Listen to interviews, features and community stories from the SBS Radio Amharic program, including news from Australia and around the world. - የአውስትራሊያና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን አካትቶ፤ ቃለ ምልልሶችን፣ ዘገባዎችንና የማኅበረሰብ ታሪኮችን ከኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ ፕሮግራም ያድምጡ።
ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን በሚቀጥለው ሳምንት የቀጥታ ሁለትዮሽ ውይይት ሊጀምሩ ነው
አማኑኤል የአዕምሮ ልዩ ሆስፒታል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ100 ሺህ በላይ ለሆኑ ተገልጋዮች የሕክምና አገልግሎት መስጠቱን ገለጠ
አቶ ዳንኤል አለማር ከዘጸአት የኢትዮጵያውያን ወንጌላውያን ህብረት የህንጻ አሰሪ ሰብሳቢ ፤ በሜልበርን ከተማ በመጪው ቅድሚ የሚመረቀው የቤተክርስቲያን ህንጻ ፤ ህብረተሰቡ ከሌለው አቅሙ ቀንሦ ለትውልዱ እና ለመጪው ትውልድ ያሳነጸው ሲሆን ፡ በህንጻ አሰሪው ኮሚቴው ስም ምስጋናዪን አቀርባለሁ ብለዋል ። አያይዘውም በምርቃቱ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲገኙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ።
የፈረንሳዩ ፕሬዚደንት ኢማኑኤል ማክሮን "ኢራን ውስጥ የሥርዓት ለውጥ ማድረግ ካስፈለገ በኢራን ሕዝብ እንጂ በቦምብ አይደለም" ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስን የሥርዓት ለውጥ ዕሳቤ ተቹ
በሳዑዲ ዓረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ 37 ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ይጠብቃቸዋል
በሺህዎች የሚቆጠሩ አውስትራሊያውያን ኢራንና እሥራኤልን ለቅቀው ወደ አውስትራሊያ ለመመለስ ተመዝግበዋል
አውስትራሊያ በሩስያ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦችን ጣለች
በወንጀል የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ በማስመሰልና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀሎችን የሚመረምሩ አካላት አስገዳጅ ሆኖ ሲገኝ ከግድያ በስተቀር ያሉ የምርመራ መንገዶችን የሚፈቅደውና አነጋጋሪ የሆነው አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ
Learn how to congratulate someone on their work or wedding anniversary. - Learn how to congratulate someone on their work or wedding anniversary.
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት አሜሪካ እንደምትደግፍ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር አስታወቁ
Learn how to ask for medical help when in an emergency department. - Learn how to ask for medical help when in an emergency department.
ኳንታስ የጄት ስታር እስያ በረራውን ገታ፤ የሲድኒ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጠናቀቀ
ፕሪሚየር ጀርሚ ሮክሊፍ ክፍለ ሀገራዊ ምርጫ እንዲካሔድ የታዝማኒያን እንደራሴ ጠየቁ
ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓልን አስመልክተው የSBS አስተዋፅዖዎችንና ሚና በምልሰት አንስተው ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።
በኢትዮጵያ ከሚገኙ 31 ባንኮች ውስጥ ሶስቱ ብቻ ሴት የቦርድ ሊቀመንበር እንዳላቸው ተመለከተ
የቀድሞው የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የፑንትላንድ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር አብዲወሊ መሐመድ ዓሊ፤ በሶማሊያ ውስጣዊ ችግሮች፣ በሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነትና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ዙሪያ የተካሔደ ውይይት (March 2017)። የSBSን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ የቀረበ።
ሼህ አብዱራህማን ሀጂ ከቢር በአውስትራሊይ የእስልምና እምነት ተከታዮች መሪ ፤ የኢድ አል አድሀ በአል ሀይማኖታዊ ዳራው ፤ ነብዩ ኢብራሂም ልጃቸው እስማኤልን ለመስእዋት ያቀረቡበት እና ፤ የአላህን ቃል መስማታቸውን እና መታዘዛቸውን ያስመሰከሩበት እንደሆነ ይናገራሉ ።
ምልሰታዊ ምልከታ፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ ከድምፃዊ ፋንታሁን ሸዋንቆጨው ጋር የተካሔደ ቃለ ምልልስ።
ምልሰታዊ ምልከታ፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ ከድምፃዊት ኤደን ገብረሥላሴ ጋር ያካሔድነው ቃለ ምልልስ።
አምባሳደር አንዋር ሙክታር መሐመድ በአውስትራሊያ የኢፌዴሪ ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ፤ የSBSን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።
አቶ ተካ አዲስ፤ የቪክቶሪያ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ፤ በሥራ አስፈፃሚ አባላት መካከል ተከስቶ ያለውን የአተያይ ልዩነት ማጥበብ እንዳልተቻለና መፍትሔ እንደሚያሻ ይናገራሉ። ግለ ምክረ ሃሳባቸውንም ያጋራሉ።
የሜልበርን መካነ ሰላም ቅዱስ ልደታ ለማርያም ወገብርኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ የሰበካ ጉባኤ አባላትና ምዕመናን የቤተክርስቲያን ግንባታ ሂደት፣ የምዕመናን ሕብረትና የአስተዋፅዖ ፋይዳዎች አንስተው ይናገራሉ።
የSBS አማርኛ አገልግሎት ራዲዮ ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ ከጋዜጠኛነት ሙያ ጅማሮው ተነስቶ የSBS ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞን ከአማርኛ አገልግሎቱ ጋር አሰናስሎ ማኅበረሰባዊና ሉላዊ አስተዋፅዖዎችን ያነሳል።
ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ በኢትዮጵያ የSBS አማርኛ አገልግሎት ዋና ዘጋቢ ነው። የSBSን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል አስመልክቶ የግል የሙያ ተሞክሮዎቹን፣ የSBS እና የSBS አማርኛ አስተዋፅዖዎችን ነቅሶ ግለ አተያዩን ያጋራል።
አውስትራሊያ ውስጥ የተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች ምጣኔ ሃብት ላይ የ2 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ወጪን ማስከተላቸው ተመለከተ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 7.7 ቢሊየን ብር ተዘርፏል ቢባልም 'የዝርፊያ ሙከራ እንጂ ዘረፋ አልተካሔደብኝም' አለ
Australia has a dark chapter of history that many are still learning about. Following European settlement, Aboriginal and Torres Strait Islander children were removed from their families and forced into non-Indigenous society. The trauma and abuse they experienced left deep scars, and the pain still echoes through the generations. But communities are creating positive change. Today these people are recognised as survivors of the Stolen Generations. - አውስትራሊያ አሁንም ድረስ አያሌዎች እየተማሩት ያለ የጨለማ ታሪክ ምዕራፍ አላት። የአውሮፓውያን ሠፈራን ተከትሎ፤ የአቦርጂናልና ቶረስ መሽመጥ ደሴት ሕፃናት ከወላጆቻቸው በኃይል ተነጥቀው ነባር ዜጎች ወደ አልሆነው ሕብረተሰብ ተወሰዱ። በውስጡ ያለፉበት የስሜት ሁከትና ጉስቁልና ጠባሳዎችን ጥሎባቸው አለፈ፤ ሕመሙ ከትውልድ ትውልድ ተሸጋግሮ እስካሁንም አለ። ይሁንና ማኅበረሰባቱ አዎንታዊ ለውጥን እየፈጠሩ ነው። ዛሬ እኒህ ሰዎች በተሰረቀው ትውልድ ተቋቋሚነት ይነሳሉ።
SBS ከ1975 አንስቶ የአውስትራሊያ መድብለባሕል የማዕዘን ደንጊያና ድምፅ ማጉሊያ ሆኖ እስከ 2025 የተጓዘበትን የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞውን ጁን 9 / ሰኔ 2 ያከብራል። ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት ምልሰታዊ ምልከታቸውን ያጋራሉ።
የአቶ ብዙአየነህ ኃይለማርያም ይፍጠር ድንገተኛ ሕልፈተ ሕይወት ከቤተሰብ እስከ ማኅበረሰብ አባላት ብርቱ ሐዘንን ፈጥሯል። ሕልፈታቸውንም ተከትሎ አብሮ አደጋቸው አቶ ኬኔዲ ገብረየሱስ "ብዙአየነህ በማኅበረሰቡ ውስጥ ጥሩ ስም ነበረው። ሕልፈቱ በጣም የሚያስደነግጥ፤ በጣም የሚያሳዝን ነው፤ ማኅበረሰቡ ይጎዳል" ሲሉ፤ የረጅም ጊዜ ወዳጃቸው አቶ ልዑል ፍስሃ "ብዙአየነህ ላመነበት ነገር በትጋት የሚሠራ፤ ለዕውቀት ከፍተኛ ቦታ የሚሰጥ፤ ትልቅ ሰው ነበር። ሐዘናችን ጥልቅ ነው" ብለዋል። የአቶ ብዙአየነህ ፀሎተ ፍትሐት ሐሙስ ግንቦት 21 ቀን 2017 / ሜይ 29 ቀን 2025 በሜልበርን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከጠዋቱ 9:00 am ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ይፈፀማል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 14.5 ሚሊየን መንገደኞችን አጓጓዘ፤ 5.6 ቢሊየን ዶላር ገቢ አገኘ
Alfred is an Indonesian migrant, and Clinton is an Aboriginal man from Western Australia. Their friendship changed the way Alfred understood his identity as a migrant Australian. - አልፍሬድ የኢንዶኔዥያ ፍልሰተኛ ሲሆን፤ ክሊንተን የምዕራብ አውስትራሊያ ነባር ዜጎች ሰው ነው። ወዳጅነታቸው ከአልፍሬድ አውስትራሊያዊ ፍልሰተኛ ማንነት ግንዛቤ ጋር ተያይዞ ለመለወጥ በቅቷል።
ጋዜጠኛ ማርታ ፀጋው፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ በምልሰታዊ ምልከታና ከአድማስ ባሻገር የመጪ ጊዜያት አገልግሎት አተያይዋንና መልካም ምኞቷን አጣምራ ታወጋለች።
የኢፌዴሪ ፖሊስ 47 የጤና ባለሙያዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሔደ መሆኑን አስታወቀ
"ጌታሁን በጣም ጥሩ ሰው ነው፤ ተፈጥሮን የሚያደንቅ ነበር። ብንለያይም በሕልፈቱ በጣም አዝኛለሁ" በመኪና አደጋ ሕይወቱ ያለፈ የጌታሁን ዝግታ የቀድሞ ባለቤት ዳናዊት ሕሉፍ። የወጣት ገዛኸኝ ታደሰ ፀሎተ ፍትሐት ቅዳሜ ግንቦት 16 / ሜይ 24 በደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን 9:30 am ከተከናወነ በኋል የቀብር ሥነ ሥርዓቱ የሚፈፀም ሲሆን፤ የአቶ ጌታሁን ዝግታ የቀብር ሥነ ሥርዓት በቅርቡ ይከናወናል።
በአሁኑ ወቅት በሕይወት የሌሉት የቀድሞው የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ስዮም መስፍን በሕይወት ሳሉ ከSBS አማርኛ ጋር ባካሔዱት ቃለ ምልልስ የኢትዮ - ቻይና ዲፕሎማሲያዊና ምጣኔ ሃብታዊ ግንኙነቶችንና የወደፊት ውጥኖቻቸውን አጋርተው ነበር (የSBS 50ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ዳግም የቀረበ)።
በአሁኑ ወቅት በሕይወት የሌሉት የቀድሞው የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ስዮም መስፍን በሕይወት ሳሉ ከSBS አማርኛ ጋር ባካሔዱት ቃለ ምልልስ ከትጥቅ ትግል ጅማሯቸው ተነስተው፤ ከሕወሓት አመራር በፈቃዳቸው ስለምን እንደተሰናበቱ አስረድተው ነበር (የSBS 50ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ዳግም የቀረበ)።
የአማራ ክልል ዳኞች በፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊ ወይም አወዛጋቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በማናቸውም ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሃሳብ እንዳይሰጡ የሚከለክል ደንብ ፀደቀ
በ77 ዓመታቸው ከአንድ አሠርት ዓመት በፊት ከእዚህ ዓለም ከመለየታቸው በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪ፣ ደራሲ፣ ጋዜጠኛና ዲፕሎማት ከነበሩት አምባሳደር ዘውዴ ረታ ጋር በሙያ ሕይወታቸው፣ የሥነ ፅሁፍ በረከቶቻቸውና ዲፕሎማሲ ዘርፍ ዙሪያ አተያያቸውን አጋርተውናል። የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግም ዳግም አቅርበነዋል።
የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠን ቀነሰ
በሜልበርን የኢሬቻ ቱሉ / አፍራሳ ክብረ በዓል አስተባባሪዎች ኦቦ ዓለማየሁ ቁቤ፣ ኦቦ በንቲ ሆሉቃና አደይቱ ሚደቅሳ የክብረ በዓሉን ፋይዳዎችና የአከባበር ሂደቱን አንስተው ያስረዳሉ።
ሰሞኑን በሀገር አቀፍ ደረጃ 'ከፊል' ያሉትን የሥራ ማቆም አድማ በማድረግ ላይ ያሉት የጤና ባለሙያዎች ያነሷቸው የደመወዝ፣ የጥቅማ ጥቅምና ምቹ የሥራ ሁኔታ ጥያቄዎቻቸው ምላሽ ካላገኙ 'ሙሉ' የሥራ ማቆም አድማ ሊያደርጉ እንደሚችሉ አሳሰቡ፤ የጤና ሚኒስቴር አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀ።
"የፉትስክሬይ ሮታሪ ክለብ፣ በጎ ፈቃደኞች፣ የአውስትራሊያ የሕክምና ተቋማትንና ለ19ኛ ዙር የተለያዩ የእርዳታ ቁሳቁሶችን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ የወጪ ድጋፋቸውን የቸሩ ኢትዮጵያውያን - አውስትራሊያውያን የማኅበረሰብ አባላትን በአውስትራሊያ ኢፌዴሪ ኤምባሲ ስም አመሰግናለሁ" አምባሳደር አንዋር ሙክታር መሐመድ
Learn how to talk about time. - Learn how to talk about time.
The migration system is complex and confusing. Experts say a lack of accessible support and credible information is leading to visa abuse. - የፍልሰት ሥርዓት ውስብስብና አደናጋሪ ነው። ጠበብት ተደራሽነት ያለው ድጋፍና ተአማኒነት ለአግባብ የለሽ የቪዛ ተፅዕኖ እንደሚያመራ ይናገራሉ።
በኢትዮጵያ የልጅነት እርግዝና 13 በመቶ መድረስ አሳሳቢ ሆኗል
ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚን ጨምሮ አዲሱ የሌበር መንግሥት ካቢኔ አባላት ቃለ መሐላ ፈፀሙ
'በሕገ ወጥ የማዕድን ቁፋሮና ዝውውር ውስጥ የክልሎችና የአካባቢ ባለስልጣናት እጆች አሉበት' አሉ የምክር ቤት አባላት
ወ/ት ሰላማዊት ወሰን ከብሪስበን "በተለይ ያለ አባት ልጆቻቸውን ላሳደጉ እናቶች 'እንኳን ለእናቶች ቀን አደርሳችሁ' ማለት እፈልጋለሁ" ሲሉ፤ ወ/ሮ ቤተልሔም ጥበቡ ከሜልበርን "እናትነትን በቃላት መግለፅ አይቻልም፤ እናትነት ትልቅ ስጦታ ነው" ይላሉ፤ ወ/ሮ ሜሮን ተስፋዬም "የእናቶችን ቀን ማሰብ የሚገባን በየዕለቱ ነው" በማለት የእናቶችና የእናት ተምሳሌዎችን የክብር መዘከሪያና ሞገስ ማላበሻዋን "የእናቶች ቀን" አስመልክተው የእናትና ልጅ ግለ ሕይወታቸውን አጣቅሰው ያጋራሉ። አቶ ኢዮብ ቀፀላም ከሲድኒ፤ ሀገር ቤት ለሚገኙት ውድ እናታቸው የእናቶች ቀን መልካም ምኞታቸውን ያስተላልፋሉ።
በመላው አለም ለምትገኙ እናቶች በሙሉ እንኳን ለእናቶች ቀን አደረሳችሁ ። " እናቶችን ማክበር ማለት ሰላምን መፍጠር ለእኩልነት መቆም ማለት ነው " በሚል መርህ የተነሳቸው አሜሪካዊቷ አና ጃርቪስ ቀኑ ሲከበር ዛሬም ድረስ የእናቶች ቀን እናት በመባል ትታወሳለች።
ቴዎድሮስ ተሾመ ከበደ፤ ፀሐፊ፣ ዳይሬክተርና ተዋናይ ነው። በቅርቡ ሰሞነኛ የነበረውን ዓባይ ወይስ ቬጋስ ፊልሙን 'የኢትዮጵያ ኔትፊሊክስ' ሲል በጠራው Habeshaview TV አማካይነት ለሕዝብ ዕይታ አቅርቧል። ስለ ፊልሙ ጭብጥ፣ በባሕር ማዶና ሀገር ቤት ያሉ የሩቅ ርቀት ፍቅርና ፈተናዎችን ከሌሎች ፈታኝ ማኅበራዊ የሕይወት ጉዞዎች ጋር አሰናስሎ ይናገራል።