፋይናንስ ጭንቀት ውስጥ ላሉ ሰዎች ነፃና ገለልተኛ የድጋፍ አገልግሎት የሚቸሩት ላይ ምልከታ አድርገናል።

አቶ ሰሎሞን አዲስ ታምሩ ባደረበት ህመም ሳቢያ ሚያዚያ 22 ቀን 2026 ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል ። አቶ ሰለሞን ወደ አውስትራሊያ ለመጀመሪያ የመጡት የአቶ አዲስ ታምሩ ሁለተኛ ልጅ ሲሆን ፤ እናቱ ወ/ሮ ሊሊያን ኒኮላስ የአቦርጅናል ዝርያ ያላቸው ናቸው። የጸሎት እና ሽኝት ስነ ስርአቱም በደብረ ሰላም መድሃኒአለም ሜልበርን ቤተክርስቲያን ተከናውኗል። ስርአተ ቀብሩም ሰኞ ሜይ 21 ቀን 2026 በሜልበርን ተፈጽሟል። በሽኝት ስነስርአቱ ላይ በሜልበርን እና በአውስትራሊያ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተዋል ። በስፍራው ከተገኙት መካከልም ፤ መላክ ጸሃይ ቀሲስ መንግስቱ ሀይሌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያ የምስራቅ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ አህጉረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም የብሪዝበን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ : መላከ አርአያም ቀሲስ ተስፋ ኅሩይ - የሜልበርን ደብረሰላም መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ : አቶ እሸቱ ሙሉጌታ ፤ ወ/ሮ ተኛኜ ወርቅ ብስራት ፤ ጄሰን አዲስ ታምሩ ( ወንድም ) ፤ ታሻ ፊትዝክላረንስ (ሚስት) ወ/ሮ ቅድስት ደስታ ፤ አቶ አበራ አያሌው እና ወ/ሮ ቆንጂት ጥላሁን የተሰማቸው ህዘን ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ተጨማሪ 9 ነጥብ 94 ቢሊዮን ብር በጀት አፀደቀ

ወ/ሮ እመቤት አሰፋ የቅድስት ማርያም የኢትዮጵያውያን ሴቶች ማህበር በሲድኒ ፤ የዘንድሮውን የእናቶች ቀን ለየት የሚያደርገው አርአያ የሆኑ እናቶችን ሁለት ከኢትዮጵያውያን እንዲሁም ሁለት ከሱዳን የማህበረሰብ አባላት የእውቅና ሽልማትን ማድረጋችን ነው ብለዋል።

በቅርቡ በሀገረ አሜሪካ - ኦክላሃማ ዩኒቨርሲቲ፤ የአንጋፋው ኢትዮጵያዊ ሰዓሊና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ የጥበብ ሥራዎችና የሕይወት ዘመን አሻራዎቹ ላይ ያተኮረና የዘከረ ሲፖዚየም ተካሂዷል። የሕይወት ዘመን የጥበብ ሥራዎቹን አንስተው ከዘከሩት ተጠባቢዎች መካከል በሥነ ግጥም፣ ሥነ ቀለም ቅብ፣ ቅርፃ ቅርፅና የንድፍ ሥራዎች ዘርፍ ስመጥርና መምህርት የሆኑት ከበደች ተክለአብ ናቸው።

በቅርቡ በሀገረ አሜሪካ - ኦክላሃማ ዩኒቨርሲቲ፤ የአንጋፋው ኢትዮጵያዊ ሰዓሊና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ የጥበብ ሥራዎችና የሕይወት ዘመን አሻራዎቹ ላይ ያተኮረና የዘከረ ሲፖዚየም ተካሂዷል። የሕይወት ዘመን የጥበብ ሥራዎቹን አንስተው ከዘከሩት ተጠባቢዎች መካከል በሥነ ግጥም፣ ሥነ ቀለም ቅብ፣ ቅርፃ ቅርፅና የንድፍ ሥራዎች ዘርፍ ስመጥርና መምህርት የሆኑት ከበደች ተክለአብ ናቸው።

እሥራኤል በደቡብ ሊባኖስ ቀዬዎች ጥቃት ሰነዘረች

በዘንድሮው የዩሮቪዥን የሙዚቃ ዝግጅት የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ቀንሷል

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተነፈገው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤልን የክልሉ ፕሬዚደንት አድርጎ መሾሙን አስታወቀ

አቶ ወርቅነህ ባይህ፤ የኩዊንስላንድ አፍሪካውያን ማኅበረሰባት ምክር ቤት የዓመቱ በጎ ፈቃደኛ ተሸላሚ ሆነዋል። ለሽልማት ስላበቋቸው የረጅም ጊዜያት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶቻቸው አንስተው ይናገራሉ።

የአምስት ዓመቷ ሕፃን ግድያ “የልብ ስብራት” ማስከተሉ ተመለከተ

Rising fuel prices are putting pressure on household budgets across Australia, and for many people, it's changing the way they travel. So what can you do to reduce your fuel costs without giving up your daily routine? Here are some simple, practical ways to save money on petrol. - በመላ አውስትራሊያ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በነዋሪዎች በጀት ላይ ጫናዎችን አሳድሯል። ለአያሌ ሰዎችም የአጓጓዝ ሁኔታቸውን እንዲቀየሩ ግድ አሰኝቷል። እናም፤ የአዘቦታዊ አጓጓዝዎን ሳይቀይሩ የነዳጅ ወጪዎን ለመቀነስ ምን ማድረግ ይችላሉ? ለነዳጅ የሚውል ገንዘብዎን ለመቆጠብ ጥቂት ቀላል፣ ግብር ላይ ዋይ መንገዶችን እነሆን።

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለ ስልጣናትና ታዋቂ አርቲስቶች ከ98 ቢሊዮን ብር በላይ ምዝበራ እንደፈፀሙ በኦዲት መረጋገጡን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ

Each year Australians gather on ANZAC Day to remember those who served in wars, conflicts and peacekeeping missions. But whose stories are we remembering? Are there stories we don't always hear? In this episode we explore an important part of Australia's history that has often been overlooked—the service of Aboriginal and Torres Strait Islander peoples. - በየዓመቱ አውስትራሊያውያን የአውስትራሊያና ኒውዝላንድ ጦር ሠራዊት ኮር ቀን (አንዛክ ቀን) ለማክበር ይታደማሉ። እኒያን በጦርነቶች፣ ግጭቶች እና የሰላም አስከባሪ ግዳጆች ተሰማርተው አገልግሎቶቻቸውን አበርክተው የነበሩትን በክብር ለመዘከር። ይሁንና የምንዘክረው የእነ ማንን ታሪክ ነው? አዘውትረን የማንሰማቸው ታሪኮችስ አሉ? በእዚህ ክፍለ ዝግጅት በጣም ጠቃሚ የሆነ ግና ቸል የተባለ ታሪክን እናነሳለን፤ የአቦርጂናልና ቶረስ ሰርጥ ደሴት ሰዎችን አገልግሎት።

Learn English useful for talking about ageing parents and family responsibilities. Practise everyday phrases for describing challenges, offering help, and discussing how to support parents. - ዕድሜያቸው እየገፋ ስላሉ ወላጆችና የቤተሰብ ኃላፊነቶች ለመናገር እንግሊዝኛን መማር ጠቀሜታ አለው። በየዕለቱ ተግዳሮቶችን፣ እርዳታ ልገሳንና ወላጆችን እንደምን ማገዝ እንደሚቻል ገላጭ የሆኑ አባባሎችን ይለማመዱ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከስድስት ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከሁሉም ክልሎችና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር 1,452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት የሚረዳ የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

በአውስትራሊያ ታሪክ የመጀመሪያው የሆነውን የቪክቶሪያ ክፍለ ሃገር የሌበር መንግሥት የአዋቂና ወጣት ወንዶች ሚኒስትር መሾምን ተከትሎ፤ የፌዴራል ተቃዋሚ ቡድኑ የአዋቂና ወጣት ወንዶች ልዑክ ሰየመ

የደቡብ ሊባኖስ ነዋሪዎች ቀዬአቸውን ለቅቀው እየወጡ ነው

የፌዴራል ፖሊስ በቴዲ አፍሮ ጉዳይ ምላሽ ሰጠ፤ የድምፃዊው የቅርብ ወዳጆች የፖሊስን ምላሽ በትክክለኛ መረጃነት አልተቀበሉም

ከአንደኛው የዓለም ጦርነት አንስቶ የአውስትራሊያ ነባር ዜጎች በአውስትራሊያ የመከላከያ ሠራዊት አባልነት አገልግለዋል። ብሔራዊ የዜግነት መብት አልነበራቸውም። ሆኖም ግና ዜግነት የነፈገቻቸው ሀገር በመቶዎች የሚቆጠሩቱን ለወታደራዊ ግዳጅ ባሕር አሻግራ ልካለች።

ሶሊያና እርሴ፤ ትንፋሽ አስዋጭ፣ የልብ ትርታን ደላቂ፣ ከዮጋም፣ ከጂምናስቲክም ልዩ አካላዊ እጥፋትና ዝርጋታን፣ ልዩ ምትሃት መሰል ክህሎትን ግድ የሚለው፤ ግና ሞገስን ተላብሶ መድረክ ላይ ግዘፍ የሚነሳ Contortionist Extraordinaire ኢትዮጵያዊት ናት። ድንቅ ክህሎቷም ከኤፕሪል 7 እስከ ሜይ 24 በሜልበርን ከተማ Meat Market ከClub Kabarett ጋር ለሕዝብ ዕይታ ይቀርባል። የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላትም ታዳሚዎቿ እንዲሆኑ ትጋብዛለች።

የአውስትራሊያ ፌዴራል መንግሥት ተጨማሪ ናፍጣ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ከተለያዩ ሀገራት ጋር ከስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ

የኢትዮጵያ የበሬ ቆዳ በጥሬው ለምግብነት እየዋለ መሆኑ ተነገረ

የዋን ኔሽን የሕዝብ አስተያየት ድጋፍ መውረድ ጀመረ፤ ሆኖም ከፌዴራል ተቃዋሚ ቡድኑ ቀድሞ ሔዷል

ኢትዮጵያ የራሷን ሳተላይቶች በሀገር ውስጥ ለመገጣጠምና መሞከር የሚያስችላትን ግዙፍ የማዕከል ግንባታ ከሩስያ የጠፈር ተቋም ጋር በጋራ ለመሥራት ዝግጅቷን ማጠናቀቋ ተነገረ

በሥርዓተ ትምህርት፣ የሴቶችና መድብለ ባሕል ተኮር የሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ምርምራቸውን በሀገረ እንግሊዝ ኤክስተር ዩኒቨርሲቲ እያካሔዱ ያሉት ወ/ት ናዲያ ሞናያ፤ ከፊል የምርምር ግኝቶቻቸውንና ፖሊሲ ነክ ጉዳዮችን አንስተው ያስረዳሉ።

በዩኒቨርሲቲ Exeter የሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ተማሪ ናዲያ ሞናያ፤ ምርምራቸው ስለሚያተኩርበት ለውጥ የሚያሻቸው የሴቶች ጉዳዮችና የመድብለ ባሕል ፋይዳዎችን አንስተው ያናገራሉ። ከግጥም ሥራዎቻቸው በቅርቡ "I Hugged a Tree" በሚል ርዕስ ለአባታቸው ዝክረ መታሰቢያ ከፃፉት የስንኝ ቋጠሯቸው በቅንጭቡ ያስደምጣሉ።

ናዲያ ሞናያ - በሀገረ እንግሊዝ ኤክስተር ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ተማሪ ናቸው። ውልደትና ዕድገታቸው አዲስ አበባ ነው። የኢትዮጵያዊት፣ ኤርትራዊትና ጣሊያናዊት ዝንቅ ብሔራዊ ማንነትን አጣምረው ይዘዋል። ሁለት ሀገርኛና አምስት የውጭ ሀገራት ቋንቋዎች ተናጋሪ ናቸው። የውልደት፣ ዕድገትና የትምህርት ሕይወታቸውን ነቅሰው ያጋራሉ።

የአውስትራሊያ ከተሞች የራሳቸውን የነዳጅ ክምችት ለርመፍጠር ቅድመ ዝግጅት ጀምረናል አሉ

Workplace discrimination, gender-based violence and financial inequality—these are just some of the reasons why women need dedicated legal services. You don't have to navigate the legal system alone. In Australia, free legal services exist to advocate for vulnerable women in ways that are safe, confidential and culturally appropriate. - ሴቶች የተለየ የህግ ባለሙያዎች እንዲያስፈልጋቸው ከሚያደርጉት ምክንያቶች መካከል ፤ በስራ ቦታ የሚፈጸም መድልዎ ፤ ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃት ፤ በገቢ ላይ የሚደረግ ማበላለጥ የሚሉት ጥቂቶቹ ናቸው ፡፡ በአውስትራሊያ የህግ ተቋማትን ብቻዎትን ማፈላልገ አይጠበቅብዎትም ፡፡ በችግር ላይ ያሉ ሴቶች ደህንነታቸ በተጠበቀ ሁኔታ ፤ ምስጢራቸው እና ባህላቸውን ባገናዘበ መልኩ ነጻ የህግ አገልግሎት አለ፡፡

በሱዳን ከ 21 ሚልዮን በላይ ዜጎች ለጽኑ ረሀብ እና የምግብ እጦት ተጋልጠዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ወኪል አስታወቁ

በኢትዮጵያ ከአንድ ሚሊየን በላይ ከደቡብ ሱዳን ፤ ኬንያ ፤ ኤርትራ እና ሶማሊያ የተፈናቀሉ ስደተኞች እንደሚኖሩ ተገለጸ

የነዳጅ ዋጋ መጨመርን ተከትሎ የኡበር አሽከርካሪዎች ደንበኞቻቸውን ተጨማሪ ዋጋ እንዲያስከፍሉ ደንብ ወጣ

መልአከ ፀሐይ መንግሥቱ ኃይሌ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያ የምስራቅ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ አኅጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የብሪስበን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የበዓለ ትንሣኤን ትርጓሜ ያስረዳሉ። የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።

ወንጌላዊ የምሩ ታደሰ፤ በዘፀዓት የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን አገልጋይ፤ የፋሲካ በዓልን አስመልክተው የ ‘እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን' መልካም ምኞት መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።

ወ/ሮ ገነት ቤተ ጌራወርቅ፤ በደብረ ብርሃን ከተማ የኤፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና በደብረ ብርሃን መጠለያ ቻይና ካምፕ ተጠላይ እናት ሩቂያ አሕመድ ስለ ተፈናቃዮች ሕይወት፣ በደቡብ አውስትራሊያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር አስተባባሪነት ሁለት ወላጆቻቸውን ላጡ ሕፃናት ስለተደረገላቸው ሰብዓዊ እርዳታ አንስተው ይናገራሉ። ልባዊ ምስጋናቸውንም ያቀርባሉ።

የደቡብ አውስትራሊያ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት ዶ/ር ለገሰ ጋረደው፣ የደቡብ አውስትራሊያ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት አቶ ጥላዬ ተከተልና አቶ መሐመድ በያን፤ እንደምን የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት ከወለጋ ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፖች ውስጥ ለሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖች ልገሳቸውን እንደቸሩ ይናገራሉ።

የአደራ ቃል "አውስትራሊያ ላላችሁ ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፤ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን ከልባችሁ አታውጡ። ምንም ይሁን ምን - እንደ ሀገር የሚሆን ነገር የለም" ድምፃዊ ተሾመ ምትኩ (ዳግም የቀረበ)

አንጋፋው ድምፃዊ ተሾመ ምትኩ፤ ገጣሚና ሙዚቃ ቀማሪም ነው። ከሙዚቃ ዓለም አዘላለቁ እስከ ስደት ሕይወቱ አንስቶ ያወጋል። (ዳግም የቀረበ)